06/03/2026
የሚቶ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በሀይጅን ና አካባቢ ጤና አጠባበቅ ስራ ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻና ሞዴል ቀበሌዎችን ለመፍጠር የንቅናቄ መድረክ አካሄደ!
የካቲት 27/2018 የሚቶ ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን
በስልጤ ዞን የሚቶ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በሀይጅን ና አካባቢ ጤና አጠባበቅ ስራ ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻና ሞዴል ቀበሌዎችን ለመፍጠር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።
በዕለቱም ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻ ና ሞዴል ቀበሌያትን ለመፍጠር የተዘጋጀውን ሰነድ የጽ/ቤቱ ምክትል ሀላፊ አቶ ዋበላ አብዶ አቅርበው በሰፊው ውይይት ተደርጎበታል።
በዕለቱም መድረክ የተገኙት የሚቶ ወረዳ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ፎሌ ሞሳ እንዳሉት፦ጤና ለሁሉም ነገር ወሳኝ እንደሆነ አንስተው ጤናማ ና አምራች ዜጋን በመፍጠር የተጀመረውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞን እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሁሉም አካል ለተግባሩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት እና ጤና ለሁሉም ልማቶች መሰረት ስለሆነ ማህበረሰቡ ጤናውን በተገቢው መጠበቅ እንዳለበት ገልጸዋል።
ሞዴል መጸዳጃ ቤቶችን በመገንባት ሞዴል ቀበሌያትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት በቁርጠኝነት ና በትኩረት መስራት እና ማህበረሰቡ በሁሉም የልማት ስራዎች ላይ ውጤታማ እንዲሆን መጀመሪያ ጤናው እንዲጠበቅ ሚናውን በሚገባ መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።
የሚቶ ወረዳ ጤና ጽ/ቤተረ ኃላፊ አቶ ዋበላ ኡስማን በበኩላቸው እንደገለጹት፦የማህበረሰቡን የልማት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ በጤናው ዘርፍ ላይ ከባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ በመስራት ጤናማ ዜጋን ለመፍጠር በልዩ መልኩ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻ በማድረግ ሞዴል ቀበሌያትን መፍጠር የማህበረሰቡን ጤና በተገቢው ለመጠበቅ የጎላ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የማህበረሰቡን ጤና በተገቢው ለመጠበቅ እና አካባቢዎችን ከውጭ ከመጸዳዳት ነጻ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀራርበው በባለቤትነት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።