Psych Addis - ሳይክ አዲስ

Psych Addis - ሳይክ አዲስ ይህ ገጽ የሥነ-ልቦና ሳይንስን ለሕይወታችን እንዲመች አድርገን እንድንጠቀም የሚያስችል መረጃ የምናገኝበት ነው:: ይከተሉንና አባል ይሁኑ!

ኢትዮጵያ ውስጥ ትርፍ ለማግኘት ሲባል የማይደረግ ነገር የለም። በሰዎች ቁስል እንጨት በመስደድ የሚከብረው ብዙ ነው። ብዙው ሰው በችግርህ ውስጥ ገብቶ ነው ሀብትን የሚሰበስበው። ደህና ነገር ...
03/12/2025

ኢትዮጵያ ውስጥ ትርፍ ለማግኘት ሲባል የማይደረግ ነገር የለም። በሰዎች ቁስል እንጨት በመስደድ የሚከብረው ብዙ ነው። ብዙው ሰው በችግርህ ውስጥ ገብቶ ነው ሀብትን የሚሰበስበው። ደህና ነገር ሰርቶ አሳምኖ ለመለወጥ ከባድ የሆነው ለዚያ ነው። በርበሬው ላይ ሸክላ፣ ቅቤው ላይ ሙዝ፣ ጤፉ ላይ አሸዋ፣ ማሩ ላይ ስኳር ቀላቅሎ በሚሸጥ ማህበረሰብ ውስጥ ማደግ እንዴት ንጹህ ፈጠራ ያለበት ቢዝነስን ያበረታታል?

በነገራችን ላይ 95% የሚሆነው ሕይወታችን የሚመራው በድብቁ የአዕምሮ ክፍል ነው። ድብቁ የአዕምሮ ክፍል ውስጥ ያሉት ነገሮች ደግሞ በቀላሉ ልናስታውሳቸው የማንችልና ከተወለድን ጀምሮ በየቀኑ ሲነገሩና ወደ ውስጣችን ሲገቡ የነበሩና የተደጋገሙ ነገሮች ናቸው። እነዚህ ነገሮች ጥሩም መጥፎም ሊሆኑ ይችላሉ። የሚታወቁት ወደ ንቃተ ሕሊና ወይም አውቀን ወደምናደርግበት የአዕምሮ ክፍል በማምጣት ነው። አውቀን የምንመራው ሕይወት 5% ብቻ ነው።

እንግዲህ አስቡት፣ በየቀኑ ከልጅነት እስከ አሁን ይህንን ጽሑፍ እስከምናይበት ድረስ ስንት መጥፎ ነገር ገብቶ ይሆን? የምናደርገው ነገር በሙሉ የዚያ ነጸብራቅ መሆኑን አስቡ። በነገራችን ላይ ድብቁ የአዕምሮ ክፍል አንድን ነገር ጥሩ/መጥፎ ብሎ የመለየት ችሎታ የለውም። ያለው ችሎታ ተመሳሳይ የሆነ ኢነርጂ ያላቸውን ነገሮች አንድ ላይ የማቀናበር ችሎታ ነው።

ፍሮይድ እንደሚለው የተደበቁ ማንኛውም ስሜቶች አይሞቱም፣ በድብቁ የአዕምሮ ክፍል ውስጥ ተጠራቅመው ምቹ ሁኔታን ሲያገኙ በአስቀያሚ መልኩ ይወጣሉ እንጂ። እናስ ይህ አሁን እያየንው ያለንው ነገር በየወቅቱ ሳናስበው የተጠራቀመብን ነገር አይመስላችሁም? እናንተስ ምን ትላላችሁ? ወደ ውስጣችሁ ምን እያስገባችሁ ነው?

ለበለጠ መረጃ👇👇👇 1st Comment!

አብዛኛው ሰው "ልጄ እኔ ባደኩበት ሁኔታ እንዲያድግ አልፈልግም፣ እኔ ያለፍኩትን ትግል እንዲያይ አልፈልግም" ይላል። ይህ ግን ፈጽሞ ስህተት ነው። ምክንያቱም ምንም እንኳን በመከራ ውስጥ ብታ...
03/12/2025

አብዛኛው ሰው "ልጄ እኔ ባደኩበት ሁኔታ እንዲያድግ አልፈልግም፣ እኔ ያለፍኩትን ትግል እንዲያይ አልፈልግም" ይላል። ይህ ግን ፈጽሞ ስህተት ነው። ምክንያቱም ምንም እንኳን በመከራ ውስጥ ብታልፍ፣ ምንም እንኳን በትግልና በውጣውረድ እዚህ ብትደርስም እያንዳንዱ ያለፍክባቸው መንገዶች ጠቃሚ ናቸው። ሁሉንም መንገዶች ባይሆንም ከዚያ ጋር ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮችን ግን ማሳየት ይኖርብሃል።

አለበለዚያ ግን የምታሳድጋቸው ልጆች ሰነፎች፣ ውድቀትን የሚፈሩ፣ ችግርን የማይፈቱ፣ ትግልን የሚሸሹ፣ እንዲሁም በቀላሉ ተስፋ የሚቆርጡ እና የሚሸነፉ እንዲሆኑ ታደርጋቸዋለህ። ስለዚህም እነሱን በማይጎዳ መልኩ ውጣውረድን እንዲማሩ፣ ያለፍክበትን መንገድ እንዲያዩ አድርጋቸው። የዚያን ጊዜ አንተ ባትኖር እንኳን በቀላሉ ከሕይወት ጋር ተላምደውና ታግለው ራሳቸውን የሚያድኑ ይሆናሉ።

ጥብቅ ማስጠንቀቂያ፦
በምንም መልኩ ልጆችን በአካላዊ ቅጣት ማስተማር አይቻልም። ምክንያቱም አካላዊ ቅጣት የሚሰራው ቀጪው እስካለ ጊዜ ድረስ ከመሆኑም ባሻገር ቅጣቱ ሌላ አዲስ ባህርይን ሊያስተምር ይችላል። ስለሆነም በአካላዊ ቅጣት መልካም ባህርይ ይዣለሁ የሚል ወላጅ ለልጁ ይህንን እንዲያስተምር በፍጹም አንመክርም!

ጎበዝ ልጆችን ለማሳደግ፣
👇👇👇
የመጀመሪያ ኮመንት ይመልከቱ!

እውነቱ ቀላል ነው። ሰዎች አንተን የሚይዙህ እንደ አንተ ልብ ሳይሆን፣ እንደ ራሳቸው ማንነት ነው።ለዚህ ነው ከክህደቱ ይልቅ፣ ከሰዎች ብዙ መጠበቅ (Expectation) የበለጠ የሚጎዳው። ም...
02/12/2025

እውነቱ ቀላል ነው። ሰዎች አንተን የሚይዙህ እንደ አንተ ልብ ሳይሆን፣ እንደ ራሳቸው ማንነት ነው።

ለዚህ ነው ከክህደቱ ይልቅ፣ ከሰዎች ብዙ መጠበቅ (Expectation) የበለጠ የሚጎዳው። ምክንያቱም ያ ቅጽበት፣ እነሱ አንተ ተስፋ እንዳደረግከው ዓይነት ሰዎች እንዳልሆኑ የምትረዳበት ጊዜ ነው።

የአንተ ታማኝነት ስለ አንተ ማንነት ይናገራል፤ የእነሱም ታማኝነት ስለ ራሳቸው ይናገራል። እነዚህ ሁለት ነገሮች ሁሌም ላይጣጣሙ ይችላሉ፤ ይህ ግን የአንተን ዋጋ የሚቀንስ አይደለም።

ልብን መጠበቅ ማለት ጨካኝ መሆን ማለት አይደለም። ይልቅስ ሰዎችን ከአቅማቸው በላይ መውደድን ማቆም መማር ማለት ነው። ለማንም ብለህ ራስህን ማሳነስ የለብህም።

ማወቅ ያለብህ ነገር ቢኖር፣ መልሶ ሊወድህ የሚችለው ማን እንደሆነ ብቻ ነው።

ቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ፦
👇👇👇

ከምቾት ቀጠናህ (Comfort Zone) ውጣ! የሰፈር ልጅነት ትልቁ ወጥመድ "መጠራራት" ነው። ጓደኞችህ ዘና ብለው ሲስቁ ማየት ደስ ይላል፤ ነገር ግን አብረሃቸው ከዋልክ ህይወትህም እዚያው ...
02/12/2025

ከምቾት ቀጠናህ (Comfort Zone) ውጣ!

የሰፈር ልጅነት ትልቁ ወጥመድ "መጠራራት" ነው። ጓደኞችህ ዘና ብለው ሲስቁ ማየት ደስ ይላል፤ ነገር ግን አብረሃቸው ከዋልክ ህይወትህም እዚያው ጋር ይቆማል።

ምስሉን ተመልከት... ወደ ኋላ የቀሩት "ተመችቷቸው" ነው፤ ወደ ፊት የሚሄደው ግን "ተጨንቆ" ነው። ልዩነቱ ይሄ ነው። ስኬታማ ለመሆን አንዳንድ ጊዜ ለጓደኞችህ "መጥፎ/ኩሩ" መስለህ መታየት አለብህ። ጊዜ ሲያልፍ ግን ውጤትህ መልስ ይሰጣቸዋል።

መንገዱ የብቸኝነት ነው፤ ግን ፍሬው ጣፋጭ ነው! 💪🏾🇪🇹

ሙሉ ጽሑፉ ቴሌግራም ቻናላችን ላይ አለላችሁ፤ የመጀመሪያ ኮመንት ላይ!
👇👇👇

Love this MAN!
29/11/2025

Love this MAN!

ከተወለድክበት ሠፈር ውጣ⁉️አንድ በስፋት የሚነገር እና በተጨባጭም ብዙ ጊዜ የሚስተዋል ጉዳይ አለ። በተወለድክበት ሰፈር ከቆየህ ወይም ለብዙ ጊዜ አንድ ሰፈር ከኖርክ ሀብታም ወይም ስኬታማ የ...
28/11/2025

ከተወለድክበት ሠፈር ውጣ⁉️

አንድ በስፋት የሚነገር እና በተጨባጭም ብዙ ጊዜ የሚስተዋል ጉዳይ አለ። በተወለድክበት ሰፈር ከቆየህ ወይም ለብዙ ጊዜ አንድ ሰፈር ከኖርክ ሀብታም ወይም ስኬታማ የመሆን እድልህ የጠበበ ነው የሚል። ይህ ምን ያህል እውነት ነው? ከሥነልቦና አንጻር እንዴት ይታያል?

በእንግሊዘኛው "Hometown Trap" (የትውልድ ቦታ ወጥመድ) ሊባል ይችላል። በተለይም እንደ አዲስ አበባ፣ እና ሌሎች ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ተወልደው ያደጉ ልጆች፤ ከክፍለ ሀገር ወደ ከተማ ከገቡት አንጻር ሲታዩ በኢኮኖሚ የመቅደምና የመለወጥ እድላቸው ዝቅ ያለ መስሎ ይታያል።

ለዚህ "የሰፈር ልጅነት ወጥመድ" ምክንያቱ እርግማን ሳይሆን ተጨባጭ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ምክንያቶች አሉት። ዋና ዋናዎቹን እንደሚከተለው እናቀርብላችኋለን፡-

1. የምቾት ቀጠና፤

ይህ ዋነኛው ምክንያት ነው። አንድ ሰው የተወለደበት ሰፈር ሲኖር፡-

▫️መሰረታዊ ፍላጎት ተሟልቷል፡ በከተማ የሚኖሩ ልጆች አብዛኛውን ጊዜ የሚኖሩበት የቤተሰብ ቤት አላቸው፣ ምግብ ይቀርባል፣ እና መጠለያ የማግኘት ጭንቀት የለባቸውም።

▫️የህልውና ስጋት የለም (Lack of Survival Mode): ከሌላ ቦታ የመጣ ሰው "ካልሰራሁ አልኖርም" ወይም "ቤት ኪራይ መክፈል አለብኝ" በሚል የህልውና ስጋት (Survival instinct) በከፍተኛ ወኔ ይሰራል። የሰፈር ልጅ ግን ያ ስጋት ስለሌለበት ለመስራት አይገደድም፤ "ነገም ሌላ ቀን ነው" በሚል መንፈስ ይዘናጋል።

2. የማህበራዊ ይሉኝታ እና የ"ግል-ገጽታ" ቀውስ፤

የሰፈር ልጅ በሰፈሩ ሰው ዘንድ የተገነባ ማንነት (Image) አለው። ይህ ማንነት ለስራ እንቅፋት ይሆናል፡-

▫️ዝቅ ብሎ ለመስራት መፍራት፡ አንድ የሰፈር ልጅ ጉልበት ስራ ወይም ንግድ ለመጀመር ሲያስብ "ሰፈሩ ምን ይለኛል?"፣ "እከሌ እኮ እንዲህ ሲሆን አየንው ይሉኛል" የሚል ፍራቻ አለበት።

▫️የ"አራዳ" አስተሳሰብ ጫና፡ በተለይ በከተማ የተወለዱ ልጆች ላይ ስራን ከማክበር ይልቅ ዘና ብሎ መታየትን እንደ "አራዳነት" የመቁጠር የተሳሳተ ስነ-ልቦና አለ። ቱታ ለብሶ ከመስራት ይልቅ፤ አምሮ ታይቶ መዋልን ይመርጣሉ። (ይህ ሁሉንም አያጠቃልልም፣ ግን በአብዛኛው)

3. የጓደኛ ተጽእኖ፤

በልጅነት አብረው ያደጉ ጓደኛሞች በአንድ ሰፈር ሲሰባሰቡ ለእድገትና ለመለወጥ ሳይሆን ለጊዜ ማሳለፊያ ቅድሚያ ይሰጣሉ፡-

▫️አንዱ ለመለወጥ ወይም ጠንክሮ ለመስራት ሲሞክር ሌሎቹ ሊያሳቅቁት ይችላሉ ("ምን አዲስ ነገር ተገኘ"፣ "ዝም ብለህ አትፍጨርጨር" በሚል መንፈስ ያጣጥሉታል)።

▫️የጋራ ልምዳቸው (ማውራት፣ መዝናናት፣ ሻይ ቡና ማለት) ጊዜን የሚገድል እንጂ ገንዘብ የሚያስገኝ አይሆንም። ከዚህ አዙሪት ወጥቶ ማሰብ ይከብዳል።

4. እድልን አለማስተዋል፤

ይህ "Familiarity breeds contempt (አብሮ መዋል ያናንቃል እንደማለት)" እንደሚባለው ነው።

▫️አንድ ሰው በለመደው አካባቢ እድሎችን ማየት ይሳነዋል። ለምሳሌ፡- አንድ ሰፈር ውስጥ ለዓመታት የኖረ ሰው ያ አካባቢ ለንግድ ያለውን ክፍተት ላያስተውል ይችላል።

▫️አዲስ የመጣ ሰው ግን አካባቢውን በአዲስ አይን ስለሚያየው የት ቦታ ምን ቢሰራ እንደሚያዋጣ በፍጥነት ይረዳል። ለሰፈር ልጅ "የቆሻሻ መጣያ" የሚመስለው ቦታ፣ ለአዲሱ ሰው "የቢዝነስ ቦታ" ሆኖ ይታየዋል።

5. የማህበራዊ ወጪ መብዛት፤

የሰፈር ልጅ በሰፈሩ ታዋቂ ስለሆነ ማህበራዊ ግዴታው ይበዛበታል፡-

▫️ለቅሶ፣ ሰርግ፣ ክርስትና፣ የጓደኛ መዝናኛ ወጪዎች ይበዙበታል።

▫️ገንዘብ ቢያገኝ እንኳን "ጓደኞቹን የመጋበዝ" ግዴታ ያለበት ይመስለዋል፤ በዚህም የተነሳ የሚቆጥበው ገንዘብ ይቀንሳል። ማንም የማያውቀው ሰው ግን እነዚህ ግዴታዎች ስለሌሉበት ገንዘቡን ለኢንቨስትመንት ያውለዋል።

በአጠቃላይ በተወለዱበት ቦታ አለመለወጥ የሚመጣው ከአቅም ማነስ ሳይሆን፣ ከአካባቢው ለውጥ አለመፈለግ እና ግለሰቡም ከለመደው ማንነት ለመውጣት ካለመፈለግ ነው። ስኬታማ የሆኑ የሰፈር ልጆች አብዛኛውን ጊዜ አስተሳሰባቸውን ከሰፈሩ ያላቀቁ ወይም ደግሞ ሰፈሩን ለቀው የወጡ ናቸው።

አንድ ሰው ከሰፈሩ ሳይወጣ እንዴት ስኬታማ መሆን ይችላል?

በቀጣይ እንገናኝ።

©ሳይክአዲስ

እስከዚያው፣ የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቀሉ!
👉 https://t.me/psychaddis

28/11/2025
https://youtu.be/BZhxgr3En1U
26/11/2025

https://youtu.be/BZhxgr3En1U

ብዙ ወንዶች ሴቶችን የሚያጡት በመጥፎ ባህሪያቸው ሳይሆን፣ "በተናገሩት የተሳሳተ ቃል" እንደሆነ ያውቃሉ? ለሴት ልጅ ፍቅርህን ስትገልጽላት፣ ሳታውቀው "እኔ ደካማ ነኝ፣ አትውደጂኝ" የሚ....

"ከወንበዴ ይልቅ ሞኝ (Stupid) ሰው አደገኛ ነው!" - ፕሮፌሰር ካርሎ ቺፖላ (ፌስቡክ ላይ ለሚሰጡ አላስፈላጊ "ኔጌቲቭ" ኮመንቶች የተሰጠ ሳይንሳዊ ማብራሪያ) 🤔 በጎ ነገር ተሰርቶ ሲያ...
26/11/2025

"ከወንበዴ ይልቅ ሞኝ (Stupid) ሰው አደገኛ ነው!" - ፕሮፌሰር ካርሎ ቺፖላ

(ፌስቡክ ላይ ለሚሰጡ አላስፈላጊ "ኔጌቲቭ" ኮመንቶች የተሰጠ ሳይንሳዊ ማብራሪያ) 🤔

በጎ ነገር ተሰርቶ ሲያዩ፣ "እንኳን ደስ አለህ ወይም ጥሩ ነው" ማለት ሲገባቸው ስድብ የሚጀምሩ፣ ለሀገር የሚጠቅም ፕሮጀክት ሲመረቅ "ምን ያደርጋል?" ብለው የሚያጣጥሉ፣ ወይም ዝም ብሎ ካለአንዳች ምክንያት ኮመንት ላይ መርዝ የሚረጩ ሰዎች አይታችሁ "ለምን ግን?" ብላችሁ ታውቃላችሁ?

ጣሊያናዊው የታሪክ ምሁር እና ኢኮኖሚስት ካርሎ ቺፖላ የሰው ልጆችን በ4 ይከፍላቸዋል። ይህንን ቲዮሪ ስታውቁ፣ ፌስቡክ ላይም ሆነ በማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ ለሚያጋጥማችሁ "ከንቱ" አስተያየት መልስ መስጠት ታቆማላችሁ።

ቺፖላ ሰዎችን በእንቅስቃሴያቸው መሰረት እንዲህ ይከፍላቸዋል፡-

1. ብልህ (Intelligent): ይህ ሰው ድርጊቱ ለራሱም ጥቅም ይሰጣል፤ ለሌሎችም ይተርፋል።

ምሳሌ፡ ፌስቡክ ላይ ጠቃሚ መረጃ ሼር የሚያደርግ፣ ሌላውም እንዲያውቅ የሚጥር። (Win-Win)

2. ወንበዴ/ሌባ/ አጭበርባሪ (Bandit): ይህ ሰው የራሱን ጥቅም ለማግኘት ሲል የሌላውን ሰው ጥቅም ይጎዳል።

ምሳሌ፡ ቦርሳ ቀማኛ፣ ወይም የሌላውን ንብረት የሚዘርፍ። እነዚህ ሰዎች ክፉ ቢሆኑም፣ አላማ አላቸው (የራሳቸውን ጥቅም)። ስለዚህ "Logic" አላቸው ማለት ነው። የምታጣው አንተ እንጂ እነሱማ ያተርፋሉ።

3. የዋህ/ፋራ (Helpless): ይህ ሰው ራሱን እየጎዳ ለሌላው ይጠቅማል።

ምሳሌ፡ ተበድሮ የሚያበድር፣ ራሱን መስዋዕት የሚያደርግ። (Lose-Win)

4. ሞኝ/Stupid (The most dangerous one): ⚠️

የቺፖላ ቲዮሪ ዋናው ነጥብ እዚህ ላይ ነው። "Stupid" ወይም ሞኝ ማለት ምን ማለት ነው? "ሞኝ ማለት፡ ለራሱ ምንም አይነት ጥቅም ሳያገኝ (እንዲያውም ኪሳራ እያወጣ)፣ በሌሎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሰው ነው።"

ወደ ፌስቡክ እንምጣ...

አንድ ሰው ጥሩ ነገር ፖስት አድርጎ፣ አንዱ መጥቶ ኮመንት ላይ ሲሳደብ ይታያችሁ።

▫️ተሳዳቢው ምን አተረፈ? ዳታው አለቀ፣ ጊዜው ባከነ፣ የራሱን "mood" አበላሸ፣ በሰው ዘንድ ተጠላ። (ለራሱ ኪሳራ ነው)።

▫️ሌላውን ጠቀመ? በፍጹም! የፖስቱን ባለቤት አስከፋ፣ የኮመንት አንባቢዎችን ረበሸ። (ሌላውንም ጎዳ)።

ቺፖላ እንደሚለው፣ "ከወንበዴ ይልቅ ሞኝ ሰው አደገኛ ነው!" ይላል። ምክንያቱም ወንበዴው/ሌባ ሊሰርቅህ ሲመጣ ቢያንስ የራሱን ጥቅም ስለምታውቅለት ልትጠነቀቅ ትችላለህ። "ሞኙ" ግን የሚመራው በምክንያት (Logic) ሳይሆን በከንቱነት ስለሆነ መቼ እና እንዴት እንደሚያበላሽ አይታወቅም።

መፍትሄው? ቺፖላ አራተኛው ህጉ ላይ እንዲህ ይላል፡- "ብልህ ሰዎች፣ ከሞኞች ጋር መከራከር የሚያመጣውን አደጋ ሁሌም ይዘነጉታል!"

ስለዚህ ወዳጄ... ፌስቡክ ላይ ስድብ፣ ጥላቻ እና አሉታዊ ነገር የሚረጩ ሰዎች "ወንበዴ/ሌባ/ቀማኛ" እንኳን አይደሉም። ወንበዴማ ቢያንስ ለራሱ ያተርፋል! እነዚህ ግን ለራሳቸውም ሳይሆኑ ለሰውም ሳይሆኑ የሚኖሩ የቺፖላ "Stupid" ካታጎሪ ተጠቂዎች ናቸው።

መልስ አትስጣቸው፣ አትከራከራቸው።

ከእነሱ ጋር መከራከር ማለት፣ አንተም ጊዜህን እያጠፋህ (እየተጎዳህ) ለእነሱም ምንም ሳትጠቅም ወደ "ሞኝ" ካታጎሪ መውረድ ማለት ነው።

ዝም ብለህ እለፋቸው፣ ወይም "Block" አድርገህ አለምህን አድን!

©ሳይክአዲስ

በየጠዋቱ ለራስህ የምትነግራቸው 6 አበረታች አባባሎች! 1. እግዚአብሔር ሁሌም ከእኔ ጋር ነው! ዛሬ ምንም ቢፈጠር ብቻህን እንዳልሆንክ አስታውስ። እግዚአብሔር ይመለከትሃል፣ አካሄድህን ይመራ...
25/11/2025

በየጠዋቱ ለራስህ የምትነግራቸው 6 አበረታች አባባሎች!

1. እግዚአብሔር ሁሌም ከእኔ ጋር ነው!

ዛሬ ምንም ቢፈጠር ብቻህን እንዳልሆንክ አስታውስ። እግዚአብሔር ይመለከትሃል፣ አካሄድህን ይመራል እንዲሁም ራስህን የመግዛት አቅምህን (Discipline) ያጠነክራል። ህይወት በትግል፣ በፈተና ወይም በጥርጣሬ ስትፈትሽህ፤ እሱ ከአንተ ጋር እንደሆነ እመን። ይህ እምነት ለዕለት ተዕለት ትግልህ (Hustle) ድፍረት ይስጥህ፤ በአላማህ ላይ እንድታተኩርም ይርዳህ። መለኮታዊ ድጋፍ እንዳለህ አውቀህ ወደ ማንኛውም ስራ ግባ።

2. እችላለሁ!

ማንኛውንም ፈተና ለማለፍ የሚያስፈልገው ብቃት አለህ። ስንፍናን፣ ፍርሃትን ወይም ትኩረት የሚሰርቁ ነገሮችን አሸንፍ፤ ምክንያቱም "እችላለሁ" ማለት ከቃላት በላይ ነው—የአእምሮ ጥንካሬንና ሥነ-ምግባርን የሚገነባ አስተሳሰብ ነው። እችላለሁ ማለት መታበይ አይደለም። ትግሉ ከባድ ሊሆን ይችላል፣ እንቅፋቶች ይኖራሉ፣ ነገር ግን እያንዳንዱ ወደፊት የሚራመድ እርምጃ ችሎታህን ያረጋግጣል። በራስህ ላይ እምነት ይኑርህ፣ ዝግጅትህን እመን፣ ዛሬውኑ ያለምንም ማመንታት ወደ ግብህ ተንቀሳቀስ።

3. እኔ ምርጡ ነኝ!

የላቀ ውጤት (Excellence) በስራ የሚገኝ እንጂ የሚሰጥ አይደለም። ከትላንት የተሻልክ ለመሆን በየቀኑ ትጋ። ሌሎች ሊጠራጠሩህ፣ ወደ ታች ሊጎትቱህ ወይም ትኩረትህን ሊሰርቁ ይሞክሩ ይሆናል፤ አንተ ግን ይህን እንደ መነሳሳት ተጠቀምበት። በትጋትህ፣ በክህሎትህና በባህሪህ ጎልተህ ውጣ። በራስህ ዋጋ እመን፣ ትህትና ይኑርህ፣ በራስ መተማመንህም ግቦችህን እንድታሳካ ይምራህ።

4. እኔ አሸናፊ ነኝ!

ማሸነፍ የሚጀምረው ከአዕምሮ ነው። ቀንህን አቅድ፣ ልማዶችህን ተቆጣጠር፣ እንዲሁም በጽናት ተግብር። ህይወት ትፈትናለች፤ ውድቀት፣ እምቢታ እና መከራዎች የጉዞው አካል ናቸው። አንተ ግን እነሱን ለማለፍ ነው የተፈጠርከው። መንፈሳዊ ጥንካሬ እና ራስን መግዛት በሁሉም የህይወት ዘርፍ ለድል ያበቁሃል። ዛሬ ትናንሽ ፈተናዎችን በማሸነፍ እና ወደ ትላልቅ ግቦችህ በመጠጋት ላይ አተኩር።

5. ዛሬ የእኔ ቀን ነው!

ቀኑን በቁጥጥርህ ስር አውለው፤ የማንንም ፈቃድ ወይም "ትክክለኛ ጊዜ ይመጣል" ብለህ አትጠብቅ። እያንዳንዱ ቀን ለማደግ፣ ስራህን ለመቆጣጠር እና አቅም ለመገንባት እድል ነው። ዛሬ ነገ ማለት (Procrastination) እና ፍርሃት ሊያቆሙህ ይሞክራሉ። ነገር ግን ቀኑ ምን መምሰል እንዳለበት የምትወስነው አንተ ነህ። ተግባርህ ከአላማህ ጋር ይሂድ፣ ወሳኝ እርምጃዎችን ውሰድ፣ ለጸጸትም ቦታ አትስጥ። ይህን ቀን እንዳንተ አድርጎ የሚጠቀምበት የለምና ወሳኝ አድርገው።

6. ፈተናዎችን ድል አደርጋለሁ!

እያንዳንዱ እንቅፋት ይበልጥ ለመጠንከር የሚገኝ እድል መሆኑን አውቀህ ቀኑን ጀምር። ህይወት ችግሮችን ትወረውራለች፦ ያልተጠበቁ ችግሮች፣ መሰናክሎች ወይም አስቸጋሪ ሰዎች ሊያጋጥሙህ ይችላሉ፤ ነገር ግን አንተ እነሱን ለማሸነፍ የሚያስችል ጥንካሬ እና ዲሲፕሊን አለህ። አእምሮህ ንቁ፣ መንፈስህ በእምነት የጸና፣ ተግባርህም ትኩረት ያደረገ ይሁን። እያንዳንዱን ፈተና ወደ ትልቅ ግብህ እንደሚያደርስ መወጣጫ ተጠቀምበት፤ ሊያቆሙህ የሞከሩትን ነገሮች ድል እንዳደረግክ አውቀህ ቀኑን ጨርስ።

ወዳጄ ሆይ፣

እያንዳንዱ ቀን አእምሮህ፣ ዲሲፕሊንህ እና መንፈስህ የሚፈተኑበት የጦር ሜዳ መሆኑን አስታውስ። ጠዋትህን በእነዚህ ማረጋገጫዎች (Affirmations) ስትጀምር ለተግባርህ፣ ለትኩረትህ እና ለድሎችህ መንገድ ትከፍታለህ። በእምነት ተናገራቸው፣ በአላማ ኑራቸው፣ የዕለት ተዕለት ትግልህንም ይምሩት፦

1. እግዚአብሔር ሁሌም ከእኔ ጋር ነው!
2. እችላለሁ!
3. እኔ ምርጡ ነኝ!
4. እኔ አሸናፊ ነኝ!
5. ዛሬ የእኔ ቀን ነው!
6. ፈተናዎችን ድል አደርጋለሁ!

እነዚህን ቃላት ከአንተ ጋር ያዝ፣ በራስ መተማመንህን ይገንቡልህ። ቀኑን የመቆጣጠር፣ ችግሮችን የማሸነፍ እንዲሁም በአዕምሮ፣ በመንፈስና በአካል የመጠንከር ኃይል እንዳለህ ለራስህ አስታውስ።

እነዚህን ማረጋገጫዎች በየጠዋቱ ስታውጅ፣ ራስን የገዛና የማይበገር ጠንካራ ሰው አስተሳሰብን ትገነባለህ።

©ሳይክ አዲስ

በሚመችህ፣
ዩቲዩብ፣ ቴሌግራም እና ቲክቶክ ላይ ተከተለን!

Address

AAU
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Psych Addis - ሳይክ አዲስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Psych Addis - ሳይክ አዲስ:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category