Dr. Seid Arage

Dr. Seid Arage Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dr. Seid Arage, Medical and health, Addis Ababa.

Maternal Fetal Medicine sub specialist
( በእናቶችና ጽንስ ህክምና አደጋ ላይ ወይም ውስብስብ ችግሮች ላይ ያተኮረ ከፍተኛ ህክምና )
ረዳት ፕሮፌሰር
አድስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
በረካ የእናቶችና ህጻናት ማእከል
+ 251910161920

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በክረምት ወቅት ሲሰጥ የነበረው ነጻ ህክምና አገልግሎት  በመላ አድስ አበባ ባሉ ክፍለ ከተማዎች ያዳረሰ ሲሆን  በዚህ ፕሮግራም የተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ...
15/09/2025

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በክረምት ወቅት ሲሰጥ የነበረው ነጻ ህክምና አገልግሎት በመላ አድስ አበባ ባሉ ክፍለ ከተማዎች ያዳረሰ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም የተሳተፋችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ ማድረግ ከነበረብኝ በታችም ተሳትፌ ይህን እውቅና ስለተሰጠኝ ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም ለእንደዚህ አይነት በጎ ተግባር ከዚህ ይበልጥ ብተባበር ደስተኛ ነኝ።
I am truly honored by the recognition of my participation to the Summer Volunteers Medical Services program of AAU titled እሽ ለበጎ. It was a privilege and a responsibility to contribute, and I deeply appreciate the dedication of the volunteers and medical professionals who made such an impact.

ክቡራና ክቡራት ነገ በሚደረገው ደም ልገሳ ፕሮግራም ቤተል አደባባይ አድስ አበባ የምትችሉ ይህን ያነበባችሁየሚመቻቸውን በተለይ ደም ሰጥተው የማያውቁትን ይዛችሁ ኑ።ከጥዋት 3:30 ጀምሮ እንጠ...
06/09/2025

ክቡራና ክቡራት
ነገ በሚደረገው ደም ልገሳ ፕሮግራም
ቤተል አደባባይ አድስ አበባ የምትችሉ ይህን ያነበባችሁ
የሚመቻቸውን በተለይ ደም ሰጥተው የማያውቁትን ይዛችሁ ኑ።
ከጥዋት 3:30 ጀምሮ እንጠብቃችዋለን ።
በመምጣታችሁ ከልብ እናመሰግናለን ።
ያልቻላችሁ ደግሞ መስጠት ይልመድባችሁ።

ነጻ የደም ግፊትና ስኳር ምርመራም በእለቱ ይኖራል።
04/09/2025

ነጻ የደም ግፊትና ስኳር ምርመራም በእለቱ ይኖራል።

30/08/2025

ውድ ተከታታዮቻችን
ዛሬ አስር ሰአት ላይ በ ETV ጤናዎ በቤትዎ ፕሮግራም
ይጠብቁን
ስለ preconception care
ከእርግዝና በፊት ምን ቅድመ ምርመራን በተመለከተ ይሆናል።

28/08/2025
Today I received the attached recognition on behalf of the department Head of Obstetrics and Gynecology ,CHS, Addis Abab...
07/08/2025

Today I received the attached recognition on behalf of the department Head of Obstetrics and Gynecology ,CHS, Addis Ababa University ,
From Bole sub city.
This is a recognition received for the Cervical cancer screening and counseling done for three days by our Residents and other CHS volunteers.
We would like to thank all who are involved in the task.
ዘወትር ስንሰራ በነበረው ስራችን ስላመሰገናችሁን
ለቦሌ ክፍለ ከተማም የላቀ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።
subcity information technology team
Ababa university
of health sciences Addis ababa University

05/07/2025

941 likes, 37 comments. “postmenopausal bleeding needs urgent evaluation”

17/04/2025

የስራ ሰአትና ቦታ ለጠየቃችሁኝ።

https://www.facebook.com/share/p/16UuQj6iT8/
15/04/2025

https://www.facebook.com/share/p/16UuQj6iT8/

የደም ማነስ ለገጠመው ፅንስ ደም መስጠት …

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የእናቶችና ፅንስ ህክምና ክፍል የደም ማነስ ያጋጠመው የአራት ወር ፅንስ ደም እንዲሰጠው በማድረግ የጽንሱን ህይወቱ ማትረፍ መቻሉን በሆስፒታሉ የእናቶችና ጽንስ ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶ/ር ሰዒድ አራጌ ገልጸዋል።

ህፃናት በማህፀን እያሉ እንደማንኛውም ሰው የደም ማነስን ጨምሮ የተለያዩ በሽታዎች ሊያጋጥማቸው እንደሚችልም ተናግረዋል።
የጤና እክል ገጥሟት ወደ ሆስፒታሉ የመጣች አንዲት ነፍሰ-ጡር እናት በተደረገላት ምርመራ ሽሉ የደም ማነስ ችግር እንደገጠመው የተደረሰበት በመሆኑ ተገቢውን ህክምና እንዲያገኝ ጥረት መደረጉን ገልጸዋል።

እናትየው ወደ ሆስፒታሉ ስትመጣ የዘገየች ቢሆንም በተደረገላት ክትትል የጽንሱን ህይወት በመታደግ ውጤታማና አስደሳች ሥራ መሰራቱን አስረድተዋል።

ሾተላይ ወይም አር ኤች ፋክተር በመባል የሚታወቀው ህመም መኖሩ ከታወቀ ህፃናት በማህፀን ሳሉ በሚደረግላቸው የህክምና ክትትል በተሳካ ሁኔታ ማዳን እንደሚቻል መታየቱን አብራርተዋል።

በመሆኑም የህክምና ባለሙያዎች እንዲህ አይነት ችግር ያለበት ፅንስ ካጋጠማቸው ለተጨማሪ ህክምና ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መላክ የሚችሉበት ዕድል መፈጠሩን አስገንዝበዋል።

ይህንን የህክምና ሂደት በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች ማስተማር እንደሚያስፈልግ የገለጹት ዶ/ር ሰዒድ፤ እናቶች ከመጀመሪያ ፅንስ ሁለተኛውና ሶስተኛው ከባድ ሊሆን እንደሚችል ተረድተው በአፋጣኝ ክትትል በማድረግ ወደተቋሙ እንዲመጡ አመላክተዋል።

ዶ/ር ሳምሶን ከሃሊ በበኩላቸው፤ በዘመናዊ አልትራሳውንድ በመታገዝ ህክምናው መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ በማህፀን እያሉ የደም ማነስ ችግር የሚገጥማቸውን ህፃናት ህይወት መታደግ ተችሏል ብለዋል።

እናቶች በእርግዝና ክትትል ወቅት የደም አይነታቸውን በመለየት መድሀኒት በ28ኛው ሳምንት በመውሰድ የችግሩን የመከሰት ዕድል ከ16 በመቶ ወደ 0 ነጥብ 3 በመቶ ገደማ መቀነስ እንደሚቻል ጠቁመዋል።

ፅንስ የሾተላይ ችግር ያለበት መሆኑ ከተረጋገጠ በማህፀን ውስጥ እያለ ለራሱ በተዘጋጀ መርፌ አማካኝነት ደም የመስጠት ስራ እንደሚከናወንም አብራርተዋል።

በእየሩስ ወርቁ

Address

Addis Ababa
7080

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr. Seid Arage posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram