Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS

Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS, Orthotics & Prosthetics Service, Mikililand Center, Addis Ababa.

25/11/2025
Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር በመሠረታዊ የማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።********...
22/11/2025

Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር በመሠረታዊ የማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።
*******************************
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት Amref (African medical Research & Education Foundation/ በማገገሚያ ህክምና ዘርፍ ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በጋራ ለመስራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ልባዊ ምስጋናቸዉን አቅርበዉ፤በዘርፉ የሚሰጠዉን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩትን የሁለትዮሽ ስራዎቻችንን አጠናክሮ በማስቀጠል አጋርነታችሁን እንድትወጡ በማለት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ አሳስበዋል።

አያይዘዉም ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ የስልጠናዉ ዋና ዓላማ የማገገሚያ ህክምና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ዉጤታማነት የመለካትና የጥራት ስታንዳርዶች ትግበራ ሂደት በማጠናከር የተገልጋዮችን የጤና ሁነታ ለማሻሻልና በሱስ ማገገም ህክምና ዘርፍ Evidance based holistic treatment (በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የሆሊስቲክ ህክምና) አገልግሎትን በማጎልበት ዉጤታማ የማገገም ሂደት ለማረጋገጥ ያለመ ስልጠና መሆኑን ም/ዋና ስራ አስፈጻሚዉ ገልፀዋል።

በAmref Health Africa የእናቶች፣ህጻናትና አፍላ ወጣቶች ጤና ፕሮግራም አስተባባሪ እና የ 'VERSO' ፕሮጀክት ማነጀር ወ/ሮ ብለን መንግስቱ እንደገለፁት Amref Health Africa በአፍሪካ ለሦስት አስርት ዓመታት ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለሁለት አስርት ዓመታት በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ አለም አቀፍ ገብረ ሰናይ ድሪጂት መሆኑን ገልፀዉ፤በጣሊያን መንግስት ድጋፍ የሚተገበረዉ 'VERSO'' ፕሮጀክት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎትን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ላይ በ''Gender based violence እና በ Mental health'' ላይ ትኩረት በማድረግ የሚሰራ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ፕሮጀክት መሆኑን አስረድተዋል።

በመቀጠልም ወ/ሮ ብሌን መንግስቱ በሱስ ምክንያት ብዙሃኑ ወጣቶች የችግሩ ሰለባ ከመሆናቸዉ ጋር ተያይዞ በማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ዘርፉ የአገልግሎት ጥራት ከማሳደግ አንፃር የአቅም ግምባታ ስራዎች ላይ ተቀናጅቶ በጋራ መስራት የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከሱስ ህመም በማገገም አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ለማድረግ ይረዳል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ከ 9/3/18 ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይሰጥ የነበረዉ ስልጠና በ'Quality Audit, Addiction Rehabilitation,እና Data Managment' ሲሆን፤ Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ባለሙያዎች የተሰጠዉ ስልጠና ለቀጣይ ስራዎቻችን ከፊተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል በማለት የስልጠናዉ ተሳታፊዎች ሀሳባቸዉን ገልፀዋል።

17/11/2025
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች
16/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች

16/11/2025

DHIBEE VAAYIRESII MAARBERG
Maalummaa Dhibichaa, Karaa Daddarbiinsaa fi Tooftaalee Ittisaa


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

12/11/2025

ወቅታዊ የጤና ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ27ኛዉ የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ  ላይ  ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ። *****************************...
26/10/2025

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ27ኛዉ የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ።
**********************************************
ዘላቂ ኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ለጠንካራ የጤና ስርአት” በሚል መሪ ቃል በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ በተካሄደዉ 27ኛው የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ፤የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታዎች ፤የፌዴራል የተጠሪ ተቋማትና የሆስፒታል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፤ የክልል ጤና ቢሮ ሃላፊዎች፤ የጤና ባለሙያዎች፤ የልማት አጋሮች እና ባለድርሻ አካላት በታደሙበት 27ኛዉ የጤናዉ ዘርፍ ዓመታዊ የምክክር ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች፤ ያስመዘገባቸዉ ስከቶች እና የቀጣይ የትኩረት አቃጣጫዎችን በተዘጋጀዉ ኤግዝቢሽን ላይ ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ።

አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ማክሰኞ፤ጥቅምት 11 /2018 ዓም.************************************************አህጉራዊ ተስፋ የተጣለበት የተቀናጀዉ የህክምና ማዕከል
21/10/2025

አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ማክሰኞ፤ጥቅምት 11 /2018 ዓም.
************************************************
አህጉራዊ ተስፋ የተጣለበት የተቀናጀዉ የህክምና ማዕከል

14/10/2025
ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፊታ ዘመን ድል ብስራት ለብሄራዊ አንድነታችን ፤ለሉአላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ!                        ***************     ...
13/10/2025

ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፊታ ዘመን ድል ብስራት ለብሄራዊ አንድነታችን ፤ለሉአላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ!
***************
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት

12/10/2025

አገልግሎቱ ከነበረብን ችግር ወጥተን አዲስ ሕይወት እንድንጀምር ተስፋ ሰጥቶናል

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፡-‎በኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ያገኙት ድጋፍ ከነበረባቸው ሱስ ተላቀው አዲስ የሕይወት ምዕራፍ እንዲጀምሩ ተስፋ እንደሆናቸው ቀደም ሲል በተለያየ ሱስ ተጠምደው የነበሩ ግለሰቦች ገለጹ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው በተለያየ ሱስ ተጠምደው የነበሩ ግለሰቦች የቤተሰብ መበታተን፣ የሥራ ማጣት እና የከፍተኛ የጤና መቃወስ አደጋ እንዳስከተለባቸው ይናገራሉ።

ነገር ግን፣ በኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ያገኙት ድጋፍ ለብዙዎች ከጨለማው ጉዞ ወጥተው አዲስ የሕይወት ምዕራፍ እንዲጀምሩ እንዳስቻላቸው ይገልፃሉ፡፡

‎ወጣት እንዳለልኝ ታዬ ለዓመታት በመጠጥና በጫት ሱስ ሲሰቃይ እንደነበር ይናገራል።

ሱሱ በሕይወቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበትና ወደ ውድቀት እንዳመራው በቁጭት ይገልጻል፡፡

ከዚህ አስከፊ ሕይወት ለመውጣት መወሰኑን ተከትሎ ወደ አገልግሎቱ መግባቱን ከሱስ ነጻ መሆን መቻሉን በደስታ ይናገራል።

‎በተመሳሳይ፣ ጌትነት ተረፈ በአገልግሎቱ ውስጥ ባሳለፋቸው ጊዚያት ከሱስ ነጻ የሚያደርገውን አገልግሎት እና እንክብካቤ ማግኘቱን ይገልጻል፡።

ጌትነት የሥነ ልቦና ድጋፍን ጨምሮ የተለያዩ አስፈላጊ አገልግሎቶች እንደተሰጠው ጠቅሶ፣ በተደረገለት በቂ ድጋፍና እንክብካቤ ምክንያት ከሱስ ነጻ መሆኑን አመላክቷል።

‎አዲስ ሕይወት የጀመሩት እነዚህ ተጠቃሚዎች ለቀጣይ ሕይወታቸውን ለመቀየር ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት፣ በትጋት ሠርተው ሕይወታቸውን ለመለወጥ እንደሚሠሩ ተናግረው፤ ወጣቶች ራሳቸውን ከሱስ እንዲጠብቁ አጥብቀው መክረዋል።

‎የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ገረመው ወንዶ በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ በተለያዩ ሱሶች የተጠመዱ ግለሰቦች ከነበረባቸው ችግር እንዲላቀቁ በትጋት እየሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ወደ አገልግሎቱ ለሚመጡ ግለሰቦች ከሱስ እንዲያገግሙ ከሚረዳ ድጋፍ በተጨማሪ፣ ወደ ሥራ እንዲመለሱ የሚያስችላቸውን የክህሎት ሥልጠና ጭምር እንደሚሰጥ አብራርተዋል።

በቀጣይ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሳደግ የማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፤ በሱስ ችግር የተጠቁ ወደ ማዕከሉ በመምጣት አገልግሎት እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል።

#ኢዜአ

የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ተከበረ።*************************************************የዘንድሮው የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በዓ...
10/10/2025

የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ተከበረ።

*************************************************

የዘንድሮው የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ 34ኛ ግዜ በሀገራችን ለ14ኛ ግዜ "የአእምሮ ጤና አገልግሎትን በድንገተኛና ከፍተኛ አደጋ ወቅት ተደራሽ እናድርግ" በሚል መሪ ሃሳብ፣ በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በተለያዩ መርኃ ግብሮች ተከብሯል። ‎ ‎

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሰ የአእምሮ ሕክምና ለረጅም ጊዜ ትኩረት ሳይሰጠው መቆየቱንና ‎ከለውጡ በኋላ በመንግስት በተሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሁለንተናዊ ጤንነት በማረጋገጥና ለአእምሮ ጤና አገልግሎት ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ ተጨባጭ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

ለአብነትም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ገፈርሳ ሳይት በ27 ሄክታር መሬት ላይ እንደ ሀገር የመጀመሪያ የሆነዉ ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የማገገሚያ ህክምና ማዕከል ፕሮጀክት ግንባታ መከናወን መጀመሩንም ተናግረዋል። ‎ ‎

የጤና ሚኒስቴር ማኅበረሰቡና ሁሉም ባለድርሻ አካላት የአእምሮ ጤና አገልግሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት እና ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመረውን ተግባር ለማሳካት ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል። ‎

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ከፊተኛ አማካሪ እና
ተወካይ አቶ ሌሌሳ አማኑኤል እንደተናገሩት በድንገተኛና ከፍተኛ አደጋዎች ወቅት የአእምሮ ጤና አገልግሎት መስጠት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዉ በተለያዩ አደጋዎች ሳቢያ ለስነ-ልቦና ቀውስ ለተጋለጡ ዜጎች ፈጣንና የተቀናጀ የአእምሮ ጤና አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ‎ ‎

መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በሀገሪቱ በሚገኙ የጤና ተቋማት የአእምሮ ህክምና አገልግሎቱን በማስፋት ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ‎ ‎

በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ህይወት ሰለሞን የዘንድሮው መሪ ሀሳብ የድንገተኛ አደጋዎችን ተከትሎ የሚከሰተውን የአእምሮ ጤና ችግር ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት ቅድሚያ መሰጠቱን አመላካች መሆኑን ገልፀዉ ፤ ለዚህም መንግስት የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ ችግሩን ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አክለው ገልጸዋል። ‎ ‎

የኢትዮጵያ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን በበኩላቸው በአእምሮ ጤናና ህመም ላይ በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ውስጥ የግንዛቤ ክፍተቶች፤ በህሙማኑ ላይ አድሎና መገለል መኖር የህክምናው ተደራሽነት ውስንነት የሚያመጣ መሆኑን አንስተው በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ የአእምሮ ጤና ክብካቤና የአእምሮ ህመም ህክምና እንዲሰጥ እየተሰራ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዉ፤የአዕምሮ ጤና ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኝ፣ ጥበቃ እንዲደረግለትና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን፣ በተለይም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግሮች ለተጎዱ ሰዎች ተደራሽ እንዲሆን መስራት ይገባናል ብለዋል።

በመረሃ ግብሩ በዘርፉ ልዕቃን ጥናትና ምርምር ቀርበዉ የፓናል ዉይይት ተደርጎበት ምክረ ሃሳብ ተሰጥቶበት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጧል።

Address

Mikililand Center
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram