18/05/2020
ግንቦት 10፣2012
በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ከእስከ ዛሬው ከፍተኛ የሆነ የኮሮና ቫይረስ ታማሚ ተገኘ፡፡
1 775 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 35 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙትን ሰዎች ቁጥር 352 አድርሶታል፡፡
ባለፉት 24 ሰዓታት ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው 17 ወንድምና 18 ሴት ናቸው ተብሏል፡፡
ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ እድሜአቸው ከ15 እስከ 80 መሆኑን ሚኒስቴሩ ተናግሯል፡፡
ከ35ቱ 29ኙ ከአዲስ አበባ፣ 1 ሰው ከኦሮሚያ ክልል፣ 4 ሰዎች ከሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ እንዲሁም 1 ሰው ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ ከተማ ለይቶ ማቆያ የተገኙ ናቸው ተብሏል፡፡
ከ35ቱ 24ቱ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው፣ 6ቱ የውጪ አገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው፣ ቀሪዎቹ 5ቱ የውጭ አገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
በሌላ በኩል በትናንትናው እለት 3 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 116 ደርሷል፡፡