28/01/2024
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት፣ በሮም ጣልያን በተሰናዳ ክብረ በዓል የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸልመዋል።
ሽልማቱ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በምግብ ዋስትና እና በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት ላሳዩት ርዕይ፣ አመራር እና ቁርጠኝነት፣ ብሎም ፈጣን፣ ተለዋዋጭ እና ፈታኝ በሆነው ከባቢያዊ ሁኔታ በስንዴ ምርት ራስን ለመቻል በተከተሉት ፈጠራዊ መፍትሔ ዕውቅና ለመስጠት የተበረከተ ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የተለያዩ ሀገራት ከፍተኛ ልዑካን ቡድኖች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች፣ በጣልያን የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ተልዕኮዎች አባላት እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተወካዮች በተገኙበት ሽልማቱን ተቀብለዋል።
ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት ዓመታት በግብርናው መስክ ቁልፍ ኢንቨስትመንቶችን ያደረገች ሲሆን በስንዴ ምርት ራስን የመቻል ሥራዎችን በማከናወን በዐበይት ምርቶችም ላይ ከፍተኛ ዕድገት አስመዝግባለች።
In a ceremony hosted by the United Nations Food and Agriculture Organization in Rome, Italy, Prime Minister Abiy Ahmed has been awarded the prestigious FAO Agricola Medal, according to the organization, for his vision, leadership and commitment to food security and nutrition as well as the pursuit of innovative solutions in wheat self-sufficiency in the context of fast-changing and challenging circumstances.
The Prime Minister received the Agricola Medal in the presence of high-level delegates of various countries, representatives of international organizations, diplomatic missions in Italy and private sector representatives.
For the past five years, Ethiopia has been making critical investments in the agricultural sector and pursuing wheat self sufficiency endeavors marking significant growth across major commodities.