22/04/2026
በሆስፒታላችን መደበኛ የነርሲንግ እና ሚድዋይፈሪ ሰርቪስ ማኔጅመንት ውይይት ተካሄደ።
ቀን: 13/08/2018 ዓም
በአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል መደበኛ የነርሲንግ እና ሚድዋይፈሪ ሰርቪስ ማኔጅመንት ውይይት አካሄደ።
በውይይቱም ሁለት አንኳር አጀንዳዎች ዙሪያ የመከሩ ሲሆን
በአንደኛነት ደረጃ የተቋሙን ጠቅላላ ወራዊ አፈፃፀም የተገመገመ ሲሆን በሁለተኛነት ደረጃ የተቋሙ ዋነኛ ግብ የሆነውን የተገልጋይ ዕርካታና ዕሴቶች ዙሪያ በጋራ መክረዋል።
በወራዊ አፈጻጸሙ ዙሪያ እንደ ጠንካራ ጎን ተብለው የተወሰዱና ሊቀጥሉ ይገባል የተባሉትን በማስቀጠል መሻሻል በሚገባቸው ዙሪያም በአጽኖት መክረዋል።
በተጨማሪም የተገልጋይን እርካታና ዕሴቶችን በሚጨምሩ የአሰራር ለውጦች በመዘርጋት ለተሻለ ውጤት በጋራ ወደ ተግባር የሚገባበት አግባብ እንደሚኖር አሳስበዋል።
በመጨረሻም በጋራ በመሆን የተሻሉ ውጤቶችን ለማስመዝገብ በጋራ መግባባት ተጠናቋል።
በውይይቱም የነርሲንግ እና ሚድዋይፈሪ ሰርቪስ ማኔጅመንት ኃላፊዎች እና የሁሉም የሥራ ክፍል አስተባባሪዎች በውይይቱ ታድመዋል።
@አርባምንጭ