Ethiopian Health professionals

Ethiopian Health professionals page to voice for Ethiopian health professionals burning issues and general public health concerns

06/12/2025

በጣም ያሳዝናል ሐኪም የሚራብበት ና የሚያለቅስበት አገር ?
ሂፖክራቶስ ኦት ይብቃኝ !!ትኩረት ለጤና ባለሞያዎች
አንድ ወንድማችን ሐኪም በመሆኑ በጣም ከፍቶት እንዲህ በማለት አልቅሰዋል ዕድሜየን የገፈገፍኩብህ በቀን አንዴ ለመብላት ነው ?
ያ ሁሉ ዓመት የጨረስኩብህ ቤተሰብ ላለመርዳት ነው ?

06/12/2025

Doctors salary by country
Ethiopian doctors 75$per month is it fair to be here?

06/12/2025

#አስቸኳይ #ዜና #ከጅንካ #ሆስፒታል
በጅንካ ጀነራል ሆስፒታል የምንሰራ ባለሙያዎች እስካሁን ውዝፍ ደመወዝ አልተከፈለንም።ግማሹ ሞቷል የቀረንም ከሞት ጋር ፊትለፊት እየተጋፈጥን ነን።😭😭

06/12/2025

በሰሜን ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ የምንሰራ የጤና ባለሙያዎች ነን ወረዳው በአዲሱ ደሞዝ አልከፍልም በማለት Duty ከተከፈለን 3ወር ሞላን
ድምፅ ሁኑን

 እኛ በሲዳማ ክልል የወንዶ ገነት ወረዳ የመጆ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ነን። ሆኖም የወረዳ አስተዳደሩ  የትርፍ ሰአት ክፍያ አንከፍልም ከአቅማችን በላይ ነው የፈደራል መንግስት የ...
06/12/2025


እኛ በሲዳማ ክልል የወንዶ ገነት ወረዳ የመጆ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ነን። ሆኖም የወረዳ አስተዳደሩ የትርፍ ሰአት ክፍያ አንከፍልም ከአቅማችን በላይ ነው የፈደራል መንግስት የእናንተን ደሞዝ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ገንዘቡን አልለቀቀልንም በሚል ፔሮልም መልሰው ደሞዝም አልገባልንም

የሀዘን መግለጫ በዋግ ህምራ ዞን የአምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል   ዳይሬክተር የነበሩት ሲ/ር ካሰች ማሞ(pedatric nurse ) ባደረባቸው ህመም በደሴ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  ፅ...
05/12/2025

የሀዘን መግለጫ

በዋግ ህምራ ዞን የአምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ዳይሬክተር የነበሩት ሲ/ር ካሰች ማሞ(pedatric nurse ) ባደረባቸው ህመም በደሴ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፅኑ ህሙማን በህክምና ሲረዱ ቆይተው ህዳር 24ቀን 2018 ዓ.ም በደረሰባቸው ድንገተኛ ሞት ከዚህ አለም አርፈዋል።ቀብራቸውም በቀን 25/3/18 በቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስትያን ተፈፅሟል።

 ድምፅ ሁኑልን.....እኛ በሲዳማ ክልል የአሮረሳ ወረዳ የመጆ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ነን። ሆኖም የወረዳ አስተዳደሩ ደሞዝም የትርፍ ሰአት ክፍያ አንከፍልም ከአቅማችን በላይ ነው...
05/12/2025


ድምፅ ሁኑልን.....እኛ በሲዳማ ክልል የአሮረሳ ወረዳ የመጆ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ነን። ሆኖም የወረዳ አስተዳደሩ ደሞዝም የትርፍ ሰአት ክፍያ አንከፍልም ከአቅማችን በላይ ነው የፈደራል መንግስት የእናንተን ደሞዝ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ገንዘቡን አልለቀቀልንም በማለት ለመጠየቅ የሄዱትን ሰራተኞችን በፖሊስ አስፈራራተው በማሰርና በመሳደብ ሁለተኛ ጥያቀ ይዛችሁ አትምጡ ከመጣችሁ ደግሞ እንደምትታሰሩ አውቃችሁ ኑ በማለት ከትናንት ማታ ጀምሮ የሆስፒታሉ ሥራ ሙሉ በሙሉ ዝግ ነው

05/12/2025

#አራተኛዋ #ታካሚ #ከማርበርግ #ቫይረስ #አገገመች

“ከሞት አፋፍ ስለታደጉኝ ከፈጣሪ ቀጥሎ ጤና ባለሙያዎችን አመሰግናለሁ!”

(ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ነፃ የሆነች እናት)
በለይቶ ማቆያ የህክምና ክትትል ሲደረግላት የቆየች እናት ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ነፃ በመሆኗ የጤና ባለሙያዎችን አመሰገነች።

ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ነፃ በመሆን የዳነች አራተኛዋ ታካሚ ከቫይረሱ ነፃ እንዲትሆን ለረዱ የህክምና ባለሙያዎች ምስጋና ይገባል ስትል ገለጸች ።

ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ነፃ የሆነች ወ/ሮ ማርታ ግዛቸው

05/12/2025

አሜሪካ በ Clinical trial(phasell) ደረጃ ላይ ያለ የማርበርግ ቫይርስ ክትባት ለኢትዮጵያ በድጋፍ መልክ ሰጠች።

Congratulations, Dr Eyerusalem Bergene Banti!Your outstanding achievement in securing the highest score in the 2025 COSE...
04/12/2025

Congratulations, Dr Eyerusalem Bergene Banti!
Your outstanding achievement in securing the highest score in the 2025 COSECSA Neurosurgery Exam makes every Ethiopian health professional proud. This milestone reflects your discipline, sharp focus, and relentless hard work.

Once again, heartfelt congratulations, Dr. Eyerusalem. We celebrate this moment with you and wish you even greater heights in the years ahead.

04/12/2025


ሰላም እንዴት ናችሁ እኔ ምሰራው በአማራ ክልል ኦሮሞ ልዩ ዞን ሲሆን ዲውቲ በአዲሱ ደሞዝ ስኬል አንከፍልም ደብዳቤ አልመጣልንም በሚል ምክንያት ይሄው ከመስከረም ወር ጀምሮ እስካሁን በድሮው ነው እየተከፈለን ያለው እና ምንም አታመጡም በሚል ሌሎች እየተከፈሉ እያ ግን እየተሰቃየን ነው ድምጽ ሁነን

"የበንሳ ዳዬ  ጠቅላላ ሆስፒታል ሰራተኞች"ሰላም እንዴት ናችሁ? ድምፅ እንድትሆኑን ስለመጠየቅ ነው እኛ የበንሳ ዳዬ ጠቅላላ ሆስፒታል ሰራተኞች በብርድ እና ቁር ተፈራርቆብን የሚሊሻ እና አድ...
04/12/2025

"የበንሳ ዳዬ ጠቅላላ ሆስፒታል ሰራተኞች"

ሰላም እንዴት ናችሁ? ድምፅ እንድትሆኑን ስለመጠየቅ ነው እኛ የበንሳ ዳዬ ጠቅላላ ሆስፒታል ሰራተኞች በብርድ እና ቁር ተፈራርቆብን የሚሊሻ እና አድማ ብተና ስድብና ጥፊ ችለን የሠራነውን የትርፍ ሰአት ክፍያ የመስከረም እና የጥቅምት አልተከፈለንም ።ክፈሉን ብለን ሰንጠይቅ በአዲሱ ደሞዝ ሳይሆን በነባሩ ደሞዝ ሰርታችሁ አምጡ በማለት እያንገራገረን ይገኛል እና ስቃያችን መገፋታችን የሚሰማ ህዝብና አስተዳደር ካለ አድርሱልን።
እናመሠግናለን!!

ከታች የሆስፒታሉን ስራ አስኬአጅ መልስ አያያዛለሁ
ሰላም እንዴት ዋላችሁ ሁላችንም ታካሚወችን በተገቢ ሁኔታ ለማገዝ እና ለመርዳት የምናረገው እርብርብ ከፍተኛ ነው ። ይህም ይሁን የሚያስብል እና የሚያስመሰግን ነው።
ይሁን እንጂ የትርፍ ሰአት ክፍያ በበጀት እጥረት ምክንያት መዘግየቱ ይታወቃል ይህም የሆነበት በተጨመረው ደመወዝ ምክንያት የሚመጣው የዲውቲ ክፍያ ልዩነት በጀት እስኪሰጠን እንድንጠብቅ ነው።
ስለሆነም ፣ በሁሉም ቦታ የዲውቲ ጥያቄ እየተነሳ ነው እንደሆስፒታል የምንሰጠው አቅጣጫ እንደሚከተለው ነው።
1.በክልሉ ጤና ቢሮ እና ገንዘብ ቢሮ በጀቱ ተፈቅዶ እስኪመጣ ድረስ መጠበቅ
2. በጀቱ እስኪፈቀድ ድረስ በድሮው ደመወዝ የመስከረምን ለጊዜው መክፈል እንችላለን ከዛም ባክ ፔይ እንከፍላለን።
3.ለሚመለከታቸው አካላት ጤና ቢሮ፣ገንዘብ ቢሮ እና ቦርድ አሳውቀናል በድጋሜ እንጠይቃለን ።
እንደተፈቀደ በተገቢው እና በአዲሱ እንከፍላለን።
እስከዛው ተረጋግቶ መጠበቅ ያሻል የተለያየ ተቋም ከፍሏል የሚባለው የተረጋገጠ መረጃ የለም የተሰጠው አቅጣጫ የከፈለ ተቋም ህገወጥ ነው በሚል የተገለፀ ነው።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Health professionals posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram