22/10/2021
፨፨በወምበርማ ወረዳ ሀገር አቀፍ የፓሊዮ ዘመቻ እየተካሄደ ነው፨፨፨
--------------------------------------------------------------------
ከዛሬ ጥቅምት 12 እስከ 15 የሚቆይ የፓሊዮ (የልጅነት ልምሻ) በሽታ መከላከያ ክትባት
በዘመቻ ዕድሜያቸው ከ5ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ቤትለቤት እየተሰጠ መሆኑን የወረዳው የህፃናትእና ስነ ምግብ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ደረጀ ዘውዴ ተናግረዋል ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አቶ ደረጀ እንደገለፁት ፓሊዮ #በቫይረስ የሚመጣ አስከፊ በሽታ መሆኑን እና በሽታው ፓሊዮ ቫይረስ 1,2,3 ዘር አማካኝነት የሚመጣ መሆኑን በመግለፅ ዋና መተላለፊያ መንገዱም ከታመመ ህፃን ከአይነ-ምድር ጋር በሚኖር ወደ አፍ ንክኪ መሆኑን ፤
በከፍተኛ ደረጃ ተላላፊ በመሆኑ እና ህፃናት ላይም የልጅነት ልምሻን የሚፈጥር አስከፊ ቫይረስ በመሆኑ ዘመቻውን ለሁሉም ህፃናት ቤትለቤት እና በተመረጡ ቦታዎች እንዲሰጥ እና ዘመቻውም ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የቅድመ ዘመቻ ስራዎችን ተሰርተዋል ። ከተሰሩ ተግባራት መካከል
፨ ለሚመለከታቸው አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ፤
፨፨ ለጤና ባለሙያዎች ፤
፨፨፨ ለጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ፤
፨፨፨፨ ለማህበረሰብ የቤትለቤት ቀስቃሾች፤
፨፨፨፨ ለክትባት ማስቀመጫ ፍሪጆች እና ቅዝቃዜ መጠበቂያ እና ማንቀሳቀሻ ቁሳቁስ በማሰራጨት ጥሩ የቅድመዝግጅት ሰራ መሰራቱን ጠቅሰው
ማህበረሰቡም ታላሚ ከ5ዓመት በታች ህፃናትን በመደበኛ እና በዘመቻ የሚሰጡ የፓሊዮ መከላከያ ክትባት በማስከተብ በፓሊዮ አማካኝነት የሚከሰት የልጅነት ልምሻነትን(ሽባነትን) እንዲሁም ሞትን እንዲከላከል ጥሪ አቅርበዋል ::
የወምበርማ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨