29/12/2025
ስለ እርግዝና ይህንን አዲስ ጥናት ልብ ይበሉ!
የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ (Columbia University) ያካሄደው አስገራሚ ጥናት በእርግዝና ወቅት የሚፈጠር ከፍተኛ ጭንቀት በሚወለደው ሕፃን ጾታ ላይ ተጽእኖ እንዳለው አረጋግጧል።
ጥናቱ ምን አዲስ ነገር አገኘ?
▫️ወንዶች ለጭንቀት ይበልጥ ተጋላጭ ናቸው፤
በጭንቀት የተሞላ እርግዝና ሲኖር፣ ወንድ ፅንሶች (Male fetuses) ባላቸው ስነ-ህይወታዊ ተፈጥሮ ምክንያት የመቋቋም አቅማቸው ዝቅተኛ ነው። በዚህም ምክንያት ከመወለዳቸው በፊት የመቋረጥ ዕድላቸው ሰፊ ነው።
▫️ሴቶች ጠንካራ ናቸው፤
በአንፃሩ ሴት ፅንሶች አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እና የናትን ጭንቀት ተቋቁሞ የመትረፍ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው።
በቁጥር ሲታይ፤
▫️ከፍተኛ አካላዊ ጭንቀት የነበረባቸው እናቶች ከወለዱት ውስጥ 31% ብቻ ወንዶች ሲሆኑ፣
▫️ጤናማና ሰላማዊ እርግዝና ያሳለፉ እናቶች ጋር ግን ይህ ቁጥር ወደ 56% ከፍ ይላል።
ይህ የሚያሳየው እናትየዋ በጭንቀት ውስጥ በምትሆንበት ጊዜ ሴት ልጅ የመውለድ ዕድሏ እንደሚጨምር ነው። ሳይንቲስቶች ይህንን ሁኔታ፣ ተፈጥሮ ሴቶችን አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እንዲቋቋሙ አድርጋ የፈጠረችበት መንገድ (Evolutionary response) እንደሆነ ይገምታሉ።
ጤናማ እና ደስተኛ እርግዝና እንዲሆንልዎ የህክምና ባለሙያዎች ምክር አይለይዎ! ❤️
መረጃው ለሌሎች እህቶች እንዲደርስ ሼር (Share) ያድርጉ! 🔄