Ethiopian health today

Ethiopian health today Ethiopian Health Today is for awareness creation: health, education,foreign relation,Aid organizations,and professional development.

ሀምሊን ኢትዮጵያልዩ ሽልማት************ከ66 ዓመታት በፊት በጽንስና ማህፀን ሐኪምነት ለማገልገልና የሚድ ዋይፈሪ ት/ቤት ለመክፈት ለሶስት አመት በኮንትራት ወደ ኢትዮጵያ በመጡት በዶ/...
25/10/2025

ሀምሊን ኢትዮጵያ
ልዩ ሽልማት

************

ከ66 ዓመታት በፊት በጽንስና ማህፀን ሐኪምነት ለማገልገልና የሚድ ዋይፈሪ ት/ቤት ለመክፈት ለሶስት አመት በኮንትራት ወደ ኢትዮጵያ በመጡት በዶ/ር ካትሪን እና በዶ/ር ሬጂናልድ ሃምሊን ነበር የተመሰረተው፡፡

ስራ የጀመሩት በልዕልት ፀሐይ መታሰቢያ ሆስፒታል/ የአሁኑ ጦር ሃይሎች ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል/ ሲሆን ከፊስቱላ የፀዳች ኢትዮጵያን ራዕይ ለማሳካት በፊስቱላ ጉዳት የደረሰባቸውን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ለማከም የሚሰራ አለም አቀፍ ድርጅት ነው፡፡

ከስድስት አስርት አመታት በላይ ፊስቱላ ያለባቸው ከ70,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ህይወት የሚቀይር የቀዶ ጥገና በማድረግ፣ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን በመስጠት ሴቶች ራሳቸውን እንዲችሉ በማቋቋምና ከ270 በላይ ሚድዋይፎችን በዲግሪ እና በማስተርስ ደረጃ አሰልጥኖ ወደ መጡበት የገጠር ክፍል መልሶ በማሰማራት የእናቶች ሞት በመቀነስ እና በወሊድ ወቅት ችግሮች እንዳፈጠሩ በመከላከል ከተገላይነት፣ ከሀፍረት እና ከሀዘን ህይወት እንዲወጡ እና ወደ ማህበረሰባቸው እንዲመለሱ አግዟል አሁንም እየሰራ ይገኛል፡፡

ዶ/ር ካትሪን እና ዶ/ር ሬጂናልድ ሃምሊን በሀገር ውስጥ የነበሩ የተለያዩ ተግዳሮቶች ሳይገድቧቸው አስከ እስከህልፈታቸው ድረስ አገልገለዋል፡፡ ላበረከቷቸው አስተዋፅኦዎችም ለኖቤል ሽልማት መታጨትን ጨምሮ በርካታ ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ ዕውቅናዎችን እና የኢትዮጵያ የክብር ዜግነትንም አግኝተዋል፡፡

ሀምሊን ኢትዮጵያ፤ በጤናው ዘርፍ ላበረከተው የላቀ አገልግሎት ጤና ሚኒስቴር በ27ኛው የጤና ዘርፍ አመታዊ ጉባኤው ልዩ ተሸላሚ ሆኖ ተመርጧል፡፡

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

🔬MESSAGE FROM THE PATHOLOGY DESK📢Here’s a quick look at the nuts and bolts of cytology reporting — what those terms real...
25/10/2025

🔬MESSAGE FROM THE PATHOLOGY DESK📢

Here’s a quick look at the nuts and bolts of cytology reporting — what those terms really mean in your patient’s report.

From Bethesda to Paris!

Dear Colleagues (in every scope of Clinical practice), Cytopathology reporting has been standardized globally to make communication between clinicians and pathologists crystal clear 🧠💬.

Here’s a quick overview of the official reporting systems we use — so our reports speak a universal language:

Here’s a quick refresher on the official reporting systems across organs 👇

🔬 Organ – Reporting System – Year

1️⃣ Cervix: The Bethesda System for Reporting Cervical cytology (TBS, 2015)

➡️ Categories like ASC-US, LSIL, HSIL guide HPV related management and follow-up.

2️⃣ Thyroid: The Bethesda System for Thyroid Cytopathology, Second edition (TBSRTC, 2023)

➡️ 6-tiered categories with defined ROM (Risk of Malignancy) & Management — from “Nondiagnostic” to “Malignant”.

➡️ Each category carries a defined risk of malignancy (ROM) → assists in deciding surgery vs. observation.

3️⃣ Salivary Gland: The Milan System (2018)

➡️ Brings clarity to categories like SUMP (salivary gland of unknown malignantl potential) And AUS (Atypia of Undetermined significance)

➡️ Stratifies neoplasms and indeterminate cases → helps plan excision or further testing.

4️⃣ Breast: The Yokohama System (2020)

➡️5-tiered categories linking cytology to clinical management.

5️⃣ Respiratory Tract: The International System for Lung Cytopathology (ISL, 2020)

➡️Applies to sputum, BAL, and FNAC specimens → supports multidisciplinary diagnosis.

6️⃣ Serous Effusions: The International System for Serous fluid cytopathology (TIS, 2020)

➡️ Standardizes reporting of pleural/peritoneal/pericardial fluids bringing global uniformity to effusion cytology.

7️⃣ Pancreaticobiliary: The Papanicolaou Society System (2015)

➡️ Helps correlate cytology with imaging/endoscopy for cystic & solid lesions.

8️⃣ Lymph Node: The Sydney System (2020)

➡️ Improves consistency in FNAC reports for suspected lymphoma or metastasis.

9️⃣ (And in the practice of Clinical Pathology) Urinary Tract: The Paris System (2022)

➡️ Which is mainly focused on detecting High-Grade Urothelial Carcinoma (HGUC) & reduces over-calling.

💡Why it matters:
These systems ensure that when you read “AUS,” “SUSPICIOUS,” or “MALIGNANT,” you can interpret it consistently, regardless of who signed out the case.

🧠 Keep this list handy for clinical discussions, CME sessions, or teaching rounds!



📩 For any pathology-related queries or if you’d like access to reference books or resources, feel free to email me. (theddo04@gmail.com)

Dr Tewodros Wubshet Desta, Assistant professor
Dire Dawa University, Department of Pathology
Dire Dawa

Telegram: t.me/HakimEthio

‎የጣና ፎረም ዝግጁነታችን ሁሉን አቀፍ ነበር። ‎‎የጤና ባለሙያዎቻችን እንግዶቻችን ከአየር እንደወረዱና ሲመለሱ የጤና ችግር እንዳይገጥማቸው፣ በስብሰባ ቦታውም እንዲሁ የስፔሻሊስት ሀኪሞቻችን...
25/10/2025

‎የጣና ፎረም ዝግጁነታችን ሁሉን አቀፍ ነበር።

‎የጤና ባለሙያዎቻችን እንግዶቻችን ከአየር እንደወረዱና ሲመለሱ የጤና ችግር እንዳይገጥማቸው፣ በስብሰባ ቦታውም እንዲሁ የስፔሻሊስት ሀኪሞቻችንን የያዘ ቡድን ተቋቁሞ በተጠንቀቅ ዝግጁ ሆነው ጠብቀዋል።

‎በተንቀሳቃሽ ተሽከርካሪ ዝግጁ የሆነው ደ/በላይ ዘለቀ አየር ማረፊያ ላይ በተጠንቀቅ የነበረው ልዩ ነበር። እስከ አነስተኛ ቀዶ ጥገና ድረስ የሚሰራበት ክፍልና መሳሪያዎች የተሟሉለት፣ የራሱ ፋርማሲ ክፍል ያለው በመሆኑ የጤና ተቋማችንን እድገትና ዝግጁነት እንዲሁም የሀኪሞቻችንን ታታሪነትና ለህዝብና ለሀገር ገፅታ ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት በእጅጉ የሚያሳይ ነውና እጅግ ከፍተኛ ኩራት ተሠምቶናል በርቱልን።

‎እናንተን ይዘን ነገ ታላላቅ ሀገር አቀፍ፣ አህጉር አቀፍ እና አለም አቀፍ መድረኮችን ማካሄድ እንችላለን። እኛም አጋጣሚውን ተጠቅመን ጤናችንን ለመጠበቅ ምርመራ አድርገናል እግዚአብሔር ይመስገን ሁሉም ነገር ሠላም ነው።

‎ዶ/ር መንገሻ ፈንታው
‎የአብክመ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ

‎ባህር ዳር (ጥቅምት 15/7/2018 ዓ/ም)


‎ #አብክመጤናቢሮ

25/10/2025

Jimma is booming in medical care.
implant
therapy
Hospital
drug-waste disposal
edge technology
century ORs
Bravo team Jimma👉

27ኛው የጤናው ዘርፍ አመታዊ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም አገር አቀፍ የጤና ዘርፍ እቅድ ማስፈጸሚያ የጋራ ስምምነት  ሠነድ በመፈራረምና ቀጣይ አቅጣጫን በማስቀመጥ ተጠናቋል።____________የእ...
25/10/2025

27ኛው የጤናው ዘርፍ አመታዊ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም አገር አቀፍ የጤና ዘርፍ እቅድ ማስፈጸሚያ የጋራ ስምምነት ሠነድ በመፈራረምና ቀጣይ አቅጣጫን በማስቀመጥ ተጠናቋል።
____________

የእቅድ ማስፈጸሚያ የጋራ ስምምነት ሰነዱን የተፈራረሙት የጤና ሚኒስትር የተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የክልልና ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሃላፊዎች ሲሆኑ በመድረኩም አዲሱ የጤና ፖሊሲ አስተዋዉቀዋል።

በጉባኤው ማጠቃለያ ውይይት ላይ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከአጀንዳ ወደ ትግበራ የገባንበት ጊዜ ነው ያሉ ሲሆን የተሻሉ አፈጻጸሞችን ለማስቀጠል ክፍተቶችን በግብአትነት ለመወሰድ ያስቻለን ውጤታማ ጉባኤ ነበር በማለት ስራዎቻችን በተከታታይ በጋራ ጠንክረን መስራት አለብን ብለዋል።

ዶክተር መቅደስ የጤና አኢንፈስትመንትና ፋይናንስ ማሳደግ፣ የመጀመሪያ ጤና ክብካቤ ማሻሻል እንዲሁም በቴክኖሎጂ የተደገፈ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አስምረውበታል።

የጤና ባለሞያዎች የደሞዝ ጥያቄና የጤና ኢንሹራንስ ምላሽ የተሰጠ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሯ የባለሞያዎች ብቃት ምዘና ስርአት መዘርጋትና ሌሎች ጥቅማ ጥቅም በተሟላ መልኩ በአሰራር ለመመለስ፣ በየደረጃዉ ካለዉ አካላት ጋር በመሆን በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል።

በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ሲካሄድ የነበረዉ 27 ኛ ዉ የጤናው ዘርፍ የምክክር ጉባኤ ከ 1000 በላይ ተሳታፊዎች በአካል እንዲሁም ከ100 ሺህ በላይ በጤና ተቋማት ደረጃ በተመቻቸዉ በየነ መረብና ጎንዮሽ መድረክ ላይ ተሳትፈዉበታል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

SPHMMC Inaugurates Palliative Care UnitSt. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) has officially inaugurate...
25/10/2025

SPHMMC Inaugurates Palliative Care Unit

St. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) has officially inaugurated its Palliative Care Unit, marking an important step in providing compassionate and holistic care for patients with life-threatening illnesses.

The new unit focuses on improving the quality of life for patients and their families through medical, psychological, social, and spiritual support. It was established through the joint efforts of the hospital leadership and the Family Medicine Unit.

As part of the launch, SPHMMC also celebrated World Hospice and Palliative Care Day under the theme “Achieving the Promise: Universal Access to Palliative Care.”

The event brought together staff, patients, and families to highlight the importance of dignity, comfort, and care for all who need palliative support.

SPHMMC remains committed to delivering patient-centered and compassionate healthcare for all.

  For many, convenience comes at a cost, raising risks of kidney disease and hypertension. Unhealthy diets have led to l...
23/10/2025

For many, convenience comes at a cost, raising risks of kidney disease and hypertension. Unhealthy diets have led to losses of 31.3 billion Br (about 1.8pc of GDP) over a decade, and 26.9 billion Br in lost productivity. Excise taxes of up to 50pc on high-sugar oils and foods are already in place, but health advocates say more must be done.

Read more -

A bill that could transform the nutritional state sits in a limbo, even as the country faces an escalating epidemic of n...

  For many, convenience comes at a cost, raising risks of kidney disease and hypertension. Unhealthy diets have led to l...
23/10/2025

For many, convenience comes at a cost, raising risks of kidney disease and hypertension. Unhealthy diets have led to losses of 31.3 billion Br (about 1.8pc of GDP) over a decade, and 26.9 billion Br in lost productivity. Excise taxes of up to 50pc on high-sugar oils and foods are already in place, but health advocates say more must be done.

Read more - https://rebrand.ly/2e9eba

23/10/2025

እኔ ልክፈልላችሁ የጤና መድህንን ወጭ አለ እንዴ መንግስት?
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፦፦፦፦፦፦፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ተናግረናልኮ መንግስት እኮ ጤናውን የሚያሳየውና የሚያስረዳው አጦ እንጅ እንዴ ጤና ባለሙያ ያለ ዜጋ ላይ ራበኝ ሲባል እገልሃለሁ አይልም ብለናል።😂

ግን መዋጮው ስንት ነው? የሚገርም ጅማሮ ነው በውነቱ👉

👇
23/10/2025

👇

የ 27ኛው የጤና ሰክተር  ዓመታዊ ጉባኤ ተሣታፍዎች  የጅማ የአገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸው የመድኃኒት ማቃጠያ ማዕከልን ጎበኙ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጤና ሚኒስቴር 27ኛውን የጤናው ዘርፍ አመታዊ የ...
23/10/2025

የ 27ኛው የጤና ሰክተር ዓመታዊ ጉባኤ ተሣታፍዎች የጅማ የአገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸው የመድኃኒት ማቃጠያ ማዕከልን ጎበኙ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጤና ሚኒስቴር 27ኛውን የጤናው ዘርፍ አመታዊ የተሃድሶ ጉባኤ በጅማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል ፤ በመሆኑም ሁሉም የጤና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት ፣ ግብረሰናይ ድርጅቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተቋማት የአገልግሎቱን ጅማ ቅርንጫፍ የማቃጠያ ማዕከል ጎብኝተዋል ።

ጅማን ጨምሮ በሀገሪቱ 8 የተለያዩ ቦታዎች የማቃጠያ ማዕከሎች እንደሚገኙ ያነሱት የጤና ሚንስትር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፤ ይህም በአዋጅ ተካቶ በመመሪያ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋቱ የጤና ተቋማት የተከማቸ አገልግሎት የማይሰጡ የህክምና ግብዓቶች ወደ ማዕከሎቹ በማምጣት እንዲያስወግዱ ጥሪ አቅርበዋል ።

ወደ ማቃጠያ ማዕከሎቹ የሚሰበሰቡት የህክምና ግብዓቶች ጊዜ ያለፈባቸው ብቻ ሳይሆኑ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በጥራት ጉድለት የታየባቸውንም እንደሚያካትት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ አስረድተው ፤ ጤና ተቋማት በቅድሚያ ምንም አይነት መድኃኒት እንዳይባክን መስራት እንደሚገባቸው ጠቁመው ፤ ጊዜው ያለፈባቸውን ግን ማስወገድ ይገባል ብለዋል ።

የማቃጠያ ማዕከሉ ያለውን ተቋማዊ መዋቅር እና የአሰራር ሂደቱን እንዲሁም ቴክኒካል የማሽኑን አሰራር የጅማ ማዕከል ኦፕሬተር አቶ ስንሸው ከበደ ለጎብኚዎች በዝርዝር አስረድተዋል ።

በጉብኝቱ የተገኙ ተሳታፊዎች በማቃጠያ ማዕከሎቹ ዙሪያ ያላቸውን ጥያቄዎች አቅርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል ።

# ማገልገል ክብር ነዉ!
ዘጋቢ ማኅሌት አበራ

“የ9 ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” - የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ➡️ “የተጎዱት ወደ 8 ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው። በአጠቃላይ 2...
23/10/2025

“የ9 ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” - የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ

➡️ “የተጎዱት ወደ 8 ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው። በአጠቃላይ 28 ባለሙያዎች ተሳፍረው ነበር” - ዞን ጤና ቢሮ

ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ተውጣጥተው ለትምህርት ወደ ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሲጓዙ በነበሩ ጤና ባለሙያዎች በመኪና አደጋ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የክልሉና የዞኑ ጤና ቢሮ ባለስልጣናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ተስፋዬ ከበበው (ዶ/ር)፣ “የመኪና አደጋ ነው የደረሰው፤ የዘጠኝ ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” ሲሉ ሰማሁት ያሉትን መረጃ ነግረውናል።

አደጋው የደረሰው ጤና ባለሙያዎቹ ለፈተና ወደ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት መሆኑንም አስረድተዋል።

ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የአርሲ ዞን ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን ሐምዲኖ፣ ጤና ባለሙያዎቹ ለትምህርት (ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ ለኢንትራንስ ፈተና) ወደ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኮንትራት መኪና እየሄዱ እንደነበር፤ ብዙዎቹ ከአርሲ እንደሆኑና ወለንጪቲ አካባቢ ሲደርሱ አደጋው እንዳጋጣማቸው አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ሞትና የጉዳት መጠን የደረሰባቸው ስንት ናቸው? ብሎ ሲጠይቃቸውም፣ “የሞቱት 7 ናቸው፤ ሦስት ወንድና አራት ሴት። የተጎዱት ወደ ስምንት ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው” ብለዋል።

በመኪናው በአጠቃላይ 28 ሰዎች ተሳፍረው እንደነበር፣ ሁሉም ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ጤና ባለሙያዎች እንደነበሩ ገልጸው፣ “ሁሉም የጤና ጣቢያ ሠራተኞች ናቸው” ነው ያሉት።

ከተሳፋሪውቹ መካከል፣ “በ4ቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፤ አራቱ ታክመው ወጥተዋል” ያሉት ኃላፊው፣ አሰላና አዳማ ሆስፒታሎች ህክምና እየተከታሀሉ ያሉ ጤና ባለሙያዎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል።

አደጋው የደረሰው ከአዳማ ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲጓዙ ወለንጪቲ እንደደረሱ ትላንት ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ገደማ መሆኑንም ገልጸዋል።

አደጋው የተከሰተው፣ ከሀረርጌ ወደ አዳማ በርበሬ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዚና ባለሙያዎቹን የጫነው ተሽከርካሪ ተጋጭተው መሆኑም አቶ ሱልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በጉዳቱ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው አስረድተው፣ “የመኪና አደጋ በጣም እየበዛ ነው፤ ትራንስፓርትና ሎጂስቲክስ ቢሮዎች በደንብ መስራት አለባቸው። በየቀኑ የሰው ሕይወት እየጠፋ ነው፤ ንብረት ላይም ውድመት እየተደረሰ ነው፤ ጥንቃቄ ያስፈልጋል” ሲሉ አሳስበበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
👇

Address

Zambiya Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian health today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian health today:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram