26/02/2025
Woba Aari Woreda Health Office page:
የ"MaPH~SOAZ" የተሰኘ ድርጅት በዎባ ኣሪ ወረዳ የዉብሐመር ጤና ጣቢያ የ"ሲሞክ" ማዕከል ማስጀመሪያ የግብዓት ድጋፍ አበረከተ።
የካቲት 19/2017 ዓ/ም(ዎባ ኣሪ)
ቦይካ
በዎባ ኣሪ ወረዳ በቅርብ ቀን ልጀመር ያለዉ የመለስተኛ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ ማሽኖችና መሣሪያዎች በNLM ድርጅት "MaPH~SOAZ"በተሰኘ ፕሮጀክት ድጋፍ ለዉብሐመር ጤና ጣቢያ መበርከቱንና ቀድመዉ የገቡ ማሽኖች ጥገና ሥራዎች መጀመሩን የወረዳው የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ገበየሁ አስታዉቀዋል ።
እንደ አቶ ዳንኤል ገለፃ ይኸ ድርጅት በዋናነት የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ቁጥር መቀነስ ላይ እንደምሰራ እና በዚህም ፅንሰ ሀሳብ መነሻነት እንደ ዎባ ኣሪ ወረዳ በሆስፒታል ደረጃ ብቻ የሚሰጡ አገልግሎቶች የሚያስፈልጓቸው እናቶችና በርካታ ህፃናት የታጡ እንደሆኔና ይኸንንም ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ የመለስተኛ ቀዶ ጥገና ለማስጀመር ታቅዶ እየተሠራ መቆየቱን ገልፀዉ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ መደረሱንም ነዉ የተናገሩት ።
በተጨማሪም ይኸን ግብረ ሰናይ ድርጅት አመስግነው ለዘርፉ የተመለመሉ ባለሙያዎችን በተለያዩ የሙያ መስኮች በራሱ ወጪ ድርጅቱ ማሰልጠኑንና ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ገንዘብ ፈሰስ በማድረግ ደረጃዉን የጠበቀ ተጨማሪ የእርጉዝ እናቶች ማቆያ ግንባታ ማስጀመሩን ገልፀዉ በህክምናዉ ዘርፍ የመብራት መቆራረጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አንድ ትልቅ ጀኔሬተርም ግዢ ፈፅሞ ማስረከቡንም አስረድተዋል ። ከምንሞ በላይ ዛሬ ለውብሐመር ጤና ጣቢያ የእናቶች ማዋላጀ አልጋ ሁለት በስጦታ መልክ መስጠታቸው ለማመሰገን ቃላቶች እያጡሩኝ ነው እናመሰግናል ።
የዉብሐመር ጤና ጣቢያ ኃላፊ የሆኑት አቶ መላኩ ዶይስ እንደተናገሩት በጤና ጣቢያዉ የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ ምቹና ቀልጣፋ ስረዓት ለመዘርጋት ብሎም አሠራሮችን ለማዘመን ተስፋ ሰጪ የሚባል እንቅስቃሴ እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዉ ከተቋሙም ሆኔ ከወረዳው መንግስት ጎን ሁሉም የማሕበረሰብ ክፍል መቆም ከቻለ ከእናቶች ዓይን እምባ የምታበስበት ቀንም ሆነ የህፃናት ሞት ተረት የሚሆንበት ቀን በቅርቡ ብስራት እንደሚያገኝም አስረድተው ለዚህ ሁሉ ስኬት ዋጋ የከፈሉ የ"NLM" ፕሮጀክት አስተባባሪዎችን በወረዳዉ ማሕበረሰብ ስም አመስግነዋቸዋል ።
በስተመጨረሻ የጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ዳንኤል ገበየሁ እንደተናገረው ዛሬ ቀኑ ደስ የሚል ነው ድርብ ደስታ ነው ማመስገን ያለብን ሁለት ነገሮችም አሉን እነሱም በወንዶችና በሴቶች መሃከል የተደረገው ድጋፍ ቢኖር ፋኢ ቀበሌና አይዳምር ከተማ ለጤና ጣቢያ አጥር ዙሩያ የሚሆን ቃርካ በግምት 45,400 ብር በስጦታ መልክ አበርክተዋል እናመሰግናለን ።ሌላኛው የዘመር የሴቶችና አይዳምር ከተማ በ1ለ10 አደረጃጀት ማቆያ ላሉት እናቶች አቅም በፈቀደው ልክ ለእናቶች ቀለብ አሰረከበዋል በአይነት ገንበዝ፣ በቆሎ፣ እንጭት ፣ጎደሬ ፣ ጎመንና የተለያዬ የቡና ቅመምቅመምን በግምት ወደ 26,000 ብር የሚሆን አብርክቷል በወረዳው ስም ከልብ እናመሰግናል ። ሌሎችም ቀበሌያት ከነገ ጀምሮ ቢዚህ ልክ በተደራጁ መልክ ጤና ጣቢያን እንዲትጎበኙ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።
ከምንም በላይ ደስታች ዛሬ ባለ3 ፌዝ ቆጣሪ መቅረቱ የድስታችን ወደር የለንም ምክንያቱ ፈጣሪ የወረዳውን ችግር በማየት በአንድ ባለሙያ ሆኖ ችግራች አቅልሏል ባለው ቆጣሪ ሁሉም ማሽኖችናን ሌሎችም እንድሰራ አድሮጎናል ዛሬም የመጣው ጀኔቴር ሁሉንም ማንቀሳቀሱ ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላቸው የወረዳችን ህዝብ ሆይ የላውንቺ ቀንም በአጭር ቀን ውስጥ ስለሆነ የበኩላችን አስተዋጽኦ እናድርግ ።