Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ Sometimes take a LOSS for a bigger WIN.

05/11/2025

አንድት ጠንካራ ሀገር ሊኖሯት ከሚገቡ ጠንካራ ተቋማት መካከል አንዱና ዋነኛው የጤና ዘርፉ ነው። ነገር ግን ሀገራችን አይደለም ጥሩ የጤና ስርአት ልትገነባ ይቅርና የነበራትን እያጣች ነው።

🔘ባለሙያዎቿ መያዝ አልቻለችም ፤ ምክንያቱም ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ ባለሙያዎቿ ስደትን መርጠው እየተሰደዱ ነው፣

🔘የጤና ተቋማቶቿ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባዶ ካዝናዎች ሆዋል ፤ በሰው ሀይልም ሆነ በመድሀኒት እጥረት ተመተዋል። ለወደፊትም ከዚህ ይብሳል፣

🔘አጠቃላይ የጤና ሴክተሩ ለባለሙያውም ሆነ ለታካሚው ምቹ አይደሉም ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጉዟቸው አሽቆልቁሏል፣

ጉድለትን መገምገም እና እንዲስተካከል ነጋ ጠባ መንግስትን መጨቅጨቅ እንደ ፖለቲካ ተቆጥሮ የሚወነጀልባት ሀገር ሆናለች። ሀገር እንደ ሀገር መለወጥ ካለባት አንዱና ዋነኛው የጤና ስርአቱ መጠንከር ነው።

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

መንግስት የጤና ባለሙያዎችን 'ሿ ሿ' መስራቱን ቀጥሏል።ደቡብ ክልል አሪ ዞን😒
05/11/2025

መንግስት የጤና ባለሙያዎችን 'ሿ ሿ' መስራቱን ቀጥሏል።

ደቡብ ክልል አሪ ዞን😒

05/11/2025

"የደመወዝ ጭማሪው ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል።"

የቤንሻንጉል ክልል ጤና ቢሮ 😃
በጣም ይቀልዱ የለ እንዴ!!!

05/11/2025

— ደቡብ ክልል የመስከረም እና የጥቅምትን ጨምሮ በአድስ ይከፈላል የተባለው ደሞዝ እስካሁን አልገባም። የድሮውን ነው ያስገቡት ፤ የት ሄደን እንደምንጮህ ግራ ገብቶናል። ድምፅ ሁኑን።

05/11/2025

ከመንግስት ደመወዝ ያነሰ እና እኩል ደመወዝ የሚከፍሉ የግል ክሊኒኮ እና ሆስፒታሎች የሰራተኛችሁን ደመወዝ አስተካክሉ። የማታስተካክሉ ካላችሁ እናጋልጣችሗለን። ትግላችን እናንተንም ይመለከታል።

05/11/2025

የብዙዎቹ የገጠር ጤና ጣቢያ እና ሆስፒታሎች የዱቲ አበል ክፍያ የሚፈፀመው ከ6 ወር እስከ 12 ወር እያሳለፉ ነው። ለዚህ ዋናው ምክንያት የወረዳ ካቢኔዎች በጀቱን ወደ ሌላ አዙረው ስለሚጠቀሙበት ነው። በዚህ ምክንያት የጤና ባለሙያው ሳይከፈላቸው የላባቸውን ዋጋ ለካድሬ አበል አስረክበው ሲኖሩ ቆይተዋል።

ይህ ችግር የጤና ሚኒስቴር የክትትልና የአፈፃፀም ችግር ነው። ዝርክርኩ ጤና ሚኒስቴር ለባለሙያው አንድትም ቀን ቆሞ አያውቅም። ከዚህ በሗላ ግን የዚህን አይነት ችግር ባለሙያው መታገስ አይችልም።

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

05/11/2025


የካቲት 12 ሆስፒታል እንደዚህ ያለን ነው ።

ለሁሉም የተቋሙ ሰራተኞች እና ክፍል ኃላፊዎች በሙሉ በጤና አገልግሎት አስተረዳደር አዋጅ ቁጥር 1362/2017 አንቀጽ 32 መሰረት ከመስከረም 01 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የጤናው ዘርፍ የመንግስት ሰራተኞች፤የትዳር አጋሮቻቸው እና ከ18-ዓመት በታች ለሆኑ ልጆቻቸው የጤና መድህን ሽፋን እንዲያገኙ በተላለፈው ሰርኩላር መሰረት የኢትዮያ የጤና መድህን አገልግሎት ሁሉም ሰራተኛ ከዚህ በታች በተያያዘው ፎርማት መሰረት የራሳቸውንም ሆነ የቤተሰቦቻቸውን ቅጽ በመሙላት ይህ ማስታወቂያ በወጣ 3-(በሶስት) ቀን ውስጥ ሁሉም ሰራተኛ ከክፍል ኃላፊው ፎርሙን በመውሰድና በመሙላት ለክፍል ኃላፊው እንዲያስረክብ እና ክፍል ኃላፊዎችም በአራተኛው ቀን የተሞላዉን ፎርም ለሰው ኃብት ዳይሬክቶሬት እንዲያስረክቡና ፎርሙን በሰዓቱ ሞልቶያላመጣ ክፍልም ሆነ ሰራተኛ የትም ቦታ ቢሆን ነጻ ህክምና ለራሱም ሆነ ለቤተሰቡ እንዲሁም ወርኃዊ ደመወዝ የማያገኝ በመሆኑ ሆሉም ሰራተኛ በተባለወው ጊዜ እንደያቀርብ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን!!

05/11/2025



ደቡብ ጎንደር ስማዳ ወረዳ የምንገኝ መንግስት ሰራተኛች ለብልፅግና 2% ትከፍላላችው እየተባልን ነው ጥቅምት 2018 ደመወዝ ላይ እባካችው ድምፅ ሁኑን?? ትክክለኛ መረጃ ነው ለምሳሌ እኔ የምሰረው ጤና ጣቢያ ሂሳብ ክፍሉ 2%ሰርተህ አምጣ ተባለ ባለሞያው እምቢ ብሎኛል ቢላቸው ዝም ብለህ ስራው ካልሰራኸው ያንተን ደመወዝ ነው የምናግደው እየተባለ ነው ።ባለፈው አብይ ያለፊርማ ደመወዝ አይቆረጥም ብሎ ነበር ።እደዚህ አይነት ብልሹ አሰራር እባካችው ድምፅ ሁኑን??? ።ስምአይጠቀስ

05/11/2025

📨
Arero primary hospital is the only hospital that denied to pay salary according to new scale. A lot of health workers are suffering here in desert. When we ask the administration for our right they took us to jail and newly assigned CEO was well known by punishing healthworkers. please be voice for us!

ዓይን አውጣነት በተግባር !================በዚህ ዘመን ያለን ጤና ባለሙያ ማጭበርበር ፈፅሞ አይቻልም!የነቃ፣ ለትግል የበቃ Smart የጤና ባለሙያ ተፈጥሯል።ከፊል የጤና ሽፋንን ብቻ...
04/11/2025

ዓይን አውጣነት በተግባር !
================
በዚህ ዘመን ያለን ጤና ባለሙያ ማጭበርበር ፈፅሞ አይቻልም!
የነቃ፣ ለትግል የበቃ Smart የጤና ባለሙያ ተፈጥሯል።

ከፊል የጤና ሽፋንን ብቻ ለመስጠት ታስቦ በኢትዮጵያ ጤና መድህን ኤጀንሲ ተዘጋጅቶ ጤና ባለሙያው እንዲመዘገብ የወረደውን መመሪያ ፣ ሙሉ የጤና ሽፋን ካልሆነ አንመዘገብም በሚል ጤና ባለሙያው መብቱን እያስከበረ ባለበት ሰዓት ፤ ሁሉን ነገር በኃይል ለመፍታት የሚዳክሩ የአገዛዙ ካድሬዎች ፣ ጤና መድህን መመዝገብ በፈቃድ እንደሆነ መመሪያው ቢገልፅም እነሱ ግን በተዘዋዋሪ የማስገደጃ ስልቶችን እየተጠቀሙ ይገኛሉ።

1ኛው ፦ ከታች በተለጠፈው ደብዳቤ እንደምታዩት "ጤና መድህን አልፈልግም ብላችሁ ስማችሁን እና ፊርማችሁን አስገቡ በማለት ባለሙያውን እያስገደዱት ይገኛሉ።

2ኛው = ጤና መድህን ካልገባችሁ Staff ህክምናን እናቆማለን

3ኛ= ከዚህ በኋላ የጤና መድህን አባልነት ምዝገባ የለም

የሚሉ አስገዳጅ ነገሮችን እያደረጉ ይገኛሉ።

አሁንም ከዚህ በታች የተጠቀሱት ነገሮች መመሪያው ውስጥ ሳይካተቱ Amoxacilin እና paracetamol ለማውጣት ብለን አንፈርምም❗️

1ኛ = ቴሌ፣ ባንክ፣አየር መንገድ ያሉ የመንግስት ሰራተኞች በመንግስትም ተቋም የማይሰጡ አገልግሎቶችን ከግል ተቋም የምርመራም እና የመድሃኒት አገልግሎቶችን በማግኘት በደረሰኝ ማወራረድ ይችላሉ --ሙሉ ወጪያቸውን ተቋሙ ይሸፍናል።

ወደኛ ስንመጣ( የሰው ጤና ስንሰጥ የራሳችንን ጤና ለTB, HBV, HCV, HIV,ለጨረር የምናጋልጥ ባለሙቻዎች) ጤና ተቋም ላይ የሌለን መድሃኒትም ሆነ ምርመራ በግላችን ወጪውን እንድንችል የተደረገው በአስቸኳይ መስተካከል አለበት❗️

2ኛ = End stage liver disease 2 Chronic Viral Hepatitis ተብለው የጉበት ንቅለ ተከላ የሚያስፈልጋቸው ፤ በአቅም እጥረት ወደ ውጭ ሄደው ህክምናውን ሳያገኙ ህይወታቸው ያለፈባቸው ባለሙያዎች አሉን - ነፍሳቸውን ይማርና.....

እነዚህ ባለሙያዎች ለ Hepatitis virus የተጋለጡት የሰውን ህይወት ለማዳን ሲሉ ነው፤ ግን የራሳቸውን ህይወት በአቅም እጥረት ምክንያት ተነጠቁ። ስለዚህ ጤና መድህኑ የውጭ ህክምናን እንዲያካትት እንጠይቃለን❗️

3ኛ፦ Valvular replacement የሚያስፈልጋቸው ብዙ የጤና ባለሙያዎቻችን አሉ። ባለፈው በጤና ባለሙያው ርብርብ የልብ ቀዶ ህክምና ያደረገች እህታችንን ሁላችንም እናስታውሳታለን።
ስለዚህ እንዲህ አይነት ህክምናዎችን ወረፋ ሳንጠብቅ በግል የልብ ቀዶ ህክምና ማዕከላት በነፃ የመታከም መብትን ጤና መድህን ውስጥ እንዲካተት እንፈልጋለን❗️

4ኛ = የመነፀር፣ ፣የተቦረቦረ ጥርስን የመሙላት፣ የዲያሊስስ፣ ከፊል የመስማት ችግርን የሚጨምሩ የህክምና መሳሪያዎችን ፤ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ በሚገጥሙን ግዜ ያሉት ህክምናዎች በጤና መድህኑ እንዲካተቱ እንጠይቃለን❗️

እነዚህ ወሳኝ ጉዳዮች ሳይካተቱ አንድም ባለሙያ ባለመፈረም መብታችንን እንድናስከብር እለምናችኋለሁ❗️

03/11/2025

— እኛ አማራ ክልል ውስጥ በምዕራብ ጎጃም በደምበጫ ወረዳ በዳባ፣ አንጄኔ እና የጨረቃ ጤና ጣቢያወች የምንሰራ ባለሙያወች በ 1 አዳር የሚያድር የ OPD ባለሙያ 1ነርስ ወይም 1ጤና መኮንን ነው። በመሆኑም ይህ ከዲውቲ አሰራር ውጭ መሆኑ እና አሁን ካለው የታካሚ ፍሰት መጨመር እና የህክምና ጥራትን ለማሻሻል የሰው ሀይል እንዲጨመረን በተደጋጋሚ ስብሰባ ቦታወች ላይ አሳውቀናል ከዚህ አልፎም ወረዳ ፣ ዞን በደብዳቤ ብንጠይቅም ሊመለስልን አልቻለም። የሚመለከተው ሁሉ እንዲያግዘን ስንል እንጠይቃለን። እናመሰግናለን።

03/11/2025

አሁንም እየጠየቅ ነው 👉 የዱቲ ፣ የተጋላጭነት ፣ የtop up ፣ የቤት እና የትራንስፖርት እንዲሁም የበረሃ አበል እና መሰል ጥቅማ ጥቅሞች ለጤና ባለሞያው በተለየ መልኩ ታይቶ የተሻለ ማስተካከያ ሊደረግ ይገባል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251934647389

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hakim Mereja ሀኪም መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Hakim Mereja ሀኪም መረጃ:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram