Nigist Eleni Hospital-WCU

Nigist Eleni Hospital-WCU Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nigist Eleni Hospital-WCU, Hospital, Hossana.
(2)

Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital is Wachemo University's Medicine and Health Science College Hospital with almost all the specialities

01/11/2025

የቅድመ-ጡት ካንሰር ምርመራዎችን ልምድ በማድረግ የጡት ካንሰር ሕመምን መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ!!
ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም
*********//**********
ከ 1:00 ሰዓት የምሽት ዜና በሗላ በደቡብ ቴሌቭዥን ይጠብቁን!!

ለተከታታይ አምስት ቀናት በነጻ ሲሰጥ የቆየው ቅድመ የጡት ካንሰር ምርመራና ህክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ!ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም*********//********በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌ...
31/10/2025

ለተከታታይ አምስት ቀናት በነጻ ሲሰጥ የቆየው ቅድመ የጡት ካንሰር ምርመራና ህክምና አገልግሎት ተጠናቀቀ!
ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም
*********//********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለተከታታይ አምስት ቀናት በነጻ ሲሰጥ የነበረው ቅድመ የጡት ካንሰር ምርመራና ህክምና አገልግሎት በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ እንደተናገሩት ፦ የጡት ካንሰር በወቅቱ ተመርምሮ ከታወቀና ልየታ ከተደረገለት ሊታከም እንደሚችል ጠቅሰው ሴቶች በጡታቸው ለይ እብጠት ፣ የቅርጽ ለውጥና ህመም በሚሰማቸው ጊዜ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ያሬድ ደሳለኝ በመልዕክታቸው እንደተናገሩት ፦ የጡት ካንሰርን በወቅቱ በመመርመርና በማከም ሊከሰት የሚችል ሞትን መቀነስ እንደሚቻል በመናገር ይህን መሰል የቅድመ ካንሰር ልየታ ምርመራዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

አክለውም ዶ/ር ያሬድ እንደገለጹት ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲሰጥ በነበረው የቅድመ ካንሰር ምርመራ ከ 400 በላይ ሴቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ በመጥቀስ በቀጣይም የተገልጋዩን ቁጥር ከፍ በማድረግ መሰል አገልግሎቶችን እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው።
Let Your light shine in the Society!!

28/10/2025
የጡት ካንሰርን መከላከል የሚያስችል ምርመራ በንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በነጻ መስጠት ተጀመረ!!ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም*******//********...
27/10/2025

የጡት ካንሰርን መከላከል የሚያስችል ምርመራ በንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በነጻ መስጠት ተጀመረ!!
ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም
*******//********

የጡት ካንሰርን መከላከል የሚያስችል ምርመራ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆሳናና አከባቢዋ ለሚገኙ እድሜያቸው ከ 25 ዓመት ለሚበልጥ ሴቶች በነጻ መስጠት ተጀምሯል።

ምርመራውም ለተከታታይ 5 ቀናት እንደሚቀጥልም በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ያሬድ ደሳለኝ ተናግረዋል።

ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው።
Let Your light shine in the Society!!

ከጡት ካንሰር መዳን እንደሚችሉ ያውቃሉ?********//*******የጡት ካንሰር ከ 8  ሴቶች በ አንዷ ላይ ይከሰታል ። ይህም ሴቶች ላይ ከሚከሰት ገዳይ የካነሰር አይነቶች ውስጥ በአንደኝነ...
26/10/2025

ከጡት ካንሰር መዳን እንደሚችሉ ያውቃሉ?
********//*******

የጡት ካንሰር ከ 8 ሴቶች በ አንዷ ላይ ይከሰታል ። ይህም ሴቶች ላይ ከሚከሰት ገዳይ የካነሰር አይነቶች ውስጥ በአንደኝነት እንዲቀመጥ አድርጎታል።

ይሁን እንጅ ቀድመው ከተመረመሩ እና ህክምናውን በአግባቡ ከተከታተሉ ከበሽታው ፈፅሞ ይድናሉ።
ለሆሳናና አካባቢው ነዋሪወች በሙሉአለም አቀፍ የጡት ካንሰር ግንዛቤ መስጫ ወርን በማስመልከት ከነገ ጥቅምት 17 ጀምሮ ለ አንድ ሳምንት የሚቆይ የራስ-በራስ የጡት ምርመራና ስልጠና እንዳስፈላጊነቱ ነፃ የጡት አልትራሳውንድ ምርመራ፣ ነፃ የፓቶሎጂ ምርመራን ጨምሮ ነፃ ምክር አገልግሎት የምንሰጥ ስለሆነ ማንኛውም እድሜው ከ25 ዓመት በላይ የሆኑ እናቶች ከጥዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በንግስት እሌኒ ሆስፒታል በመገኘት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናሳስባለን።
ቀድመው ይመርመሩ ህይወት ይታደጉ!

ዶ/ር ያሬድ ደሳለኝ የ ካንሰር ህክምና ስፔሻሊስት
ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ።
Let Your light shine in the Society!!

25/10/2025

25/10/2025

📣መልካም ዜና ለሆሳዕናና አካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ
———————————-
♻️አለም አቀፍ የጡት ካንሰር ግንዛቤ መስጫ ወርን በማስመልከት ከመጪው ጥቅምት 17 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራና የምክር አገልግሎት በንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚሰጥ ስለሆነ ማንኛውም ከ25 እድሜ በላይ የሆኑ ሴቶች ከጧዋቱ 2 :30 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት:-
❇️ነፃ የራስ በራስ የጡት ምርመራና ስልጠና
❇️ነፃ የጡት አልትራሳውንድ ምርመራ
❇️ነፃ የፓቶሎጂ ምርመራን ጨምሮ
❇️ነፃ ምክር አገልግሎት የምንሰጥ ስለሆነ
እርሰዎም የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።

♥️ልብ ይበሉ!
🔰የጡት ካንሰር ከ8 ሴቶች በአንዷ ላይ ይከሰታል ። ይህም ሴቶች ላይ ከሚከሰት ገዳይ የካነሰር አይነቶች ውስጥ በአንደኝነት እንዲቀመጥ አድርጎታል።ይሁን እንጅ ቀድመው ከተመረመሩ እና ህክምናውን በአግባቡ ከተከታተሉ ከበሽታው ፈፅሞ ይድናሉ።

ቀድመው ይመርመሩ ህይወትዎን ይታደጉ!

ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል!

23/10/2025
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የቁልፍ አፈፃፀም አመላካች/KPI የእቅድ ስምምነት ውል ከተቋሙ ከተለያዩ የስራ ዘርፎች ጋር የፊርማ ማኖር ክንውን ተደረገ።ጥቅም...
21/10/2025

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የቁልፍ አፈፃፀም አመላካች/KPI የእቅድ ስምምነት ውል ከተቋሙ ከተለያዩ የስራ ዘርፎች ጋር የፊርማ ማኖር ክንውን ተደረገ።
ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም
*******//*******

ከትምህርት ሚኒስቴርና ከጤና ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚገኙ የማስተማሪያ ሆስፒታሎች ከታቀዱና ሊተገበሩ ከታሰቡ እንዲሁም ቀልጣፋና ጥራቱን የጠበቀ ህክምና ፣ የሆስፒታሎች ተወዳዳሪ የመማር-ማስተማር ስርአትን እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚረዳው የቁልፍ አፈፃፀም አመላካች (KPI) ስምምነት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተለያዩ የስራ ዘርፍ ሀላፊዎች ጋር ተደርጓል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት፦

ከተለያዩ ዘርፍ ሀላፊዎች ጋር የቁልፍ አፈፃፀም አመላካች(KPI) የስምምነት መደረጉ በተቋሙ በየደረጃውና በየተዋረዱ የስራ ተግባራቶችን ቆጥሮ ለመረከብ፣ በጥራትና በብቃት ስራን በመወጣት እንዲሁም ሆስፒታሉን ይበልጥ የሚያዘምኑ በርካታ ስራዎችን ከውጤት ጋር አስተሳስሮ ለማስኬድ እንደሚረዳ ተናግረዋል።

አክለውም ዶ/ር ይድነቃቸው እንደተናገሩት የየዘርፉ ሀላፊዎች KPI ተከትሎ በመስራት የተሻለ ወጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው በመግለጽ ይህንንም ለማሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲወጡም መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዕለቱም የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ከተለያዩ ዘርፍ ዳይሬክተሮችና ዲን ጋር ስምምነቱን ፈፅመዋል።

በመጨረሻም በሆስፒታሉ ውስጥ እየተሰጡ የሚገኙ በርካታ የህክምና አገልግሎቶችን ጥራታቸውን ከፍ ለማድረግ በሚያስችሉ ሃሳቦች ዙሪያ ከሆስፒታሉ የ Quality ስራ አባላት ጋር በመወያየት ውጤት በሚያስገኙ ሀሳቦች ዙሪያ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው።
Let Your light shine in the Society!!

179 ኛው የአለም-አቀፍ የ አንስቴዥያ ቀን በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በደማቅ ሁኔታ ተከበረጥቅምት 8/2018 ዓ.ም******//*******179ኛው የአለም-አቀፍ የአንስቴዥያ ቀን በዋቸሞ...
18/10/2025

179 ኛው የአለም-አቀፍ የ አንስቴዥያ ቀን በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ
ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም
******//*******

179ኛው የአለም-አቀፍ የአንስቴዥያ ቀን በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በደማቅ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን በዕለቱም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ የትምህርት ክፍሉ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኤርሚያስ ሞሊቶ እንደተናገሩት፦ የአንስቴዥያ ህክምና መኖሩ ውጤታማ የሆነ የቀዶ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ባለሞያውም ሀላፊነቱ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ በከፍተኛ ትኩረት እና በአገልጋይነት መንፈስ መስራት እንደሚገባው አሳስበዋል።

አክለውም ዶ/ር ኤርሚያስ፦ የአንስቴዥያ አገልግሎት ከጊዜ ወደጊዜ እየዘመነ መምጣቱን ተከትሎ ለታካሚዎች ያለው ፋይዳ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።
በመጨረሻም ለመላው የአንስቴዥያ ባለሞያና ተማሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጥቅምት 8/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው።
Let Your light shine in the Society!!

የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ዲፕሎማ ስልጠና በዋችሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስጀመርያ ፕሮግራም ተካሔደጥቅምት 7/2018 ዓ.ም*******...
17/10/2025

የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ዲፕሎማ ስልጠና በዋችሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስጀመርያ ፕሮግራም ተካሔደ
ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም
*******//********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲብ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ዲፕሎማ ስልጠና በሆስፒታሉ ውስጥ በማስተማር ለሚገኙ ሀኪሞች መስጠት ተጀምሯል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የፔዳጎጅካል ስልጠና ማዕከል አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ብርቅነሽ አለሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ሲሆን በንግግራቸውም ስልጠናው በ ሁለት ሴሚስተር እንደሚሰጥ በመግለጽ ሰልጣኝ መምህራን ክላሱን ሳያቆራርጡ መከታተል እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው።
Let Your light shine in the Society!!

Address

Hossana
42528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigist Eleni Hospital-WCU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category