የጤና መረጃ

የጤና መረጃ This page is Created to provide BEST Medical information ወዳጅ ዘመድዎ እንዲደርሰው ሼር በማድረግ ያሳውቁ
FACEBOOK
www.facebook.com/ethiomedhealth
ፔጃችንን Like በማድረግ ይከታተሉን
(1)

27/02/2025
17/07/2023

እንኳን ደስ ያላችሁ! ደስ ብሎናል!
ሁሉም ተማሪዎች አልፈዋል!
100% !

ተማሪዎቻችን በExit Exam ከፍተኛ ነጥብ አስመዝግበዋል።

የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስቴር በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ባስጀመረው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መውጫ ፈተና የኮሌጃችን ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማምጣታቸውን በትናንትናው ዕለት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባወጣው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት :- በያዝነው 2015 ትምህርታቸውን የሚያጠናቅቁ 151 የሕክምና ተማሪዎች( Intern) የሚከተለውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል።

- 44 በመቶው 85 እና ከዚያ በላይ አግኝተዋል ።
74 በመቶው ተፈታኞች ደግሞ ከ80 እና ከዚያ በላይ ውጤት አግኝተዋል።

ውድ መምህራን እና የኮሌጁ ማሕበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ!
ውድ ተማሪዎች እንኳን ለዚህ ስኬት አበቃችሁ!

Via :- SPMMC

17/07/2023

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የላቀ ወጤት!

በአገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲያችን በግምባር ቀደምትነት ተማሪዎችን በማሳለፉ እንኳን ደስ አለን፤ እንኳን ደስ አላችሁ።
***

በአገር ዓቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው እና በዩኒቨርሲቲያችን ባሉ 8 ኮሌጆች፣ 2 ኢንስቲትዩቶችና 1 ትምህርት ቤት ስር በሚገኙ 73 ትምህርት ክፍሎች ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል።

በአጠቃላይ ካስፈተናቸው 3,089 ተማሪዎች ውስጥ 2,760(89.35%) ተፈታኞች በብቃት አልፈዋል። ፈተናውን ከወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎች መካከል 34 ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ (100%) አሳልፈዋል።

ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በመደበኛ መርሐግብር ካስፈተናቸው 2,919 ተማሪዎች 2,703 (92.6%) ያለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ 170 ተማሪዎች በተከታታይ መርሐግብር ተፈተነው 57(33.53%) ፈተናውን በብቃት አልፈዋል።

ይህም ውጤት በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ ያደርገዋል።

በዚህም መላው የዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብና አጋሮቻችን ከፍተኛ ኩራትና ደስታ ተሰምቷቸዋል። የተገኘው ስኬት አበረታችና ለቀጣይ ትልቅ ኃላፊነትን የሰጠን ነው።

ስለሆነም ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆች፣ የቴክኒክ ረዳቶች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ ትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች አጋር አካላት እንዲሁም መላ የትምህርት ቤተሰቡ በትብብር ያስመዘገባችሁት ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እንወዳለን።
***
ለልህቀት እንተጋለን!
ህዝብና ዓለም ዓቀፍ ግኝኙነት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም

05/06/2023
01/11/2022

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ የምትፈልጉ:
ሙያ እና ሥራ ልምዳችሁንና
መስራት የምትፈልጉ አከባቢ

Inbox or comment ላይ
በ English, or Amharic Or Afan Oromo ፃፉ

20/07/2022

አዲስ አበባን ከትምባሆ ጭስ ነፃ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
------------------------------
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አዲስ አበባን ከትምባሆ ጭስ ነፃ ለማድረግ በትምባሆ ቁጥጥር የተከናወኑ ተግባራት፣ ከትምባሆ ጭስ ነፃ አካባቢን ለመፍጠር ልንከተላቸው ስለሚገቡ ቁልፍ ተግባራትና የባለድርሻ አካላት ሚና በማስመልከት በመቋሚያ የማህበረሰብ ልማት ድርጅት አጋርነት ሀምሌ 12/2014 ዓ.ም ውይይት አካሄደ፡፡
በውይይት መድረኩም የባለስልጣን መ/ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት በዳዳ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት አዲስ አበባን ከትምባሆ ጭስ ነፃ ለማድረግ በነበሩት ተግባራት ብዙ ተግዳሮቶች ቢኖሩም በባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ለውጥ የተመዘገበ መሆኑን አውስተው በቀጣይም በጋራ በመደጋገፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን አውቀው የተሻለ ስኬት ለማስመዝገብ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል፡፡
በውይይት መድረኩም የመነሻ ፁሁፍ ያቀረቡት የባለስልጣን መ/ቤቱ የቁጥጥር ባለሙያና የትምባሆ ፎካልፕርሰን አቶ ሞላ ታደለ በትምባሆ ቁጥጥር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ ከትምባሆ ጭስ ነፃ አካባቢን ለመፍጠር ልንከተላቸው ስለሚገቡ ቁልፍ ተግባራትና የባለድርሻ አካላት ሚና፣ ተግባርና ሀላፊነት ምን ምን እንደሆነ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
የመቋሚያ ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የፕሮጀክት ኦፊሰርም አቶ ኢሲሻ መንግስቱ አዲስ አበባን ከትምባሆ ጭስ ነፃ ለማድረግ ከልማት ድርጅቱ ምን እንደሚጠበቅና ሚናቸው ምን እንደሆነ በሰፊው አቅርበዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎችም የትምባሆ ቁጥጥር ስራን ማጠናከር ከሱስ ጋር ተያይዞ የሚመጡ የሰላምና ደህንነት ጉዳዮችን በመቀነስ ለሀገር ግንባታ ሚናው የላቀ መሆኑን፣ ሀላፊነታችንና ግዴታችንን በቀጥታ ወስደን መስራት እንደሚስፈልግ፣ ከትምህርት ሴክተሮች ጋር የፀረ- ሱስ ከበብ በማቋቋም መሰራት እንዳለበት፣ የትምባሆ ጭስ የማይነካው የማህበረሰብ ክፍል ስለሌለ ሁላችንም ሁለተኛ አጫሾች መሆናችንን በመገንዘብ ሀላፊነታችንን መወጣት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የመቋሚያ ማህበረሰብ ልማት ድርጅት ስራ አስፈፃሚ አቶ ኤልያስ ካላዩ እንዳሉት ሁላችንም እንደ ባለድርሻ አካላት ሚናችንን መወጣት እንደሚያስፈልግ፣ ድርጅቱ ባለፉት ዓመታት ከሱስ ማገገሚያ ጋር ዘርፈ ብዙ ስራ መሰራቱንና በቀጣይም የቁጥጥር፣ መልሶ የማገገምና የማስተማር ተግባራትን እንደ ሀገር ብሎም እንደ አህጉር አቅዶ ለመስራት በቂ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የባለስልጣን መ/ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት በዳዳ በበኩላቸው ትምባሆ ሞኖፖል ለጉዳት እንደሚሰራው ሁሉ እኛም ችግሩን ለመመከት እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ተቋም ሚናችንን በመወጣት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ፣ ጉዳዩ ትኩረት እንዲያገኝ ለከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ለማሳወቅ እተሰራ ስለመሆኑ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት አንዳችን ለአንዳችን በመቀናጀት ተመጋጋቢ የሆነ ስራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ፣የመድሀኒት የጤና ክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ባለስልጣን

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጤና መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram