የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals

የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals, Medical and health, Addis Abeba, Addis Ababa.

የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ ካልተፈታ የጤና ስርዓቱ አደጋ ውስጥ ይገባል ሲል የትግራይ የጤና ባለሞያዎች ማህበር አስታወቀማህበሩ በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ መፍትሄ...
07/04/2025

የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ ካልተፈታ የጤና ስርዓቱ አደጋ ውስጥ ይገባል ሲል የትግራይ የጤና ባለሞያዎች ማህበር አስታወቀ

ማህበሩ በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ መፍትሄ ካልተሰጠውና ተገቢውን ተኩረት ካላገኘ ሰራተኞቹ ስራ እየለቀቁ መሄዳቸው አይቀሬ ነው ያለ ሲሆን ይህ ደግሞ በማገገም ላይ የሚገኘውን የጤና ስርዓት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ብሏል።

ማህበሩ አሁን ላይ እየሰራቸው ስላሉ ስራዎችና እየገጠሙት ስለሚገኙት ችገሮች ለሚመለከታቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና ለፌደራል መንግስት አመራሮች አቅርቧል ያሉት የትግራይ የጤና ባለሙያዎች ማህበር ሊቀመንበሩ ዶ/ር ፍስሀ አሸብር ከችግሮቹ መካከል ያልተከፈለ ውዝፍ ደመወዝ፣ የሙያተኛ ከለለ አለማግኘት ፣ የትራንስፖር አገልግሎት፣ የስራ ቦታ፣ የመኖሪያ ቤት ጥያቄ፣ ነፃ የህክምና አገልግሎት፣ በኮቪድ ጊዜ ለተሰራ ስራ ያልተፈፀመ ክፍያና የደመወዝና የስራ መደብ እርከን እድገት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

ሊቀመንበሩ አክለው ሞያተኛው ያለውን ሁሉ ለመስጠት የሚያስችል ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሞያተኛው እያበረከተው ላለው አስተዋፅኦና እየከፈለው ላለው ዋጋ ተገቢ ክብርና እውቅና ሊሰጠው ይገባል ሲሉም ተደምጠዋል።

ማህበሩ አሁንም እያነሳቸው ያሉ ጥያቄዎች ምንም ምላሽ ሳያጉኙ አመት ከስምንት ወር መቆየታቸው የገለፁት ዶ/ር ፍስሃ የሞያተኛው ጥያቄና ችግር በአፋጣኝ መፍትሄ ካልተበጀለት የትግራይን የጤና ስርዓት አደጋ ውስጥ የሚከት ይሆናል፣ ሞያተኛውም በዚህ ተስፋ በመቁረጥ ስራ እየለቀቀ ይሄዳል ሲሉ መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

ከዚህ ቀደም ማህበሩ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ከሰሜኑ ግጭት ወዲህ 200 ዶክተሮች ጨምሮ ከ915 የህክምና ባለሞያዎች ከስራ ለቀው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው መግለፁ አይዘነጋም።

ከዱባይ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራውስደተኛ Pharmasiset ነኝበማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራው የአንድ ዓመት ከግማሽ ድ...
06/04/2025

ከዱባይ

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና
ጣቢያ ነበር የምሰራው

ስደተኛ Pharmasiset ነኝ

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራው የአንድ ዓመት ከግማሽ ድሞዝ ሳይከፈልኝ ኑሮው ቢከብደኝ

የምወድውን ማሕበረሰብ ለሁለት ዓመት ካገለገልኩበት የጤና ተቋም ትቼ ስደት ዱባይ ተሰደድኩኝ::

ነገር ግን በጣም የማዝነው::

አቡድልሰመድ ከዱባይ

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴
# Via ጉርሻ

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram