Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS

Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS, Orthotics & Prosthetics Service, Mikililand Center, Addis Ababa.

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ'4-Bar Prosthetic Knee Joint' ፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ  ጋር ውይይት አካሄደ።*****************...
17/12/2025

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ'4-Bar Prosthetic Knee Joint' ፕሮጀክት አፈጻጸም ላይ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውይይት አካሄደ።

********************************************
በውይይቱም የፕርጀክቱ ዋና ተመራማሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ሻ/ቃ ዶ/ር ሰለሞን ሰይድ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን አጠቃላይ ሁነታ ለአመራሮቹ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ፤ በዚህም መሰረት የፕሮጀክቱ ሙሉ የዲዛይን ስራ ተጠናቆ የፕሮቶታይፕ ምርት ስራዉ ሀገር በቀል አምራች ኢንዱስትሪ ከሆነዉ ከአቢሲኒያ ፍሌክሴብል ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ማምረቻ አክሲዮን ማህበር ጋር በመሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዉ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 64% በመቶ የተጠናቀቀ መሆኑን ለቡድኑ አስረድተዉ በቀጣይ የምርት ስራውን አጠናቆ ወደ ክሊኒካል የሙከራ ስራ እንደሚገባ ዋና ተመራማሪዉ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሰ በቀረበዉ የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት ደስተኛ መሆናቸዉን በመግለጽ ለኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ አመራር እና ለፕሮጀክት ቡድኑ ምስጋናቸዉን አቅርበዉ ፤ ፕሮጀክቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ከማጠናከር ባለፈ ሀገራዊ ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን በማስረዳት፤ ፕሮጀክቱ በዘርፉ የሚታዩትን ተግዳሮቶች በመፍታት ከሚያስገኘዉ ፋይዳ አንጻር የፕሮጀክት ቡድኑን አቅም የሚያጎለብቱ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችንና ሌሎች ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ለማመቻቸት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የሚናዉን እንደምወጣ ገልፀዉ ፤ በቀጣይ የምሰሩ ቀሪ ስራዎችም ርብርብ የሚጠይቁና በተለየ ትኩረት የምሰሩ መሆናቸዉን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሰ ለፕሮጀክት ቡድኑ አስረድቷል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ኮማንዳንት ብርጋዴየር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ሂደት ጥሩ መሆኑን አንስተው ፤ ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች አንፃር ቀሪ የክሊኒካል የሙከራ ስራው በፍጥነት የሚጀመርበትና ከፕሮቶታይፕ ወደ አጠቃላይ ምርት የሚገባበትን ሁኔታ በጋራ ለማመቻቸትና ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀው፤ ከፕሮጀክቱ ባሻገር እንደተቋም ካሪኩለም ተቀርጾለት በምርምርና በመማር ማስተማር ዙሪያ ታቅዶ ወደ ስራ የሚገባበትን ሁነታ በማሰብ ለተሻሉ ስራዎች ከወድሁ በመዘጋጀት በጋራ የተጀመሩት የትብብር ስራዎች ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ አሳስበዉ፤ትኩረት የሚሹ የቀጣይ ስራዎችን በማመላከት አገልግሎቱን ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባን አስመልክቶ ለአጠቃላይ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።********************************...
16/12/2025

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባን አስመልክቶ ለአጠቃላይ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።
*******************************************
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቶሎሳ ባይሳ እንደገለጹት የሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ሥርዓት ዋነኛ ዓላማዉ ሙስናን አስቀድሞ በመከላከል የግልጽነትና የተጠያቂነት ሥርዓትን በማስፈን ብልሹ አሰራሮች ላይ የጋራ ትግል ለማድረግ እና ለህዝባችን ፍትሃዊ አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ገልፆ፤ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ሰራተኞች ስራን በአግባቡና በወቅቱ በመስራት መብትና ግዴታቸውን በወል በመረዳት ህዝብ እና መንግስት ከእኔ ምን ይጠብቃል? የሚለውን ተገንዝቦ በተለየ ትኩረት መስራትና ትግል ማድረግ ይጠበቃል በማለት ገልጸዋል ።

አክለዉም አቶ ቶለሳ ‎የሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ሥርዓት የጥቅም ግጭትን በመከላከልና በማስወገድ ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራርን በማስፈን ውጤታማ የሆነ ምዝገባ ሥርዓት ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቁመዉ፤ በተሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት የዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ በተቋማችን በስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን አማካኝነት መመዝገብ ይኖርብናል ብለዋል።

የዲጂታል የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አስፈላጊነት ሀብትን ማሳወቅና ማስመዝገብ፣በመንግስት የአሰራር ሂደት ላይ ተጠያቂነት ለማስፈን፣ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ለመከላከልና የመልካም አስተዳደር ለማስፈን እና የመንግስት የስራ ኃላፊነትና የግል ጥቅም ሳይቀላቀሉ በየራሳቸው መንገድ የሚመሩበትን እና ሊፈጠር የሚችለውን ግጭት ለመግታት የሚረዳ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የቀድሞ የስነ-ምግባር እና የፀረ- ሙስና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሻምበል ነጋሳ ገልጸዋል።

አቶ ሻምበል ነጋሳ አያይዘዉም አዋጅ 668/2012 ቁጥር 8/2013 ስለ ሀብት ምዝገባ የሚደነግግ መሆኑን ጠቅሰዉ፤ ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ እና የመንግስት ሰራተኛ የዲጂታል ሀብት ማስመዝገብ የሚጠበቅበት መሆኑን ያስረዱ ሲሆን፤ ይህን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ያዘጋጀውም በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የስነ-ምግባርና ጸረ-ሙስና ቡድን መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

12/12/2025
እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!“ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት”       ኅዳር 29 ቀን ፡ የኢትዮጵያን ብሔሮች፣ ብሔ...
08/12/2025

እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

“ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት”

ኅዳር 29 ቀን ፡ የኢትዮጵያን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን !!!

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት
******* ******** ******** *******

25/11/2025
Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር በመሠረታዊ የማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።********...
22/11/2025

Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር በመሠረታዊ የማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ላይ ለተቋሙ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ።
*******************************
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት Amref (African medical Research & Education Foundation/ በማገገሚያ ህክምና ዘርፍ ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በጋራ ለመስራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ልባዊ ምስጋናቸዉን አቅርበዉ፤በዘርፉ የሚሰጠዉን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩትን የሁለትዮሽ ስራዎቻችንን አጠናክሮ በማስቀጠል አጋርነታችሁን እንድትወጡ በማለት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ አሳስበዋል።

አያይዘዉም ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ የስልጠናዉ ዋና ዓላማ የማገገሚያ ህክምና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ዉጤታማነት የመለካትና የጥራት ስታንዳርዶች ትግበራ ሂደት በማጠናከር የተገልጋዮችን የጤና ሁነታ ለማሻሻልና በሱስ ማገገም ህክምና ዘርፍ Evidance based holistic treatment (በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የሆሊስቲክ ህክምና) አገልግሎትን በማጎልበት ዉጤታማ የማገገም ሂደት ለማረጋገጥ ያለመ ስልጠና መሆኑን ም/ዋና ስራ አስፈጻሚዉ ገልፀዋል።

በAmref Health Africa የእናቶች፣ህጻናትና አፍላ ወጣቶች ጤና ፕሮግራም አስተባባሪ እና የ 'VERSO' ፕሮጀክት ማነጀር ወ/ሮ ብለን መንግስቱ እንደገለፁት Amref Health Africa በአፍሪካ ለሦስት አስርት ዓመታት ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ለሁለት አስርት ዓመታት በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ አለም አቀፍ ገብረ ሰናይ ድሪጂት መሆኑን ገልፀዉ፤በጣሊያን መንግስት ድጋፍ የሚተገበረዉ 'VERSO'' ፕሮጀክት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎትን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ላይ በ''Gender based violence እና በ Mental health'' ላይ ትኩረት በማድረግ የሚሰራ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ፕሮጀክት መሆኑን አስረድተዋል።

በመቀጠልም ወ/ሮ ብሌን መንግስቱ በሱስ ምክንያት ብዙሃኑ ወጣቶች የችግሩ ሰለባ ከመሆናቸዉ ጋር ተያይዞ በማገገሚያ ህክምና አገልግሎት ዘርፉ የአገልግሎት ጥራት ከማሳደግ አንፃር የአቅም ግምባታ ስራዎች ላይ ተቀናጅቶ በጋራ መስራት የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከሱስ ህመም በማገገም አምራች ዜጋ እንዲሆኑ ለማድረግ ይረዳል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ከ 9/3/18 ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ይሰጥ የነበረዉ ስልጠና በ'Quality Audit, Addiction Rehabilitation,እና Data Managment' ሲሆን፤ Amref Health Africa ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ባለሙያዎች የተሰጠዉ ስልጠና ለቀጣይ ስራዎቻችን ከፊተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል በማለት የስልጠናዉ ተሳታፊዎች ሀሳባቸዉን ገልፀዋል።

17/11/2025
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች
16/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች

16/11/2025

DHIBEE VAAYIRESII MAARBERG
Maalummaa Dhibichaa, Karaa Daddarbiinsaa fi Tooftaalee Ittisaa


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

12/11/2025

ወቅታዊ የጤና ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ27ኛዉ የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ  ላይ  ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ። *****************************...
26/10/2025

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በ27ኛዉ የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ።
**********************************************
ዘላቂ ኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ለጠንካራ የጤና ስርአት” በሚል መሪ ቃል በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ በተካሄደዉ 27ኛው የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማት ክላስተር አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ፤የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታዎች ፤የፌዴራል የተጠሪ ተቋማትና የሆስፒታል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፤ የክልል ጤና ቢሮ ሃላፊዎች፤ የጤና ባለሙያዎች፤ የልማት አጋሮች እና ባለድርሻ አካላት በታደሙበት 27ኛዉ የጤናዉ ዘርፍ ዓመታዊ የምክክር ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ተቋሙ የሚሰጠዉን አገልግሎቶች፤ ያስመዘገባቸዉ ስከቶች እና የቀጣይ የትኩረት አቃጣጫዎችን በተዘጋጀዉ ኤግዝቢሽን ላይ ለጉባኤዉ ተሳታፊዎች አስተዋወቀ።

አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ማክሰኞ፤ጥቅምት 11 /2018 ዓም.************************************************አህጉራዊ ተስፋ የተጣለበት የተቀናጀዉ የህክምና ማዕከል
21/10/2025

አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ማክሰኞ፤ጥቅምት 11 /2018 ዓም.
************************************************
አህጉራዊ ተስፋ የተጣለበት የተቀናጀዉ የህክምና ማዕከል

Address

Mikililand Center
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram