World Class Quality Award Organization

World Class Quality Award Organization award for an outstanding achievements that has saved the world and its peoples

24/04/2026

ተቀጥራችሁ የምትሰሩ ሰራተኞች ሁሉ ልታውቁት የሚገባ
: አዲስ የሰበር አቋም!
🔑🔑🔑🔑🔑
ለ5 ተከታታይ ቀናት ያለፈቃድ ከስራ የቀረ ሰራተኛ
ያለማስጠንቀቂያ ከስራ መሰናበት ያለበት ስለመሆኑ
በ7 ዳኞች የተሰጠ ትርጉም!

1. ሰበር በ7 ዳኞች መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በሰ/መ/ቁ 271726 የተሰጠው አስገዳጅ ትርጉም ከዚህ በፊት በሰ/መ/ቁ 249795 ሰራተኛው ለተከታታይ 5 ቀናት ቢቀር እንኳን ከስራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን አሰሪ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የስራ ውልን ማቋረጥ እንደማይችል ተይዞ የነበረውን የሰበር አቋም የቀየረ ብሎም በሰራተኞች የስራ ደህንነት ላይ አሉታዊ ውጤት የሚኖረው ነው፡፡

2. ሰበር በ7 ዳኞቹ በያዘው አዲስ አቋሙ ሰራተኛ ያለፈቃድ ለ5 ተከታታይ ቀን ከቀረ ያለማስጠንቀቂያ ማሰናበትን የሚፈቅድ ይዘት በአዋጅ 1156 ላይ የለም ብሏል ፡፡

3. ይህ አዲስ አቋም የአንቀጽ 27 (1)(ለ) ይዘት በዚህ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጭ የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው በስድስት ወር ውስጥ ለ5 ቀናት ከስራ መቅረት ለአሰሪው የስራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማቋረጥ ያስችለዋል የሚል ነው።

ነገር ግን የዚህ አንቀፅ ይዘት በግልፅ የሚያመለክተው አሰሪው የሰራተኛውን ከስራ መቅረት ለስራ ስንብት መነሻ ሊያደርግ የሚችለው ሰራተኛውን ለማረም የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ስለመሆኑ ብቻ ነው።

ከዚህ አንጻር የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ ሳይደርሰው ከስራ ቀርቷል በሚል የስራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ለማሰናበት የህግ መሰረት አለ ወይ? የሚለው ትልቅ ጥያቄ ነው፡፡

4. የሰበር ሰሚ ችሎቱ በ7 ዳኞች አዲስ ለሰጠው አስገዳጅ ትርጉም መነሻ ያደረጋቸው አመክንዮዎች የሚከተሉት ናቸው፡-

4.1. በአንቀጽ 27 (1)(ለ) ሰራተኛው በተከታታይ ለ5 ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ፈቃድም ሆነ እረፍት ሳይሰጠው ከስራ ቢቀር አሰሪው የስራ ውሉን ያለ ማስጠንቀቂያ ከማቋረጡ በፊት ለሰራተኛው የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ አይደነገግም፡፡ (የ7 ዳኞች አዲስ አቋም)

4.2. በአዋጁ አንቀጽ 27(1)(2) ላይ የተመለከተው የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ ሰራተኛው ያለፈቃድ ከስራ ከቀረ በኋላ ወደ ስራው ሲመጣ ለወደፊት ተመሳሳይ ጥፋት እንዳፈጽም ተገልጾ የሚሰጥ ማስጠንቀቂያ እንደመሆኑ መጠን ለ5 እና ተከታታይ ያለ ፈቃድ ለቀረ ሰራተኛ ጥፋቱን እንዳይደግም በመግለጽ ሰራተኛው ከስራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን በአንቀጽ (27)(1)(ለ) ላይ የተመለከተውን ማስጠንቀቂያ መስጠት የሚቻል አይደለም፡፡

ለዚህ ድምዳሜ ምክንያት በሚል የተሰጠው ደሞ ሰራተኛው ከ5 ተከታታይ ቀናት በላይ ከቀረ በኋላ ሰራተኛውን አግኝቶ ያለፈቃድ ከስራ ከመቅረት ጥፋቱ እንዲታረም አስሪው የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ ለመስጠት አሰሪው እድል ሊያገኝ አይችልምና የሚል ነው፡፡

4.3. ከዚህም ባሻገር የጥፋት ተግባሩን እየቀጠለ ያለንና ገና ወደ ስራ ገበታው ያልተመለሰን ሰራተኛን ጥፋቱን እንዳይደግም ወይም ለወደፊቱ ከጥፋቱ እንዲታረም ተገልጾ የጽኁፍ ማስጠንቀቂያ (Warning in writing) እንዲሰጠው አሰሪውን ማስገደድ ከስረ አመክንዩ (logic) አኳያ ሲታይም አሳማኝነት ያለው አይደለም፡፤ የሚቻል አይደለም የሚለውን ነጥብ አንስተዋል፡፡

4.4. በተጨማሪም ለተከታታይ 5 ቀናት ያለ በቂ ምክንያት ከስራ መቅረት ሌላ ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ ሳይኖር አሰሪው ያለማስጠንቀቂያ የስራ ውልን እንዲያቋርጥ የሚያስችለው ስለመሆኑ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከመታወጁ በፊት በስራ ላይ በነበረው አዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 27(1)(ለ) በግልጽ ተደንግጎ የሚገኝ ነው አዋጅ 1156/2011 ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ስለቀረ ሰራተኛ ሊኖው ስለሚገባ ውጤት ምንም አይልም የሚለውንም አንስተዋል፡፡

4.5. በሌላ በኩል ህጉ ግልጽነት ሲጎድለው ጠቅላላን የህጉን ይዘትና አቀራረጽ መሰረት በማድረግ ክፍተቱን በትርጉም መሙላት አስፈላጊ ስለመሆኑ አንስተው፡፡ የአዋጅ 1156 አንዱ አላማ አሰሪና ሰራተኛ የጋራ ራእይ ኖሯቸው ለድርጅቱ ምርታማነት እንዲሰሩ ስለመሆኑ ሰራተኛ የስራ ሰአትና የስራ ዲሲፒሊን አክብሮ ስራውን የመሰይሰራ ከሆነ አሰሪው ተወዳዳሪ ሊሆን አይችልም የሚለውም ለአዲሱ የ7 ዳኞች የሰበር አቋም ሌላ መነሻ ሆኗል፡፡

4.6. በመጨረሻም ሰበር የ1156ን የረቂቅ ህጉን አጭር ማብራሪያና ሀተታ ዘምክንያት ለአዲስ አቋሙ መነሻ ማድረጉ ተመልክቷል፡፡

5. እነኚህን ከላይ የተመለከቱትን ምክንያቶችን በመዘርዘር በሰ/መ/ቁ 249795 ሰበር ይዞት የነበረውን ሰራተኛው በተከታታይ ከ5 ቀናት በላይ ለሆነ ጊዜ ቢቀር እንኳን አሰሪው ሰራተኛው ከስራ ለቀረበት ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የስራ ውልን ማቋረጥ እንደማይችል ሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ ትርጉም ለውጦ በ7 ዳኞች መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በሰ/መ/ቁ 271726 በሰጠው አዲስ አስገዳጅ ትርጉም መሰረት የአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27/1/ለ ድንጋጌ ሰራተኛው በዚሁ አዋጅ ከተመለከቱ እረፍቶችና ልዩ ልዩ ፈቃዶች ውጪ ለአምስት ተከታታይ የስራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከስራ ላይ ከቀረ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የስራው ውልን ያለ ማስጠንቀቂያ ማቋረጥ ይችላል የሚል አቋም ወስዷል፡፡

ስለሆነም ሰራተኞች ይህን አዲስ የሰበር 7 ዳኞች አስገዳጅ ትርጉም መገንዘብና መጠንቀቅ ያስፈልጋቸዋል።

Legal Eagles Law Firm LLP Seble Asefa #ጠበቃ #ሕግምክር #ጠበቃሰብለአሰፋ

23/04/2026

ቀን   06 /  08  / 2018 ዓ. ምአስቸኳይ ክፍት የስራ  ቦታ ማስታወቂያ / የሙሉ_ጊዜ_ሰራተኞች /1.  የምዘና ዘርፍ ሥራ አስኪያጅ    የት/ት ደረጃ፡- PH.D in any field...
14/04/2026

ቀን 06 / 08 / 2018 ዓ. ም
አስቸኳይ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ / የሙሉ_ጊዜ_ሰራተኞች /
1. የምዘና ዘርፍ ሥራ አስኪያጅ
የት/ት ደረጃ፡- PH.D in any field የ15 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡ የስራው ጊዜ፡- የሙሉ ጊዜ ቋሚ ሰራተኛ
ደሞዝ፡- የመነሻ ደሞዝ ከ35,500/40,500 ብር እንደብቃታቸው እድሜ፡- ከ35 - 60 ብዛት፡-1 ፆታ፡- አይለይም
2. የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ
የትምህርት ደረጃ፡- በሥራ አመራር መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ የ5 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡ በሥራ አመራር መስኮች በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ የ3 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡ ከፍተኛ የኮምፒውተር ጽሁፍ ችሎታ ያላቸው፡፡
ደሞዝ:- ደሞዝ ከ30,500/35,500 ብር በቅደም ተከተል እንደ ደረጃቸው እድሜ፡- ከ30 - 45 ብዛት፡- 4 ፆታ፡- አይለይም
3. የጥራት ሽልማት ምዘና ሙያተኛ :- የጤና ፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ፣ የትምህርት ፣ ለግብር ፣ ለአገልግሎት ሰጪ እና የንግድ ዘርፎች፡፡
ተፈላጊ የቋሚ ሰራተኛ ብዛት፡- 18 ተፈላጊ የ2 ወራት በኮንትራት ሰራተኞች ብዛት፡-17
የመዛኞች የስራ መደቦች ተፈላጊ ብቃቶች/መስፈርቶች
የመጀመሪያ ዲግሪ ላለቸው በተመረቁበት ሙያ የ10 ዓመታት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡
በዘርፋቸው ማስተርስ ዲግሪ ያላቸው እና በተማሩበት ሙያ የ5 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡
PH.D in any field እና በተማሩበት ሙያ የ5 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡
PH.D in any field እና በተማሩበት ሙያ የ15 ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው፡፡
የመነሻ ደሞዝ፡- 30,500 / 35,500 / 40,500 / 45,500 ብር በቅደም ተከተል እንደ ደረጃቸው
ከፍተኛ የእንግሊዘኛ ማንበብና ተንትኖ መፃፍ ችሎታ ያላቸው፡፡ እድሜ፡- ከ30-65 ፆታ፡- አይለይም
ከፍተኛ የኮምፒውተር ጽሁፍ ችሎታ ያላቸውና የምዘና ስራዎች በላፕቶፕ መስራትና ማቅረብ የሚችሉ፡፡
የምዘና ስራ ዘርፍ አመልካቾች በድርጅታችችን ለዘርፉ የተዘጋጀውን ስልጠና መውሰድ ግዴታ ሲሆን ለስልጠናውም በስልጠናው ሒደት ተቋማችን የሚከፍላችሁ ክፍያ አይኖርም ከሰልጣኞቹም ክፍያ አይቀበልም፡፡
ከስልጠናው በኋላ ፈተና የምንሰጥ ሲሆን የላቀ ውጤት ያመጡት በያመለከቱበት ደረጃ ይቀጠራሉ፡፡
4. የሽልማት እጩ ምልመላ የመስክ ሰራተኛ
የትምህርት ደረጃ፡- በማንኛውም ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ፡፡ ብዛት፡- 42 እድሜ፡- ከ25 - 45 ፆታ፡- ወንድ
ዲፕሎማ እና 12/10ኛ ክፍል ላጠናቀቁት የተፃፈ የስራ ልምድ ያላቸው፡፡ ከፍተኛ የንግግርና የማስረዳት ችሎታቸው ያላቸው፡፡
ደሞዝ:- የመነሻ ደሞዝ ከ12.500 /15,500 ብር በቅደም ተከተል እንደብቃታቸው
5. የሰው ኃይል ምልመላና ስልጠና ሰራተኛ
የት/ት ደረጃ፡- በተዛማጅ መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ፡፡ የስራ ልምድ፡- 1 ዓመት የስራ ልምድ
ደሞዝ:- 16,500/ 20,500 ብር እንደብቃታቸው እድሜ፡- ከ28 - 45 ብዛት፡- 2 ፆታ፡- - አይለይም
6. የቪዲዮ ኢዲቲንግና የግራፊክስ የሙያተኛ
የትምህርት ደረጃ፡- በዘርፉ የሰለጠኑና በተግባር መስራት የሚችሉ የስራ ናሙና ማቅረብ የሚችሉ፡፡
ደሞዝ:- 20,500 ብር እድሜ፡- ከ25-40 ብዛት፡- 2 ፆታ፡- አይለይም የስራው ጊዜ፡- የሙሉ ጊዜ ሰራተኛ
7. ጀማሪ የስልክ ኦፕሬተር እና እንግዳ አቀባበል ሰራተኛ እና ከፍተኛ የስልክ ኦፕሬተር እና እንግዳ አቀባበል ሰራተኛ
የትምህርት ደረጃ፡- 10ኛ ወይም 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ /የቴ/ሙያ ዲፕሎማ ያላቸው/በማንኛውም ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ፡፡
ደሞዝ:- 10,500 / 12,500 / 15,500 ብር በቅደም ተከተል እንደ ደረጃቸው እድሜ፡- ከ25 - 40 ብዛት፡- 16 ፆታ፡- ሴት

ለማመልከት ስትመጡም ሆነ በስራ ወቅት የድርጅቱ አለባበስ መመሪያ ፡- ለሴቶች፡- ስርአት ያለው የሴቶች አለባበስ ቀሚስ ወይም ጨርቅ ኮትና ሱሪ ያሟሉ፡፡ ለወንዶች፡- ሸሚዝ ፣ ክራቫት ፣ ጨርቅ ሱሪና ኮት ቆዳ ጫማ በአጭር የተስተካከለ ፀጉርና ፂም ግዴታ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- አመልካቾች የት/ት ማስረጃችሁን ከ10/12ኛ ክፍል ጀምሮ እና ተዛማጅ ማስረጃችሁን ኦሪጂናል እና ኮፒ ይዘው ይቅረቡ፡፡ CV ፣ ማመልከቻና ለቅጥር ለማለፍ ይጠቅመኛል ያሉትን ማስረጃ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በአካል ቢሮ በማቅረብ አመልክቱ፡፡
የመመዝገቢያ ጊዜ:- 06 / 08 / 2018 ዓ.ም እስከ 30 / 08 / 2018 ዓ.ም ድረስ
አድራሻ፡- ቦሌ መድሃኒያለም ኢድናሞል አካባቢ / አለምነሽ ፕላዛ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 801
ለተጨማሪ መረጃ:-- 0966 – 00 85 85 / 0966 – 72 7070

03/04/2026

በከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 988/ 2016 መሠረት የተቋማት ደረጃ ስያሜን በተመለከተ ፡-
---------------------------------------------------------------------------------------------------
** ተቋማት የደረጃ ስያሜ የሚሰጣቸው በሚቋቋሙበት ጊዜ ወይም የመጀመሪያ ፈቃድ በሚሰጣቸው ወቅት ወይም ፈቃድ ተሰጥቷቸው በሥራ ላይ እያሉ የደረጃ ስያሚ ጥያቄ ሲያቀርቡ እና መስፈርቱን ሲያሟሉ ሆኖ ቀጥሎ ባሉት የደረጃ ስያሜ መሠረት ይሆናል፤



** በከፍተኛ ትምህርት ተቋም በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 13 መሠረት በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ቢያንስ በአንድ የትምህርት ዓይነት በዲግሪ ፕሮግራም ትምህርት መስጠት የሚችል እና ባለሥልጣኑ የሚያወጣቸውን ዝርዝር መስፈቶች ሲያሟላ የሚሰጥ ስያሜ ነው ፤

** የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋም በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ በደረጃ 1 እና 2 ላይ የሚመደቡ የሙያ መስኮችን በማካተት አጫጭር ስልጠናን ጨምሮ ትምህርትና ስልጠና ለሚሰጥ ተቋም የሚሰጥ ስያሜ ነው፤



**በከፍተኛ ትምህርት ተቋም በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 13 መሠረት በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ቢያንስ ከዲፓርትመንት በላይ በሆነ አንድ የትምህርት ክፍል በዲግሪ ፕሮግራም ትምህርት የሚሰጥ እና ባለስልጣኑ የሚያወጣቸውን ዝርዝር መስፈቶች ሲያሟላ የሚሰጥ ስያሜ ነው፤

** የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋም በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ከደረጃ 1 እስከ 4 ላይ የሚመደቡ የሙያ መስኮችን በማካተት ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥ ተቋም ነው፤



**በከፍተኛ ትምህርት ተቋም በአዋጅ ቁጥር በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 11 መሠረት ንዑስ አንቀጽ 1 እስከ 3 የተቀመጠውን መስፈርት የሚያሟላ እንዲሁም ባለሥልጣኑ የሚያወጣቸውን ዝርዝር መስፈቶች ሲያሟላ የሚሰጥ ስያሜ ነው፤

** ማንኛውም ተቋም ወይም ፕሮግራም የትምህርት ጥራትን ካጓደለ፤የከፍተኛ ትምህርት አሰጣጥ ህጎችን ከጣሰ እና የእግድ ቅጣት ተላልፎበት ካላሻሻለ ባለሥልጣኑ የሰጠውን ፈቃዱ ይሰረዛል፤


** በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ከደረጃ ከ1 እስከ 5 ላይ የሚመደቡ የሙያ መስኮችን በማካተት ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥ ተቋም ነው፤



** በከፍተኛ ትምህርት ተቋም በአዋጅ ቁጥር በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 አንቀጽ 10 መሠረት ንዑስ አንቀጽ 1 እስከ 3 የተቀመጠውን መስፈርት የሚያሟላ እንዲሁም ባለሥልጣኑ የሚያወጣቸውን ዝርዝር መስፈርቶች ሲያሟላ የሚሰጥ ስያሜ ነው፡፡

የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ


Encourage and assist the growth of organizational culture in education and training institutions.

21/03/2026

ማሳሰቢያ
የጥራት ሽልማት ስልጠና ለመውሰድ ክፍያ በመፈፀም ያመለከታችሁ በሙሉ ስልጠናው ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ ይሰጣል ተብሎ የተላለፈ መሆኑ ይታወቃል።
ይሁንና የበአል ማግስት በመሆኑ ወደ ተለያዩ ክልሎች የሔዱ አመልካቾች በአንድ ሳምንት እንዲራዘም ጠይቀዋል።
በመሆኑም ስልጠናው በቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ መጋቢት 19 ከቀኑ 7:30 ጀምሮ ይሰጣል።
በቀጣይ ሳምንት በየትኛውም ምክንያት ስልጠናው አይቀየርም።
አዲስ ተመዝግባችሁ መሰልጠን ለምትፈልጉ ምዝገባ እስከ መጋቢት 18 ቀን ድረስ ይከናወናል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉእንኳን ለኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!ኢድ ሙባረክ!
19/03/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለኢድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!

ኢድ ሙባረክ!

17/03/2026

ለክልል ስራ አመልካቾች
በተለያየ ጊዜ በድርጅታችን ለስራ ያመለከታችሁ የክልል የስራ አመልካቾች በክልል የሚታዩ አንዳንድ ሁኔታዎች ስራዎች ሳይጀመሩ የቆዩቢቸው አካባቢዎች መኖራቸው ይታወቃል።
በዚሁ መሰረት በውስን አካባቢዎች በድጋሚ ሁኔታዎች ተመርምረው ወደ ስራ ለመግባት የተወሰነ በመሆኑ ከዚህ በፊት በተሰጣችሁ ሊንክ ቀድሞ የላካችሁትን ዶክመንቶችና ጀተናዎች እንድትልኩ እናሳስባለን።
የመላኪያ ሊንክ
t.me/worldclassqualityabc



https://t.me/worldclassqualityawardethiopia

ማሳሰቢያየጥራት ሽልማት ስልጠና ለመውሰድ ክፍያ በመፈፀም ያመለከታችሁ በሙሉ ስልጠናው ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ ይሰጣል። በመሆኑም በእለቱ ለስልጠና የሚያስፈል...
17/03/2026

ማሳሰቢያ
የጥራት ሽልማት ስልጠና ለመውሰድ ክፍያ በመፈፀም ያመለከታችሁ በሙሉ ስልጠናው ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ ይሰጣል። በመሆኑም በእለቱ ለስልጠና የሚያስፈልጉ ግብአቶች ይዛችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን!
አዲስ ተመዝግባችሁ መሰልጠን ለምትፈልጉ ምዝገባ እስከ መጋቢት 11 ቀን ድረስ ይከናወናል።

📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌ለምዘና ስራ አመልካቾች!  በድርጅታችን ግራንድ አፍሪካን ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለመዛኝነት ስራ መደብ አመልክተው የነበራችሁ  በሙሉ  ድርጅታችን ለመዛኝነት...
16/03/2026

📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌
ለምዘና ስራ አመልካቾች!
በድርጅታችን ግራንድ አፍሪካን ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለመዛኝነት ስራ መደብ አመልክተው የነበራችሁ በሙሉ ድርጅታችን ለመዛኝነት ያመለከቱትን በሙሉ የአለም አቀፍ የጥራት ሽልማት ምዘና ስርኣት ስልጠና ሰጥቶ የተሸለ ውጤት ያስመዘገቡትን ቀጥሮ ለማሰራት ወስኗል፡፡
♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️♻️
ስልጠናው መጋቢት 8 ቀን ከቀኑ 7፡30 እስከ 11፡30 የሚሰጥ ሲሆን የስልጠናውም ቦታ ቦሌ ኣለምነሽ ፕላዛ 8ኛ ፎቅ የቤት ቁጥር 801 የሆነው የወርልድ ክላስ አዳራሽ ውስጥ ነው፡፡
🎖🎖🎖🎖🎖🎖🎖🎖
ስልጠናው የሚሰጠው በነጻ ነው፡፡ ስልጠናው ለግማሽ ቀን ብቻም ይሰጣል፡፡
እርሶ ስልናውን ወስደው ከስልጠናው በኋላ በሚሰጥ ፈተና የተሸለ ውጤት በማምጣት ከእኛ ጋር መስራት የሚፈልጉ ከሆነ ነገ መጋቢት 8 ቀን ተገኝተው እንዲሰለጥኑ እናሳውቃለን፡፡
🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯🎯
ለስልጠና ሲመጡ የድርጅቱን የአለባበስ መመሪያ አሟልተው ይምጡ፡፡ እስክሪብቶና የማስታወሻ ደብተር ይያዙ፡፡ በሰዓቶ ይገኙ ፡፡
አርፍዶ የሚመጡና የድርጅቱን መመሪያ የማያሟሉትን እናሰናብታለን፡፡
መልካም ቀን!
📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌

ሽልማት የሠው ልጅ መልካም የመስራት ባህሪ ያሳድጋል! መልካም የሠራ ሁሉ ቢያንስ ጥሩ ሠርተሀል ተብሎ መመዘን አለበት! ለዚህ ደግሞ መልካም የሰሩትን በማህበረሰቡ ውስጥ የምታዩ ሁሉ በመጠ....

🔺 Fraud Triangle – Pressure, Opportunity & RationalizationFraud rarely happens by accident. In most cases, it occurs whe...
07/03/2026

🔺 Fraud Triangle – Pressure, Opportunity & Rationalization

Fraud rarely happens by accident. In most cases, it occurs when three critical factors come together — a concept widely known in auditing as the Fraud Triangle.

Understanding this model helps auditors, accountants, and business leaders identify potential fraud risks and strengthen internal controls within organizations.

1️⃣ Pressure (Motivation)
Personal or financial stress that pushes an individual toward fraudulent behavior.
Examples: financial difficulties, unrealistic performance targets, or lifestyle pressures.

2️⃣ Opportunity
Weak internal controls or poor oversight that create the chance to commit fraud without immediate detection.

Examples: lack of segregation of duties, poor supervision, or unrestricted access to records.

3️⃣ Rationalization
The psychological justification individuals use to convince themselves that the fraudulent act is acceptable.

Examples: “I’m just borrowing the money” or “The company will not notice.”

📊 For auditors and organizations, recognizing these three elements is essential for:

✔ Identifying fraud risk areas
✔ Strengthening internal control systems
✔ Designing effective audit procedures
✔ Promoting ethical organizational culture



07/03/2026

GRAND AFRICAN ORGANIZATIONAL & LEADERSHIP AWARD ORGANIZATION

                    🔧📈🔴 KAIZEN – The Power of Continuous Improvement 🔴👉🏻 How can we improve continuously?👉🏻 How do we in...
05/03/2026

🔧📈

🔴 KAIZEN – The Power of Continuous Improvement 🔴

👉🏻 How can we improve continuously?
👉🏻 How do we involve teams effectively?
👉🏻 How can we eliminate waste and aim for zero defects?
👉🏻How do we evolve step by step and standardize progress?

Kaizen is not about radical change.
It’s about small, consistent improvements that create long-term excellence.

In maintenance, production, and operations, applying Kaizen means:

1️⃣ Higher performance.
2️⃣ Reduced waste.
3️⃣ Improved quality.
4️⃣ Stronger team engagement.
5️⃣ Sustainable growth
🎯 Continuous improvement is not an option anymore — it’s a necessity for competitive industries.
♦️Let’s build a culture where improvement never stops. 🚀

Address

Djibouti Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when World Class Quality Award Organization posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to World Class Quality Award Organization:

Share