04/12/2025
ለጤና ባለሙያዎች በተለያዩ ቦታ የተለያየ የduty ክፍያ በተለያየ መመሪያ እየተተገበረ ይገኛል ።
ለምን ተመሳሳይ የሆነ አሰራር አይተገበርም?
ለምሳሌ ያህል አዲስአበባ ላይ በአዲሱ ደሞዝ scale መሰረት በ2014 በወጣው መመሪያ ሲከፈል በሌሎች ክልሎች ባሉ ሆስፒታሎች ደሞ በደሞዝ scale ሆኖ በ 1 ተባዝቶ ሲሆን
አንዳንድ የወረዳ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ ደሞ በድሮው ደሞዝ scale ነው የምንከፍለው እያሉ እየዛቱብን ይገኛሉ ።
አንድ አገር እየኖርን የዚህን ያህል ልዩነት ለምን ??የጤና ስርዓቱ ግን እውነት ተቆጣጣሪ አለው?? ምንድን ነው ችግሩ??
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ የጤና ባለሙያዎች duty ክፍያ በድሮ ደሞዝ ነው የምንከፍል ብለው ከመስከረም ጀምሮ አልተከፈለንም ምክንያቱን ስንጠይቅ ክልል ከፌዴራል በጀት ባለመልቀቁ ምክንያት ባለው ክፈሉ ተብለናል የሚል መልስ እየተሰጠን ይገኛል። ድምፅ ሁኑን በአንድ አገር እየኖርን የተለያየ አሰራር መመሪያ ለምን??
ፌደራል ባወጣው መመሪያ እና ህግ መሰረት እየተሰራ አደለም።
ለጤና ባለሙያ ጥቅማጥቅም በተሻሻለው መሰረት ተግባራዊ ይሆን ዘንድ ጥብቅ ክትትል እና ቁጥጥር ይደረግ ።
ባርነት ይቁም እየጠየቅን ያለነው እንቅልፍ አጥተን ስለምንሰራው ስራ ክፍያ ነው።