17/12/2025
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ'4-Bar Prosthetic Knee Joint' ፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውይይት አካሄደ።
********************************************
በውይይቱም የፕርጀክቱ ዋና ተመራማሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሻ/ቃ ዶ/ር ሰለሞን ሰይድ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን አጠቃላይ ሁነታ ለአመራሮቹ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ፤ በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ ሙሉ የዲዛይን ስራ ተጠናቆ የፕሮቶታይፕ ምርት ስራዉ ሀገር በቀል አምራች ኢንዱስትሪ ከሆነዉ ከአቢሲኒያ ፍሌክሴብል ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ማምረቻ አክሲዮን ማህበር ጋር በመሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዉ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 64% በመቶ የተጠናቀቀ መሆኑን ለቡድኑ አስረድተዉ በቀጣይ የምርት ስራውን አጠናቆ ወደ ክሊኒካል የሙከራ ስራ እንደሚገባ ዋና ተመራማሪዉ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሰ በቀረበዉ የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት ደስተኛ መሆናቸዉን በመግለጽ ለኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ አመራር እና ለፕሮጀክት ቡድኑ ምስጋናቸዉን አቅርበዉ ፤ ፕሮጀክቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ከማጠናከር ባለፈ ሀገራዊ ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን በማስረዳት፤ ፕሮጀክቱ በዘርፉ የሚታዩትን ተግዳሮቶች በመፍታት ከሚያስገኘዉ ፋይዳ አንጻር የፕሮጀክት ቡድኑን አቅም የሚያጎለብቱ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችንና ሌሎች ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ለማመቻቸት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የሚናዉን እንደምወጣ ገልፀዉ ፤ በቀጣይ የምሰሩ ቀሪ ስራዎችም ርብርብ የሚጠይቁና በተለየ ትኩረት የምሰሩ መሆናቸዉን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሰ ለፕሮጀክት ቡድኑ አስረድቷል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዴየር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ሂደት ጥሩ መሆኑን አንስተው ፤ ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች አንፃር ቀሪ የክሊኒካል የሙከራ ስራው በፍጥነት የሚጀመርበትና ከፕሮቶታይፕ ወደ አጠቃላይ ምርት የሚገባበትን ሁኔታ በጋራ ለማመቻቸትና ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀው፤ ከፕሮጀክቱ ባሻገር እንደተቋም ካሪኩለም ተቀርጾለት በምርምርና በመማር ማስተማር ዙሪያ ታቅዶ ወደ ስራ የሚገባበትን ሁነታ በማሰብ ለተሻሉ ስራዎች ከወድሁ በመዘጋጀት በጋራ የተጀመሩት የትብብር ስራዎች ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ አሳስበዉ፤ትኩረት የሚሹ የቀጣይ ስራዎችን በማመላከት አገልግሎቱን ጎብኝተዋል።