Dr Mekides Daba Minister of Health, Ethiopia

Dr Mekides Daba Minister of Health, Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dr Mekides Daba Minister of Health, Ethiopia, Medical and health, Addis Ababa.

15/04/2024

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__________

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Medicine, Nursing, Health Officer, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Technology, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatrics Nursing እና Emergency & Critical Care Nursing ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በግንቦት 2016 ዓ.ም የብቃት ምዘና ፈተና ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡
ስለሆነም አዲስም ሆነ ነባር፣ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የኦንላይን ምዝገባው ከሚያዚያ 7/2016 እስከ ሚያዚያ 21/2016 ዓ.ም ብቻ የሚቆይና ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፦

- የግል ትምህርት ተቋማት ተመዛኞች ከምዝገባ በፊት የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን (ETA) Authenticate ማስደረግና ስማችሁን ከባለስልጣኑ ወደ ጤና ሚኒስቴር ማስላክ ይጠበቅባችኋል፡፡

- ከጥር 1/2015 ዓ.ም በኋላ የተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የትምህርት ሚኒስቴር መውጫ ፈተና(Exit Exam) ማለፍ ይጠበቅባችኋል፡፡

- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

11/03/2024
"ማህበራዊ የባህሪ ለውጥ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል 3ኛው ሀገር አቀፍ የማህበራዊና የባህሪ ለውጥ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡-------------------------ጤና...
28/02/2024

"ማህበራዊ የባህሪ ለውጥ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል 3ኛው ሀገር አቀፍ የማህበራዊና የባህሪ ለውጥ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

-------------------------

ጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ ጤና ትምህርትና ፕሮሞሽን ባለሙያዎች ማህበር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሶስተኛውን ሃገር አቀፍ የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ጉባዔ “የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ተግባራት ለዘላቂ የጤና ልማት” በሚል መሪ ቃል ከ13 አለም አቀፍ አገራት ከመጡ የዘርፉ ባለሙያዎችን ጨምሮ 400 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአዲስ አባባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ አገራዊ ፋይዳው ከፍተኛ በሆነው ወሳኝ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በምዕተ ዓመቱ ግብ ላይ በተለያዩ የጤና ዘርፎች ከፍተኛ መሻሻሎችን አስመዝግባለች። እነዚህ ስኬቶች ሊገኙ የቻሉት አንድም የማህበራዊ እና የባህርይ ለውጥ በመተግበሩ ነው፡፡ የማህበራዊ እና የባህርይ ለውጥ ፕሮግራም፣ በሽታን ለመከላከል፣ በአጠቃላይ ለጤና ስርዓቱ ውጤታማ ለማድረግ ቁልፍ መሳሪያ ነው። እንዲሁም ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት፣ በሁሉም መርሃ ግብሮች ውስጥ አስፈላጊ ስትራቴጂ ነው። የጤና ሚኒስቴር የማህበራዊ ለውጥ ፕሮግራምን ተግባራዊ በማድረግ በጤናው ዘርፍ እምርታ ለማስመዝገብ ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል በጤናው ዘርፍ እንደ ሀገር የማህበራዊ እና የባህሪ ለውጥ ለማምጣት፣ የጤና ሚኒስቴር የአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱን የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትሯ፣ የህብረተሰባችንን የባህሪ ለውጥ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በተለያዩ ቋንቋዎች፣ በልዩ ልዩ መድረኮች፣ በስልክ መስመሮች፣ እና በሳምንታዊ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ለማህበራዊ የባህሪ ለውጥ ስኬት፣ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የአለም አቀፍ የጆንስ ሆፕኪንስ ሴንተር ፎር ኮሙኒኬሽን ፕሮግራሞች ላይ ከፍተኛ አበርክቶ የነበራቸውን ዶክተር ቤንጃሚን ሎዛሬ ህልፈትን አስመልክቶ የህሊና ፀሎት ያስደረጉት በUSAID የማህበራዊ እና የባህርይ ለውጥ ኃላፊ ዶክተር ጉዳ አለማየሁ፣ ጤናማ ሰዎች ውጤታማ ናቸው ብለን እናምናለን፤ ጠንክረው ከሰሩ ለሀገር ዘላቂ ልማት አስተዋፅዖ ያደርጋሉ፤ ይህ ሊሳካ የሚችለው ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች እና ማህበረሰቦች የራሳቸውን ጤና እንዲያመርቱ ያልተቋረጠ የማስተማር ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎች ልማድ ሆነው ሲተገበሩ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጤና ትምህርትና ፕሮሞሽን ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት፣ ዶክተር እሸቱ ግርማ በበኩላቸው የጉባዔው ዋና ዓላማ በማህበራዊ የባህሪ ለውጦች ላይ ያሉ ስራዎች፣ ልምዶችን መቀመር እርስበርስ መማማር ነው ብለዋል፡፡

ዶክተር እሸቱ አክለውም ስለጤናው የሚጠይቅና የሚያውቅ ማህበረሰብ ለመፍጠር የማህበራዊ እና የባህርይ ለውጥ ተግባቦት ትልቅ ሚና አለው ብለው፣ አገራችን ኢትዮጵያ ኤች አይቪን ጨምሮ አለም አቀፍ ወረርሽኝ የነበረውን የCOVID-19 ለመከላከል የማህበራዊ እና የባህርይ ለውጥን ተጠቅመንበት ያመጣነው ውጤት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ጤና ኮሚዩኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ተገኔ ረጋሳ ይኼ ጉባዔ በአገራችን ለሶስተኛ ጊዜ እየተካሄደ መሆኑን፣ እ.ኤ.አ. በ2016 አዲስ አበባ ላይ የመጀመሪያው አለም አቀፍ ጉባኤ ተካሂዶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ጉባኤዎቹ ትልልቅ የማህበራዊ እና የባህሪ ለውጥ ጉዳዮች የተነሱባቸው መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው አስቀድሞ በሽታ መከላከል ላይ እንደመሆኑ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr Mekides Daba Minister of Health, Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram