Woba Ari Worda Health Office page 2012

Woba Ari Worda Health Office page 2012 Boyka

የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የአንጀት ጥገኛ ትላትል ክትባት ዘመቻ ኦሬንቴሽን ለጤና ኤክስቴንሽንና ለጤና ባለሙያዎች መስጠቱን አስታወቀ ።ሰኔ 6/2017 ዓ/ም      ቦይካበመድረኩ መክፈቻ ...
13/06/2025

የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የአንጀት ጥገኛ ትላትል ክትባት ዘመቻ ኦሬንቴሽን ለጤና ኤክስቴንሽንና ለጤና ባለሙያዎች መስጠቱን አስታወቀ ።

ሰኔ 6/2017 ዓ/ም
ቦይካ

በመድረኩ መክፈቻ ክቡር የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሕዝቅኤል ጋርታ እንደተናገሩት ከቅርብ ግዜ ወዲህ ጀምሮ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ እና እየተስፋፋ ሕዝብን እያመሰ ካለዉ የወባ በሽታ ወረርሽኝ በተጨማሪ በወቅታዊነት የአንጀት ጥገኛ ትላትል እየተስፋፋ መሆኑን ተከትሎ የክትባት ዘመቻ በሁሉም ቀበሌ ከቀን 9-15/10/2017 ዓ/ም ድረስ እንደሚካሄድ ገልፀዉ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል የየበኩላቸውን ሚና እንድወጡም ጥብቅ መለዕክትም አስተላልፈዋል ።

አቶ ዳንኤል ገበየዉ የጤና ጽ/ቤት አክለዉ በመንግስት በጀት ድጎማ በነፃ የሚታደሉ መድሐኒቶች ዋጋቸዉ ዉድ ከመሆኑ የተነሳ በግለሰብ ደረጃ ለመግዛት የማይቻል መሆኑን በመገንዘብ ህፃናትንና ክትባቱ የሚዳስሳቸዉ የእድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍልን በሙሉ በማስከተብና በመከተብ የዜግነት ግዴታቸዉን እንድወጡ ጥሪ አስተላልፈዋል ።

በስተመጨረሻም ለዘርፉ ሥራ ለባለሙያዎች ስምሪት በመስጠትና ያለፉ ግዜያት ጉዴሌቶችን ለማረም አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ለተግባራዊነቱ አስፈፃሚ ግብረሃይል እና ኮማንድ ፖስት በማቋቋም መድረኩን መቋጨቱን ተናግረዋል ።

የዎባ ኣሪ ወረዳ"ወባን መከላከል ከእኔ ይጀምራል "በሚል መርህ ቃል የወባ በሽታ መከለል ዘመቻ ቅድመ ዝግጅ መርሃግብር ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሄዴ ።ግንቦት 26/2017 ዓ/ም   ...
03/06/2025

የዎባ ኣሪ ወረዳ"ወባን መከላከል ከእኔ ይጀምራል "በሚል መርህ ቃል የወባ በሽታ መከለል ዘመቻ ቅድመ ዝግጅ መርሃግብር ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሄዴ ።

ግንቦት 26/2017 ዓ/ም
ቦይካ

በመድረኩ መክፈቻ ክቡር የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሕዝቅኤል ጋርታ እንደተናገሩት ከቅርብ ወራት ጀምሮ ሕብረተሰባችንን በከፍተኛ ሁኔታ እያመሰና ለበርካቶች የሕወት መቀጠፍ እየሆነ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ ያለዉን የወባ ወረርሽኝ ለመግታትና የአምራቹን ኃይል አቅም በማዳከም ኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ቀዉስ እያስከተለ የሚገኘዉን የወባ በሽታ ለመከላከል ዘላቂዉ መፍትሔ ሕክምና ሳይሆን ከቤት ጀምሮ አካባቢያችንን ፅዱ ማድረግ እንደሆነ በማስገንዘብ የመንግስት ተቋማትንና ባለሙያን ጨምሮ ለአንድ ሳምንትየፅዳት ዘመቻ እንድያካህድና የዘርፉ ባለሙያዎችም የግንዛቤ ሥራዎችን አጠናክረው እንድሠሩ መለዕክት አስተላልፈዋል ።

አክለዉም ይኸንን የወባ በሽታ ወረርሽኝ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ነገ የእያንዳንዳችን በር ሳያንኳኳ የማይቀር እንደሆነ በመገንዘብ የሚንወዳቸዉን ከማጣትና በሕክምና ላልተፈለገ ወጪ ከመዳረግ የተሻለዉ አማራጭ ቤትንና አካባቢን ማፅዳት በእጃችን ያሉ አጎበሮች በማጠብና በመስፋት በአግባቡ በመወጠር መጠቀም መቻል የመጀመሪያ የመከላከል ሥራ በመሆኑ ልተኮርና ልዘወተር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል ።

በተጨማሪም የወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ መምህሩ ጌታቸዉ እንዳሉት የሕዝብን ቁጥር በፍጥነት ከመቀነሱም በጤና መናጋት የማምረት ምጣኔ ላይም አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠረ ያለ ወቅታዊ ወረርሽኝ በመሆኑ ችላ ማለት እንደማያስፈልግና ከጤና ባለሙያዎች የሚተላለፉ ምክረ ሀሶቦችን በመተግበር የራሳችንና የቤተሰቦቻችንን ብሎም የሕብረተሰባችንን ደኅንነት ለመታደግ የበኩላችንን ሚና ለመወጣት ወባን መከላከል ከእኔ ይጀምራል ዘመቻን ተግባራዊ ልናደርግ ያስፈልጋልም ብለዋል ።

በስተመጨረሻም ክቡር አቶ ዳንኤል ገበየዉ የወረዳው የጤና ጽ/ቤት አያይዘዉ ከነገ ጀምሮ በሁሉም በኮማንድ ፖስት ግብረ ሀይል በሁሉም ቀበሌ የፅዳት ዘመቻዉንና የሕክምና አገልግሎት ይዘዉ እንደሚወርዱ አስረድተዉ በዚህም ዘመቻ የመፀዳጃ ቤትና የአካባቢ ንፅሕና ጉድሌት የሚስተዋልባቸዉ ምግብ ቤቶችና ድርጅቶች የግለሰብ መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ እርምጃ እየተወሰደ እንድከድ መወሰኑንም ገልፀዋል።

በዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሁለተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተካሄደግንቦት 22/9/2017 ዓ/ም።።።።። ቦይካ።።።።።።በዎባ  አሪ ወረዳ  ሁለተኛው ዙ...
30/05/2025

በዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሁለተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ተካሄደ
ግንቦት 22/9/2017 ዓ/ም
።።።።። ቦይካ።።።።።።
በዎባ አሪ ወረዳ ሁለተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለትካ ዘረፍ መለሰና የመንግሰት ተጠሪ አቶ ስዩም ዳረጋንሶ በተገኙበት በሻማምር ቀበሌ ጋርዲ ከተማ ላይ ተካሂዷል።

ሁለተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ለ4 ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ የዎባ አሪ ወረዳ አቶ ዳንኤልን ገበየሁ የገለፁ ሲሆን እድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህጻናት ከግንቦት 22-25/2017 ዓ.ም ድረስ በቤት ለቤት በሚደረግ ጉብኝት ስለሚሰጥ ህፃናት ከዚህ በፊት የፖልዮ ክትባት ቢከተቡም ባይከተቡሞ ወላጆች በዘመቻው እንድከተቡ በማድረግ የወላጅነት ሃላፊነታቸዉን እንድወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በሁለተኛዉ ዙር ዘመቻ እንደ ወረዳ 9829 ሕጻናትን መከተብ የሚያስችል ግብዓት ተረክበዉ ዝግጅት ተጠናቅቆ ወደ ተግባር መገባቱንም አንስተዋል።

ከዘመቻዉ በተጨማሪም የፖሊዮ መሰል ኬዝ ለመግታት የቅኝትና አሰሳ ሥራዎችም ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉም ገልፀዋል።

ከአምስት አመት በታች የሆኑ በመደበኛው የክትባት መርሀ-ግብር ተደራሽ ያልሆነ ወይም ጀምረው ያቋረጡ ህፃናትን መለየት እና በጤና ተቋማት ወይም በጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች እንድከተቡ ማድረግ አንዱ የዘመቻዉ አካል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የትንሳኤ በዓል መዳንና መለወጥ ከመስዓዋትነት በቀር እንዲሁ የማይታሰብ መሆኑን የሚያመላክት አስተምህሮት ያለውና ከመጥፎ ወደ በጎ የመለወጥ እሳቤና ተስፋን ማየት እንድንችል ታላቅ አስተምህሮት...
17/04/2025

የትንሳኤ በዓል መዳንና መለወጥ ከመስዓዋትነት በቀር እንዲሁ የማይታሰብ መሆኑን የሚያመላክት አስተምህሮት ያለውና ከመጥፎ ወደ በጎ የመለወጥ እሳቤና ተስፋን ማየት እንድንችል ታላቅ አስተምህሮትን ለሰው ልጆች የሰጠ መንፈሳዊ በዓል ነው፡፡

አቶ ዳንኤል ገበየሁ
የዎባ አሪ ወረዳ ጤ/ጽ/ቤት ኃላፊ

ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም (ዎአወጤ)፤ ቦይካ
አቶ ዳንኤል ገበየሁ የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የስቅለትና የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለዎባ አሪ ወረዳ ህዝብና ለመላው ኢትዮጽያን የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ! አደረሰን! መልዕክት አስተላልፈዋል።

አቶ ዳንኤል ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ፍጹም ፍቅር እና አክብሮት በህማማቱ፣ በስቅለቱ፣ በሞቱ እና በትንሳኤው የገለጸበት ነው።

የትንሳኤ በዓል መዳን፣ ነፃነትና መለወጥ ከመስዓዋትነት በቀር እንዲሁ የማይታሰብ መሆኑን የሚያመላክት ሐይማኖታዊ አስተምህሮት ያለው ፤ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበር በዓል መሆኑን የገለፁት አቶ ዳንኤል ገበየሁ ክህደትና እምነትንም አካቶ ያስተማረ በዓል መሆኑን ተናግረዋል።

የአስቆሮቱ ይሁዳ ወዳጁን መምህሩን በዕለተ ሐሙስ የካደበት፣ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት ምክንያት የሆነበትና ከመከራና ፈተናዎች ሁሉ ከባድ ጭካኔ የተፈፀመበት፤ ስቅለት ለትንሳኤ ምክንያት የሆነበት በዓል መሆኑን የተናገሩት አቶ ዳንኤል ገበየሁ ከመጥፎ ወደ በጎ የመለወጥ እሳቤና ተስፋን ማየት እንድንችል ታላቅ አስተምህሮትን ለሰው ልጆች የሰጠም ነው ብለዋል።

የትንሳኤ በዓል ጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ በመስቀል ላይ እስከሞት ድረስ ራሱን አሳልፎ በመሰጠት ፅኑ ፍቅር ያሳየበት ለበደሉትም ሳይቀር ይቅርታና ምህረትን የሰጠበት፣ ሞትንም ድል ያደረገበት በዓል በመሆኑ እኛም እርስ በርሳችን በመዋደድ፣ በይቅርታና በመረዳዳት ልንኖር ይገባልም ብለዋል ።

ስለሆነም የዘንድሮውን የትንሳዔ በዓል ስናከብር እንደዞንም ሆነ፥ እንደሀገር ባላፉት የለውጥ አመታት የታዩ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን በመውሰድ፤ በቀጣይ ጊዜያት አዲስ ነገር በምንሰራበት ሁኔታ ላይ በማተኮር መሆን አለበት ያሉት አቶ ዳንኤል ገበየሁ ፤ በሚገጥሙን ፈታኝ ሁኔታዎች እጅ ሳንሰጥ ለውጤታማነት የበለጠ ተቀናጅተን በትብብር ልንሰራ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በተለይም መንግስትም የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት መላውን ህዝብ በማሳተፍ በከተማ እና በገጠር ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እያካሄደ ያለው ጥረት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኘ ያለ ስለሆነ፣ የተጀመረው የለውጥና የብልፅግ ጉዞ ሊጠናከር ስለሚገው፣ መላው ህዝብ በየአካባቢው ያሉ ዕድሎች እና ፀጋዎች ሳይመክኑ በሙሉ አቅሙ በመጠቀም፣ የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ እያበረከተ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በመልዕክታቸው አስገንዝበዋል።

በዓሉ የእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤን የምናስታውስበትና የምናከብርበት መስዋዕትነቱን እና ለሰው ልጆች ሁሉ ያለውን ፍፁም ፍቅር የምናሰላስልበት ጊዜ እንደመሆኑ መጠን ይህንን ታላቅ በዓል ስናከብር በአመስጋኝነት ፣ በደግነት የምንችለውን ሁሉ ለተቸገሩ ወገኖች በመለገስና በማጋራት ልናከበረው ይገባል ሲሉም አቶ ዳንኤል ገበየሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

በስተመጨረሻው በዓሉ ለቀበሌ ፣ ለወረዳ፣ ለዞን ፣ክልልሉና ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የብልጽግና እንዲሆን መልካሙን ሁሉ ተመኝተዋል።

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አቶ ዳንኤል ገበየሁ ለዒድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፥ቦይካ ፣መጋቢት 20/2017 (ዎአወጤጽ/ቤት)፦ ለመላዉ የእስልምና  እምነት ...
30/03/2025

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አቶ ዳንኤል ገበየሁ ለዒድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፥

ቦይካ ፣መጋቢት 20/2017 (ዎአወጤጽ/ቤት)፦

ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል ፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ!

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ዳንኤል ገበየሁ በመልዕክታቸው፤ ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በዓሉን ስናከብር ለዘመናት የገነባነውን የሰላም፤ የመቻቻል፣ የመደጋገፍ እና የአንድነት እሴቶች በማጠናከር እና በየተሰማራንበት ዘርፍ ሀገራችንን በሀቀኝነት በማገልገል የድርሻችንን እየተወጣን እንዲሆን አደራ ለማለት እወዳለሁ፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቴን እንገልፃለሁ ።

በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ !! ዛሬ ድንቅና ታርካዊ ቀን ነው ምክንያቱም የስሞክ ማዕከላችን ዛሬ ይፋዊ በተመርቀበት ቀን ማታ  ከምሽቱ 7:00 ስዓት አከባቢ አንድት እናት ህይወት በሰለጠኑት...
23/03/2025

በድጋሜ እንኳን ደስ አላችሁ !! ዛሬ ድንቅና ታርካዊ ቀን ነው ምክንያቱም የስሞክ ማዕከላችን ዛሬ ይፋዊ በተመርቀበት ቀን ማታ ከምሽቱ 7:00 ስዓት አከባቢ አንድት እናት ህይወት በሰለጠኑት ሙያችው በተሳካ ሁኔታ የኦፕራሶን አገልግሎት በመሰጠት ፈጣሪያችውን አመሰግነዋለሁ ። ደግሞም ለዎባ አሪ ህዝብ በሙሉ እንኳን ደስ ብለዋል እኛም ደስ ብሎናል ። የአንድት እናት ከነ ልጇ ህይወት መታደግ ለመጀመሪያ ጊዜ ውብሐመር ጤና ጣቢያ ሥራ መጀመራችን በታላቅ ደስታም ገልፀዋል ። ቀጣይ መረጃዎች በሌላ ፕርግራም ይዘን ብቅ እንላለን መልካም እለት ሰንበት ይሁንላችሁ ።
14/2017
ቦይካ

የዎባ ኣሪ ወረዳ ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆኔ በጀት የተገነባ የእናቶች የቀዶ ጥገና ሕክምና ማስጀመሪያ ማዕከል አስመረቀ ።መጋቢት 13/2017 ዓ/ም(ኣዞመኮመ)የዎባ ኣሪ ወረዳ ከ8 ሚሊዮን ...
23/03/2025

የዎባ ኣሪ ወረዳ ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆኔ በጀት የተገነባ የእናቶች የቀዶ ጥገና ሕክምና ማስጀመሪያ ማዕከል አስመረቀ ።

መጋቢት 13/2017 ዓ/ም(ኣዞመኮመ)

የዎባ ኣሪ ወረዳ ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ በሆኔ በጀት የተገነባ የእናቶች ቀዶ ጥገና ሕክምና ማስጀመሪያ ማዕከል አስመርቋል ።

የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ እንደተናገሩት የወረዳዉ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ አንድ ምዕራፍ ወደ ከፍታና ወደ እድገት እየተቃረበ በመሆኑና የእናቶችና የህፃናት ሞትን ለመቅረፍ በ"RMM" ግብረሰናይ ድርጅት በ MaPHፕሮጀክት የበጀት ድጋፍ የተመራ ዛሬ ለምረቃ በመብቃቱ ለመላዉ የወረዳው ማሕበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት በዞኑ ስም 500 ሺህ ብር ድጋፍ ለማድረግም ቃል ገብተዋል ።

የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሕዝቅኤል ጋርታም አክለዉ ለዘመናት በእናቶችና ህፃናት ሞት የማይደርቅ የእንባ ጎርፍ ለማፍሰስ የተገደድንበትን ጊዜ ዛሬ ማብቅያ ላይ በመድረሱ በወረዳዉ ሕብረተሰብ ስም የRMM ድርጅት እና የMaPH ፕሮጀክት እንዲሁም የዞኑን መንግስት ከልብ አመስግነዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የዞን አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት የወረዳ አመራሮች የጤና ባለሙያዎችና የቦይካ ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

Woba Aari Woreda Health Office page:የ"MaPH~SOAZ" የተሰኘ ድርጅት በዎባ ኣሪ ወረዳ የዉብሐመር ጤና ጣቢያ የ"ሲሞክ" ማዕከል ማስጀመሪያ የግብዓት ድጋፍ አበረከተ።የ...
26/02/2025

Woba Aari Woreda Health Office page:
የ"MaPH~SOAZ" የተሰኘ ድርጅት በዎባ ኣሪ ወረዳ የዉብሐመር ጤና ጣቢያ የ"ሲሞክ" ማዕከል ማስጀመሪያ የግብዓት ድጋፍ አበረከተ።

የካቲት 19/2017 ዓ/ም(ዎባ ኣሪ)
ቦይካ
በዎባ ኣሪ ወረዳ በቅርብ ቀን ልጀመር ያለዉ የመለስተኛ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ ማሽኖችና መሣሪያዎች በNLM ድርጅት "MaPH~SOAZ"በተሰኘ ፕሮጀክት ድጋፍ ለዉብሐመር ጤና ጣቢያ መበርከቱንና ቀድመዉ የገቡ ማሽኖች ጥገና ሥራዎች መጀመሩን የወረዳው የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ገበየሁ አስታዉቀዋል ።

እንደ አቶ ዳንኤል ገለፃ ይኸ ድርጅት በዋናነት የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ቁጥር መቀነስ ላይ እንደምሰራ እና በዚህም ፅንሰ ሀሳብ መነሻነት እንደ ዎባ ኣሪ ወረዳ በሆስፒታል ደረጃ ብቻ የሚሰጡ አገልግሎቶች የሚያስፈልጓቸው እናቶችና በርካታ ህፃናት የታጡ እንደሆኔና ይኸንንም ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ የመለስተኛ ቀዶ ጥገና ለማስጀመር ታቅዶ እየተሠራ መቆየቱን ገልፀዉ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ መደረሱንም ነዉ የተናገሩት ።

በተጨማሪም ይኸን ግብረ ሰናይ ድርጅት አመስግነው ለዘርፉ የተመለመሉ ባለሙያዎችን በተለያዩ የሙያ መስኮች በራሱ ወጪ ድርጅቱ ማሰልጠኑንና ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ገንዘብ ፈሰስ በማድረግ ደረጃዉን የጠበቀ ተጨማሪ የእርጉዝ እናቶች ማቆያ ግንባታ ማስጀመሩን ገልፀዉ በህክምናዉ ዘርፍ የመብራት መቆራረጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አንድ ትልቅ ጀኔሬተርም ግዢ ፈፅሞ ማስረከቡንም አስረድተዋል ። ከምንሞ በላይ ዛሬ ለውብሐመር ጤና ጣቢያ የእናቶች ማዋላጀ አልጋ ሁለት በስጦታ መልክ መስጠታቸው ለማመሰገን ቃላቶች እያጡሩኝ ነው እናመሰግናል ።

የዉብሐመር ጤና ጣቢያ ኃላፊ የሆኑት አቶ መላኩ ዶይስ እንደተናገሩት በጤና ጣቢያዉ የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ ምቹና ቀልጣፋ ስረዓት ለመዘርጋት ብሎም አሠራሮችን ለማዘመን ተስፋ ሰጪ የሚባል እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዉ ከተቋሙም ሆኔ ከወረዳው መንግስት ጎን ሁሉም የማሕበረሰብ ክፍል መቆም ከቻለ ከእናቶች ዓይን እምባ የምታበስበት ቀንም ሆነ የህፃናት ሞት ተረት የሚሆንበት ቀን በቅርቡ ብስራት እንደሚያገኝም አስረድተው ለዚህ ሁሉ ስኬት ዋጋ የከፈሉ የ"NLM" ፕሮጀክት አስተባባሪዎችን በወረዳዉ ማሕበረሰብ ስም አመስግነዋቸዋል ።

በስተመጨረሻ የጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ዳንኤል ገበየሁ እንደተናገረው ዛሬ ቀኑ ደስ የሚል ነው ድርብ ደስታ ነው ማመስገን ያለብን ሁለት ነገሮችም አሉን እነሱም በወንዶችና በሴቶች መሃከል የተደረገው ድጋፍ ቢኖር ፋኢ ቀበሌና አይዳምር ከተማ ለጤና ጣቢያ አጥር ዙሩያ የሚሆን ቃርካ በግምት 45,400 ብር በስጦታ መልክ አበርክተዋል እናመሰግናለን ።ሌላኛው የዘመር የሴቶችና አይዳምር ከተማ በ1ለ10 አደረጃጀት ማቆያ ላሉት እናቶች አቅም በፈቀደው ልክ ለእናቶች ቀለብ አሰረከበዋል በአይነት ገንበዝ፣ በቆሎ፣ እንጭት ፣ጎደሬ ፣ ጎመንና የተለያዬ የቡና ቅመምቅመምን በግምት ወደ 26,000 ብር የሚሆን አብርክቷል በወረዳው ስም ከልብ እናመሰግናል ። ሌሎችም ቀበሌያት ከነገ ጀምሮ ቢዚህ ልክ በተደራጁ መልክ ጤና ጣቢያን እንዲትጎበኙ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

ከምንም በላይ ደስታች ዛሬ ባለ3 ፌዝ ቆጣሪ መቅረቱ የድስታችን ወደር የለንም ምክንያቱ ፈጣሪ የወረዳውን ችግር በማየት በአንድ ባለሙያ ሆኖ ችግራች አቅልሏል ባለው ቆጣሪ ሁሉም ማሽኖችናን ሌሎችም እንድሰራ አድሮጎናል ዛሬም የመጣው ጀኔቴር ሁሉንም ማንቀሳቀሱ ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላቸው የወረዳችን ህዝብ ሆይ የላውንቺ ቀንም በአጭር ቀን ውስጥ ስለሆነ የበኩላችን አስተዋጽኦ እናድርግ ።

የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በዎባ አሪ ወረዳ  በይፋ ተጀመረ። የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ች እድሜያችው 5 ዓመት በታች  ለሆኑ ህጻናት ከየካቲት 14-17/2017 ዓ....
21/02/2025

የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በዎባ አሪ ወረዳ በይፋ ተጀመረ።
የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ች እድሜያችው 5 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት ከየካቲት 14-17/2017 ዓ.ም ድረስ በወረዳችን ውስጥ በሁሉም ቀበሌያት ቤት ለቤት የማሰጀመሪያ ፕሮግራም በድራመር ቀበሌ ላይ ላውንቺንግ ተካሄዴ ፡፡
ቦይካ 14/6/2017 ዓ/ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን በዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ገበየሁ ፣ የዎባ አሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህዝቅኤል ጋርታ ፣የዎባ አሪ ወረዳ የብልግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፍ የመንግስት ተጠሪ አቶ መምህሩ ጌታቸው እና ሌሎች አሰተባባር ኮሜቴና የጽ/ቤት ማናጅሜንት የጤና ጣቢያ ኃላፍ በተገኙበት ዘመቻው በድራመር ቀበሌ በይፋ አስጀምረዋል።

በወረዳው ከ9,849 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህጻናት የፖሊዮ ክትባት ለማድረስ ታቅዶ ተከታታይ ቀናቶች ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ገበየሁ ፤ በቂ ዝግጅት በመደረጉ የተሸለ ውጤት እንጠብቃለን ብለዋል።

የዎባ አሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህዝቅኤል ጋርታ በኩላቸው፤ ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ህጻናት እየተሰጠ ላለው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የወረዳ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለው ክትባቱ በትኩረት መሰጠት እንዳለበት አመላክተዋል።

አንድም ህጻን ሳይከተብ መቅረት የለበትም ያሉት የፖርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መምህሩ ጌታቸው ለዚህም ነው ዘመቻው ቤት ለቤት እየተደረገ ያለው ብለዋል።

ከፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ጎን ለጎን የህጻናት የምግብ እጥረት፣ የነፍሰ ጡር እናቶች፣ የሽንት ቤት ኦድትና የመለየት ፣ የቆልማማ እግር እና ፖሊዮ የተገኘባቸውም ካሉ የመለየት ስራ የሚሠራ መሆኑን አሰረድቷል

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ሌሎች የወረዳውና የቀበሌ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ዘመቻው ከ14/06/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
"መከተብ የህፃናት መብት ማስከተብ ደግሞ የወላጆች ሃላፊነት ነው”

ዘጋቢ: ከዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ከ4ት ወረዳዎች እና ከ2 ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤቶች ከእያንዳንዱ 5 ተሳታፊዎች በተገኙበት የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ እና ለሎች በቅንጅት የ...
15/02/2025

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ከ4ት ወረዳዎች እና ከ2 ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤቶች ከእያንዳንዱ 5 ተሳታፊዎች በተገኙበት የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ እና ለሎች በቅንጅት የሚሰሩ ተግባራት ኦሬንተሽን በመስጠት ላይ ይገኛል ።
የካቲት 8/2017 ዓ.ም(ኣዞጤመ_ጂንካ)

በቴሌግራም ገጻችን ይከታተሉን
https://t.me/+9ChLwsFQYos1N2E0

የጥርስና የድድ ህመም መፍትሔዎች የድድ መድማት ዕድሜና ፆታ ሳይለይ በበርካታ ሰዎች ዘንድ የሚከሰት ሲሆን ይህ ችግር ብዙውን ጊዜ የሚከሰተው ከጥርስ ጋር  የተያያዘው ነርቭ ሲቆጣ፣ በድድ በሽ...
23/01/2025

የጥርስና የድድ ህመም መፍትሔዎች

የድድ መድማት ዕድሜና ፆታ ሳይለይ በበርካታ ሰዎች ዘንድ የሚከሰት ሲሆን ይህ ችግር ብዙውን ጊዜ የሚከሰተው ከጥርስ ጋር የተያያዘው ነርቭ ሲቆጣ፣ በድድ በሽታ፣ በጥርስ ቆሻሻ፣ በጥርስ መበስበስ፣ በድንገተኛ አደጋና በጥርስ መነቀል ምክንያት ነው፡፡

የጥርስ መነቀል የጥርስ መሸረፍን የሚያጠቃልል ነው፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት ብዙውን ጊዜ ለጥርስ ወይም ለድድ መድማት እንደ ምክንያት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

አንዳንዴ ከጥርስና ድድ አካባቢ ውጭ የሚከሰት ህመም ወደ አፍም ውስጥ በመስፋፋት የድድ ወይም የጥርስ በሽታን ሊያስከትል ይችላል፡፡

ይህ ብዙውን ጊዜ በመንጋጋ መገጣጠሚያ አካባቢ ችግር ሲፈጠር ሲሆን ይህም የመንጋጋ መገጣጠሚያ በህክምናው አጠራር ቴምፖሮ ማንዲቡለር ጆይንት ተብሎ የሚጠራ ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ የጆሮ ህመም አንዳንዴም የልብ ችግርና የጥርስ ውስጥ ህመምን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ሊከሰት የሚችልን የጥርስና የድድ ህመም በቀላሉ መከላከል ይቻላል፡፡

የጥርስ ህመም ፐልፕ በተሰኘው የጥርስ ማዕከላዊ ቦታ በሚገኘው የአካል እብጠት ምክንያት የሚከሰት ነው፡፡

ፐልፕ ለህመም ተጋላጭ የሆነ የነርቭ ጫፍ የሚገኝበት አካል ነው፡፡ የፐልፕ ውስጥ እብጠት በጥርስ ጎድጓዳ ቦታዎች ውስጥ ሊከሰት ይችላል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ጉዳትና ኢንፌክሽን የፐልፕ እብጠት ሊያስከትል ይችላል፡፡

የጥርስ እና የድድ ህመም ምልክቶች
የጥርስና የድድ ህመሞች ተመሳሳይ ምልክቶች አሏቸው፡፡

አንድ ሰው በጣም ቀዝቃዛ ወይም በጣም የሞቀ ምግብ ወይም መጠጥ ሲወስድ ህመም ሊሰማው ይችላል፡፡ ህመሙ በጣም ሃይለኛና ከ15 ሴኮንድ በላይ የሚቆይ ከሆነ ይህ ከባድ የጥርስ ወይም የድድ ህመም ምልክት ሆኖ ሊቆጠር ይችላል፡፡

በጥርስ ውስጥ ያለው ህመም እየሰፋ ከሄደ ህመሙ በጉንጭ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ የጥርስ እብጠት የጆሮና የመንጋጋ ህመም ሊያስከትል ይችላል።

ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ምልክቶች አንድ ሰው ለጥርስ ወይም ለድድ ህመም ሊጋለጥ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፡፡

ስናኝክ ህመም መታየት፣ ለቀዝቃዛ ወይም ሙቅ ነገሮች በቀላሉ ለህመም መጋለጥ፣ በጥርስ አካባቢ ወይም የድድ መድማት በጥርስ ዙሪያ፣ በመንጋጋና በጉንጭ ውስጥ እብጠት መከሰት ድንገተኛ ጉዳት ወይም ህመም እና በየጊዜው የሚታዩ የጥርስና የድድ ህመምና መቅላት የጥርስ ህመም ምልክቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

የጥርስ ህመም ከሌሎች በፊት ወይም በአፍ ውስጥ ከሚከሰቱ ህመሞች ተለይተው መታየት ይኖርባቸዋል፡፡

በተለይም ከአፍንጫ፣ ከጆሮ ወይም ከጉሮሮ እንዲሁም ከመንጋጋ መገጣጠሚያ ህመም ጋር የማይገናኙ መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል፡፡

አንዳንድ ሰዎች የመንጋጋ በሽታን ከጥርስ በሽታ ጋር አዛምደው ይገልፁታል፡፡ መልካም አመለካከትም አይደለም።ይለያያልና
ዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት
❤❤ቦይካ❤❤❤

𝐕𝐢𝐬𝐢𝐭  ❤❤❤❤❤❤❤❤ ?𝙑𝙄𝙎𝙄𝙏 𝙀𝙏𝙃𝙄𝙊𝙋𝙄𝘼𝑽𝒊𝒔𝒊𝒕 𝒐𝒖𝒓  #𝑱𝒊𝒏𝒌𝒂 𝑪𝒐𝒓𝒓𝒊𝒅𝒐𝒓 𝒅𝒆𝒗𝒆𝒍𝒐𝒑𝒎𝒆𝒏𝒕 𝒑𝒓𝒐𝒋𝒆𝒄𝒕, 𝒘𝒉𝒊𝒄𝒉 𝒊𝒔 𝒕𝒉𝒆 𝒄𝒂𝒑𝒊𝒕𝒂𝒍 𝒐𝒇 𝑨𝒓𝒊 𝒁𝒐𝒏𝒆 𝒊𝒏 𝒕𝒉𝒆 𝑺...
22/01/2025

𝐕𝐢𝐬𝐢𝐭 ❤❤❤❤❤❤❤❤ ?
𝙑𝙄𝙎𝙄𝙏 𝙀𝙏𝙃𝙄𝙊𝙋𝙄𝘼
𝑽𝒊𝒔𝒊𝒕 𝒐𝒖𝒓 #𝑱𝒊𝒏𝒌𝒂 𝑪𝒐𝒓𝒓𝒊𝒅𝒐𝒓 𝒅𝒆𝒗𝒆𝒍𝒐𝒑𝒎𝒆𝒏𝒕 𝒑𝒓𝒐𝒋𝒆𝒄𝒕, 𝒘𝒉𝒊𝒄𝒉 𝒊𝒔 𝒕𝒉𝒆 𝒄𝒂𝒑𝒊𝒕𝒂𝒍 𝒐𝒇 𝑨𝒓𝒊 𝒁𝒐𝒏𝒆 𝒊𝒏 𝒕𝒉𝒆 𝑺𝒐𝒖𝒕𝒉𝒆𝒓𝒏 𝑬𝒕𝒉𝒊𝒐𝒑𝒊𝒂𝒏 𝑹𝒆𝒈𝒊𝒐𝒏.
𝙳𝚒𝚜𝚌𝚘𝚟𝚎𝚛 𝚃𝚑𝚎 𝙱𝚎𝚊𝚞𝚝𝚒𝚏𝚞𝚕 𝚗𝚊𝚝𝚞𝚛𝚎 𝚊𝚗𝚍 𝚌𝚞𝚕𝚝𝚞𝚛𝚎.
𝙨𝙝𝙖𝙧𝙚 𝙪𝙣𝙛𝙤𝙧𝙜𝙚𝙩𝙩𝙖𝙗𝙡𝙚 𝙢𝙤𝙢𝙚𝙣𝙩𝙨.. 𝙬𝙞𝙩𝙝 your 𝙛𝙧𝙞𝙚𝙣𝙙𝙨.
𝕐𝕠𝕦 𝕨𝕚𝕝𝕝 𝕖𝕟𝕛𝕠𝕪 𝕥𝕙𝕖 𝕨𝕒𝕣𝕞 𝕨𝕖𝕝𝕔𝕠𝕞𝕚𝕟𝕘 𝕠𝕗 Jinka
aari zone Jinka Ethiopia

Address

SNNPRG Jinka
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woba Ari Worda Health Office page 2012 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram