Eka Kotebe Hospital - ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል

Eka Kotebe Hospital - ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል We are committed to becoming the premiere Neuroscience Institute in Africa, excelling in Mental Health, Neurology, and Neurosurgery.

This is the official page of Eka Kotebe General Hospital, Addis Ababa, Ethiopia. We are committed to becoming the first Neuroscience Institute in East Africa, with a focus on Mental Health, Neurology, and Neurosurgery.

የኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል የትንሳኤ በዓልን ከታማሚዎች እና ከሰራተኞች ጋር በደማቅ ሁኔታ አከበረ!አዲስ አበባ:-​ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።​በበ...
13/04/2026

የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የትንሳኤ በዓልን ከታማሚዎች እና ከሰራተኞች ጋር በደማቅ ሁኔታ አከበረ!

አዲስ አበባ:-​ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።

​በበዓሉ ዕለት የሆስፒታሉ የሲኒየር ማኔጅመንት አባላት በየክፍሉ በመዘዋወር በሕክምና ላይ የሚገኙ ታማሚዎችን የጎበኙ ሲሆን፣ ለታማሚዎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክትና የፈውስ ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። ይህ ጉብኝት ታማሚዎች የበዓል ስሜት እንዳይለያቸውና የብቸኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው ለማድረግ ነው።

​በተጨማሪም በበዓል ቀን ቤተሰቦቻቸውን ትተው በስራ ተረኝነት ላይ በመገኘት ለታማሚዎች ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የህክምና አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ማኔጅመንቱ አመስግኗል።

በ​መርሃ ግብሩ ለታካሚዎች ለአስታማሚ እንዲሁም ለስታፍ የምሳ ግብዣ በማድረግ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

ይህ ባህል የታካሚና የባለሙያዎችን ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር የተለመደ መልካም እሴት ነው።

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የፍቅርና የደስታ  ይሁንላችሁ። መልካም ፋሲካ!"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"
11/04/2026

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የፍቅርና የደስታ ይሁንላችሁ።

መልካም ፋሲካ!

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች!እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
10/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች!
እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በደብረ ብርሃን ለሚገኙ ወገኖች ሰብአዊ ድጋፍ አደረገ!​ደብረ ብርሃን — ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን ከተማ መጠለ...
03/04/2026

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በደብረ ብርሃን ለሚገኙ ወገኖች ሰብአዊ ድጋፍ አደረገ!

​ደብረ ብርሃን — ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው በደብረ ብርሃን ከተማ መጠለያ ለሚገኙ ወገኖች ሰብአዊ ድጋፍ አደረገ።

​ድጋፎቹ :-​የተለያዩ የአልባሳት አይነቶች፣
​እንዲሁም የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ይገኙበታል።

​ድጋፉን የተቀበሉ ወገኖች ሆስፒታሉ ላሳየው አጋርነትና ላደረገው ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ይህ ተግባር ሆስፒታሉ ከህክምና አገልግሎት ባሻገር ያለውን ማህበራዊ ሀላፊነትና ሰብአዊ ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት ሆኗል።

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
30/03/2026

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

📌 ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የምርምር የትኩረት መስክ ልየታን አከናወነ​📍 ቢሾፍቱ — ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የምርምርና ጥናት በተግባር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ አበይት የትኩረት መስኮችን (Th...
26/03/2026

📌 ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የምርምር የትኩረት መስክ ልየታን አከናወነ

​📍 ቢሾፍቱ — ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የምርምርና ጥናት በተግባር ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችሉ አበይት የትኩረት መስኮችን (Thematic Areas) የመምረጥ ስራ በቢሾፍቱ ከተማ ባካሄደው የምክክር መድረክ አከናወነ።

​🚩 የዶክተር መገርሳ አለሙ (የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር) ዋና ዋና ነጥቦች፦
​📍 ሆስፒታሉ በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ ላለው ሰፊ ስራ የምርምርና ጥናት ዘርፍ እንደ ጀርባ አጥንት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
​📍 ምርምርና ጥናቶች በመረጃ ላይ የተደገፉ (Evidence-based) መሆናቸው ለችግር ፈቺነታቸው ያላቸው ፋይዳ የላቀ ነው።
​📍 ጥናቶቹ የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ መሰረት እንደሚሆኑና ተቋሙ የጀመረውን የልህቀት ጉዞ ለማሳካት ሚናቸው የጎላ ነው።

​🚩 የወይዘሮ ወይናበባ ዳመነ (የሆስፒታሉ የምርምርና ጥናት ዳይሬክተር) መልዕክት፦
​📍 ዛሬ የተመረጡት የትኩረት መስኮች በቀጣይ ለሚከናወኑ የምርምር ስራዎች እንደ መሪ መንገድ እንደሚያገለግሉ ጠቁመዋል።
​🚩 የዶክተር ዮሐንስ ሞላ ገለጻ፦
​📍 ሆስፒታሉ ወደ ኒውሮሳይንስ ኢንስቲትዩትነት በሚያደርገው ሽግግር ውስጥ ሊከተላቸው ስለሚገቡ የጥናትና ምርምር አቅጣጫዎች እንዲሁም ስለ አጋርነትና ትብብር ስራዎች ሰፊ ገለጻ አቅርበዋል።
​🚩 የመድረኩ ማጠቃለያ፦
​📍 ተሳታፊዎች በየክፍላቸው በመለየት፣ አስቀድሞ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት የምርምርና ጥናት ዘርፎችን የመምረጥ ስራ አከናውነዋል።
​📍 ይህም ሆስፒታሉ በቀጣይ ለሚያደርጋቸው ሳይንሳዊ ግኝቶች ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

​📌 “የአገልግሎት ጥራት አርማችን!”

🏆ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል ላቦራቶሪ የ 4 ኮከብ እውቅና ተሸላሚ ሆነ! 🌟ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል ላቦራቶሪ በባዮ-ሴፍቲ እና ባዮ-ሴኩሪቲ (Bio-safety & Bio-security) ዘርፍ ባሳየው ...
24/03/2026

🏆ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላቦራቶሪ የ 4 ኮከብ እውቅና ተሸላሚ ሆነ! 🌟

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላቦራቶሪ በባዮ-ሴፍቲ እና ባዮ-ሴኩሪቲ (Bio-safety & Bio-security) ዘርፍ ባሳየው ከፍተኛ ብቃት የ4 ኮከብ የደረጃ እውቅና ሽልማት አገኘ። በ ሀገር አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ በሚካሄደው የሆስፒታሎች ሰርቲፊኬሽን ፕሮግራም፣በሁለተኛው ዙር ከተካተቱት እና ለ አንድ አመት ያህል በኘሮግራሙ ውስጥ ከቆዩ 18 ሆስፒታሎች መካከል ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላቦራቶሪ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።🎖

የሆስፒታሉ ላቦራቶሪ የባዮ-ሴፍቲ ባዮሰኪውሪቲ ፕሮግራም ውስጥ መካተት ካለባቸው የባዮሴፌቲ ደረጃ 2(BSL II )ላቦራቶሪዎች መካከል የሚካተት ሲሆን የአንድ አመት ሂደቱን ጨርሶ በ ዛሬው እለት ውጤቱ ይፋ ሆኗል ::

የስኬቱ ጉዞ፡ ይህ ውጤት የተገኘው ("base line Assessment" ) በማሰራት ፣ ተከታታይ ስልጠናዎችን በመውሰድ፣ በሜንተርሺፕ ፕሮግራም ውስጥ በማለፍ እና በመጨረሻም ጥብቅ በሆነ ግምገማ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ ነው።
በዚህ የእውቅና ፕሮግራም ከተሳተፉ የፌደራል ሆስፒታል ላቦራቶሪዎች መካከል ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላቦራቶሪ እና ጅማ ሆስፒታል ላቦራቶሪ ብቻ 4 ኮከብ ባለቤት መሆን ችለዋል። በተለይም በአዲስ አበባ ውስጥ ከተካተቱት 4 የፌደራል ሆስፒታሎች መካከል የ4 ኮከብ ደረጃን በማግኘት ኤካ ኮተቤ ሆሰፒታል ላቦራቶሪ ብቸኛ ና ቀዳሚ ሆኗል።✨

🙌የምስጋና መልዕክት፦ "ለዚህ ታላቅ ድል እና እውቅና ላበቃችሁን፣ ሌት ተቀን በቁርጠኝነት ለምትሰሩ ታታሪ የሆስፒታላችን ሰራተኞች በተለ ይም የላቦራቶሪ ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን!" 🎉🎊 እንኳን ደስ አለን !

“የአገልግሎት ጥራት አርማችን”

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ዒድ ሙባረክ! ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"
19/03/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ዒድ ሙባረክ!
ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል
"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

📌 ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በስትራክቸሩ ወደ አመራርነት ለመጡ ባለሙያዎች  የሙያ ማጎልበቻ (CPD) ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ! 🎓ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለዳይሬክ...
18/03/2026

📌 ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በስትራክቸሩ ወደ አመራርነት ለመጡ ባለሙያዎች የሙያ ማጎልበቻ (CPD) ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ! 🎓

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለዳይሬክተሮችና ለዴስክ ኃላፊዎች በቢሾፍቱ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ። ✨

🎤 መድረኩን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ረዳኤት ሰለሞን በንግግር ከፍተዋል።
📜 ጥልቅ ገለጻ በጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት ልማትና ሙያ ማሻሻያ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተገኔ አረጋ እና የሲፒዲ (CPD) ኤክስፐርት አቶ እውነቱ ገነት ሰፊና ጥልቅ ስልጠና ሰጥተዋል።
🚀💊ዓላማው፦ የጤና ባለሙያዎች በፍጥነት ከሚቀያየረው የጤናው ዘርፍ ጋር ራሳቸውን በማሳደግ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል ነው።

🔹 የተቀናጀ ስራ፦ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የሲፒዲ (CPD) ማዕከል በመሆኑ፣ ከሚኒስቴሩ ጋር በቅንጅት ለመስራት ያለመ መድረክ ነው። 🤝🏥
"ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ ለተሻለ የጤና አገልግሎት!" 💪🇪🇹

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

🌙 የፍቅር እና የአንድነት ምሽት በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል! ✨ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ታላቁን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ፣ ከሆስፒታሉ የሙስሊም ማህበረሰብ እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን...
17/03/2026

🌙 የፍቅር እና የአንድነት ምሽት በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል! ✨

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ታላቁን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ፣ ከሆስፒታሉ የሙስሊም ማህበረሰብ እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን ደማቅ የጋራ የአፍጥር ፕሮግራም አከናውኗል። 🥘🤝

በፕሮግራሙ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶር መገርሳ አለሙ እንደገለጹት፦

"የረመዳን ወር ወደ አምላክ ይበልጥ የምንቀርብበት፣ እርስ በእርስ የምንደጋገፍበትና ፍጹም ፍቅርን የምናስተላልፍበት ወቅት በመሆኑ፤ ተቋማችን ይህንን የአንድነት እሴት ሁልጊዜም በታላቅ ክብር ያከብራል።" 🕊❤️

የአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ አባላትም ሆስፒታሉ ላደረገላቸው ሞቅ ያለ አቀባበልና ላሳየው አጋርነት ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 🙏✨

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

🇪🇹🌙

ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል ለአመራር ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ!ቢሾፍቱ  — ኤካ ኮተቤ  ሆስፒታል በቅርቡ በሆስፒታሉ አዲስ መዋቅር ተወዳድረው ለአመራርነት የተመረጡ ባለሙያዎችን ክህሎ...
14/03/2026

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ለአመራር ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ!

ቢሾፍቱ — ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በቅርቡ በሆስፒታሉ አዲስ መዋቅር ተወዳድረው ለአመራርነት የተመረጡ ባለሙያዎችን ክህሎት የሚያሳድግና ተቋማዊ ሪፎርሙን የሚያፋጥን ጥልቅ ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ ሰጠ።

የስልጠናውን መርሃ-ግብር በንግግር የከፈቱት የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር መገርሳ አለሙ እንደገለጹት፤ አዲሱ መዋቅር ውጤታማ እንዲሆን አመራሩ በዘመናዊ የሥራ አመራር ዕውቀት ራሱን ማብቃት ይኖርበታል ብለዋል
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ አመራሮች የአሰራር ስልቶችን በመቀየስና የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቶችን በማቀላጠፍ ለታካሚዎች ጥራት ያለውና ቀልጣፋ ግልጋሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል።

ይህ ስልጠና በዋናነት ትኩረት ያደረገው በቀጣይ በሚከናወኑ የሆስፒታሉ የሥራ እንቅስቃሴዎች ላይ የጥራት ደረጃን ለማዘመን በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ነው።

የስራ ሀላፊዎች የስራ መዘርዝርን በመውሰድ ተፈጻሚ እንዲያደርጉ ዘመናዊ የሥራ ስልቶችን መዘርጋት፣ ግልጽ የሆኑ የተጠያቂነት መመሪያዎችን ተግባራዊ ማድረግ፣ ሠራተኞችን የሚያበረታቱ የማትጊያ መመሪያዎችን ሥራ ላይ ማዋል የሚሉ ነጥቦች በስልጠናው በስፋት ተዳስሰዋል።

እነዚህ መመሪያዎች ተቋሙ የላቀ፣ የተቀላጠፈና በውጤት ሊለካ የሚችል የሥራ ባህል እንዲገነባ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል።

በስልጠናው ላይ የተሳተፉ የየክፍሉ ዳይሬክተሮች እና የዴስክ ኃላፊዎች በስራቸው ለሚገኙ ባለሙያዎች ስራን በቁጥርና በጊዜ ለክቶ የመስጠት፣ የሥራ አፈፃፀምን ተከታትሎ የመረከብ እንዲሁም በትጋት ለሚሠሩ ባለሙያዎች ተገቢውን ዕውቅና የመስጠት ክህሎታቸውን የሚያሳድጉ የሥልጠና ሞጁሎች ቀርበውላቸዋል።

በተጨማሪም በሥራ ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን አስቀድሞ በመለየትና መፍትሔ በመስጠት፣ የሆስፒታሉን ራዕይ ዳር ለማድረስ የሚያስችል "ተቋማዊ የአሠራር ሮድ ማፕ" ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ሰልጣኞቹ በቆይታቸው የቀሰሟቸውን ዕውቀቶች በሥራ ላይ እንዴት ማዋል እንደሚችሉ የሚያሳዩ ዕቅዶችን አቅርበው የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

"የአገልግሎት ጥራት አርማችን"

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል እና ዲላ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙአዲስ አበባ – ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ ባለው ጠንካራ ጥረት፣ ከ...
11/03/2026

ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል እና ዲላ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ – ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ ባለው ጠንካራ ጥረት፣ ከውጭ አገራት ተቋማት ጋር የሚያደርገውን ትብብር ከመጠናከር ባሻገር ከአገር በቀል ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያሳደገ ይገኛል።

🤝በዚሁ መሰረት ዛሬ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ ስራን የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈራርሟል።

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታልን በመወከል የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር መገርሳ አለሙ እና የቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት ግዛው ተገኝተዋል። እንዲሁም ዲላ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ አለሙ እና የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ መምህር ትዛለኝ ተስፋዬ ተሳትፈዋል።

🏥የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር መገርሳ አለሙ እንደገለጹት፤ ከአገር በቀል ተቋማት ጋር በጋራ መስራት የታካሚዎችን የህክምና ጥራት ለማሻሻልና አገር በቀል እውቀቶችን ለማሳደግ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በተለይም የስነ-አእምሮ ህክምና ማዘመን እና በምርምርና ጥናት መስኮች ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር የሚደረግ ትብብር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል።

🎓የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ኤሊያስ አለሙ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በጋራ መስራታቸው ወጣት የተማረ የሰው ኃይል ለማፍራትና አገር በቀል እውቀቶችን በማበልፀግ የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል እንደሚረዳ ገልጸዋል። እንዲሁም ይህ ትብብር በተለይ የስነ-አእምሮ ህክምናን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያደርሰው አመልክተዋል።
ይህ ስምምነት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የስራ ትስስር የሚያጠናክር ሲሆን፣ በጋራ የውል ስምምነት ሰነድ ፊርማ ስነ-ስርዓቱ በስኬት ተጠናቋል።

“✨ ጥራትን ለማሻሻልና ምርምርን ለማሳደግ በጋራ እንሰራለን!”

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eka Kotebe Hospital - ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share