26/07/2025
የጤና አገልግሎትን ለማሻሻል ጠንካራ የሰዉ ሀብት አስተዳደር ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ተገለፀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የሰዉ ሀብት አስተዳደር ልማት ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ምክክር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ነቢዩ ቤዛ በወቅቱ እንዳሉት፣ የጤና አገልግሎትን ለማሻሻል ጠንካራ የሰዉ ሀብት ልማት ሥርዓትን መዘርጋት ይገባል።
በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ8ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎች የአጫጭር ጊዜ ስልጠና ወስደዋል ብለዋል።
የጤና ባለሙያዎችን ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋር ለማላመድ በሰፊዉ ተሰርቷል ነዉ ያሉት።
የጤና መረጃን ዲጂታላይዝ ለማድረግ በተከናወነ ተግባር የ29 ሺህ ባለሙያዎችን መረጃ ወደ ቋት ማስገባት መቻሉን ጠቁመዋል።
በበጀት ዓመቱ በጤናዉ ዘርፍ ከተለዩ 61 የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች 58ቱ ምላሽ ማግኘታቸዉን አብራርተዋል።
የጤና ባለሙያዎችን የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
መዋቅሮች የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በየደረጃዉ ለመመስ መስራት አለባቸዉ ብለዋል።
በመድረኩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲና ጤና ሳይንስ ኮሌጂ አመራሮች፣የዞን ጤና መምሪያ የሰዉ ሀብት ልማት አስተዳደር ባለሙያዎች፣የደም ባንካ ተወካዮች፣ የሲፒዲ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።