የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals

የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals, Medical and health, Addis Abeba, Addis Ababa.

የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ ካልተፈታ የጤና ስርዓቱ አደጋ ውስጥ ይገባል ሲል የትግራይ የጤና ባለሞያዎች ማህበር አስታወቀማህበሩ በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ መፍትሄ...
07/04/2025

የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ ካልተፈታ የጤና ስርዓቱ አደጋ ውስጥ ይገባል ሲል የትግራይ የጤና ባለሞያዎች ማህበር አስታወቀ

ማህበሩ በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ችግር በቶሎ መፍትሄ ካልተሰጠውና ተገቢውን ተኩረት ካላገኘ ሰራተኞቹ ስራ እየለቀቁ መሄዳቸው አይቀሬ ነው ያለ ሲሆን ይህ ደግሞ በማገገም ላይ የሚገኘውን የጤና ስርዓት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ብሏል።

ማህበሩ አሁን ላይ እየሰራቸው ስላሉ ስራዎችና እየገጠሙት ስለሚገኙት ችገሮች ለሚመለከታቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና ለፌደራል መንግስት አመራሮች አቅርቧል ያሉት የትግራይ የጤና ባለሙያዎች ማህበር ሊቀመንበሩ ዶ/ር ፍስሀ አሸብር ከችግሮቹ መካከል ያልተከፈለ ውዝፍ ደመወዝ፣ የሙያተኛ ከለለ አለማግኘት ፣ የትራንስፖር አገልግሎት፣ የስራ ቦታ፣ የመኖሪያ ቤት ጥያቄ፣ ነፃ የህክምና አገልግሎት፣ በኮቪድ ጊዜ ለተሰራ ስራ ያልተፈፀመ ክፍያና የደመወዝና የስራ መደብ እርከን እድገት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

ሊቀመንበሩ አክለው ሞያተኛው ያለውን ሁሉ ለመስጠት የሚያስችል ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሞያተኛው እያበረከተው ላለው አስተዋፅኦና እየከፈለው ላለው ዋጋ ተገቢ ክብርና እውቅና ሊሰጠው ይገባል ሲሉም ተደምጠዋል።

ማህበሩ አሁንም እያነሳቸው ያሉ ጥያቄዎች ምንም ምላሽ ሳያጉኙ አመት ከስምንት ወር መቆየታቸው የገለፁት ዶ/ር ፍስሃ የሞያተኛው ጥያቄና ችግር በአፋጣኝ መፍትሄ ካልተበጀለት የትግራይን የጤና ስርዓት አደጋ ውስጥ የሚከት ይሆናል፣ ሞያተኛውም በዚህ ተስፋ በመቁረጥ ስራ እየለቀቀ ይሄዳል ሲሉ መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

ከዚህ ቀደም ማህበሩ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ከሰሜኑ ግጭት ወዲህ 200 ዶክተሮች ጨምሮ ከ915 የህክምና ባለሞያዎች ከስራ ለቀው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው መግለፁ አይዘነጋም።

ከዱባይ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራውስደተኛ Pharmasiset ነኝበማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራው የአንድ ዓመት ከግማሽ ድ...
06/04/2025

ከዱባይ

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና
ጣቢያ ነበር የምሰራው

ስደተኛ Pharmasiset ነኝ

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሀላባ ዞኑ በደኔ ጤና ጣቢያ ነበር የምሰራው የአንድ ዓመት ከግማሽ ድሞዝ ሳይከፈልኝ ኑሮው ቢከብደኝ

የምወድውን ማሕበረሰብ ለሁለት ዓመት ካገለገልኩበት የጤና ተቋም ትቼ ስደት ዱባይ ተሰደድኩኝ::

ነገር ግን በጣም የማዝነው::

አቡድልሰመድ ከዱባይ

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴
# Via ጉርሻ

የዩኒቨርሲቲ ዘበኛ 30 አመት በጊቢው ውስጥ ቢኖር አይመረቅም ግን 30 አመት ሙሉ ቆሞ ያስመርቃል ይለኛልወንድሜ እሱ ከተመረቁት ይሻላል ቢያንስ ስራ አለው ማስታወሻነቱ ለስራ አጥ ጤና ባለሙያ...
08/12/2023

የዩኒቨርሲቲ ዘበኛ 30 አመት በጊቢው ውስጥ ቢኖር አይመረቅም ግን 30 አመት ሙሉ ቆሞ ያስመርቃል ይለኛል
ወንድሜ እሱ ከተመረቁት ይሻላል ቢያንስ ስራ አለው ማስታወሻነቱ ለስራ አጥ ጤና ባለሙያዎች
health info and vacancy news

07/12/2023

በእያንዳንዱ ተቋም በሚታየው የመድሃኒት የአልጋ የሁሉም ማተሪያሎች አለመሟላት ብዙ ጊዜ ጤና ባለሙያዎችን ተጠያቂ ለማድረግ የሚሞከረው ነገር ፍፁም ስህተት ነው ። ጤና በለሙያው የሰራበትን በመከልከል ጭምር እነዛን የመሳሪያ ጉድሎቶች እንዲኖሩ በመሸጥ በማጭበርበር የሚፈፅመው ከታች ከወረዳ ጤና ጣቢያ/ኬላ ጀምሮ እስከ ጤና ሚኒስቴር ያሉ ወንበር ላይ የተቀመጡ ሃላፊዎች ችግር መሆኑን ህብረተሰቡ ሊገነዘብ እና ሊጠይቅ ይገባል።

በአማራ ክልል የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ በጤናው ዘርፍ በርካታ ችግሮችን መፍጠሩን የጤና ባለሙያዎችና ባለሥልጣናት ተናገሩ። የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ከጤና ባለሙያዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላ...
06/12/2023

በአማራ ክልል የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ በጤናው ዘርፍ በርካታ ችግሮችን መፍጠሩን የጤና ባለሙያዎችና ባለሥልጣናት ተናገሩ።
የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ከጤና ባለሙያዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ የተገኙ አንዳንድ የጤና ባለሙያዎች በግብዓት እጥረት ሙሉ የጤና አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ አመልክተዋል።
በምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ መሪጌታ ዘለዓለም መዝገቡ አንደገልፁት በመንገዶች መዘጋት ምክንያት ደም ከደብረማርቆስ ማምጣት ባለመቻሉ ህሙማንን ማገዝ አልተቻለም ብለዋል።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ የህክምና አገልግሎት አስተባባሪ አቶ አምላኩ በላይ በበኩላቸው በዞኑ ያሉ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ክፍት ቢሆኑም መድኃኒት የላቸውም ነው ያሉት። የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱርከሪም መንግሥቱ በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንት 10 ሺህ ቀዶ ህክምና የሚያደርጉ ወገኖች አገልግሎቱን ማግኘት አልቻሉም ብለዋል።
የመንገዶች መዘጋጋት መድኃኒቶችን ከማዕክል ለማምጣት ከፍተኛ ፈተና እንደነበር የተናገሩት የቢሮ ኃላፊው በአውሮፕላንና በደሴ አቅጣጫ ወደ ባሕር ዳር ማስገባት ቢቻለም ከዚያ በኋላ ወደ ተቋማቱ ማድረስ ችግር እንደገጠመ አስረድተዋል።
የኅብረተሰብ ጤና አደጋዎች ባልተለመደ መልኩ በክልሉ በስፋት እንደታዩ የተናገሩት አቶ አብዱርከሪም 5 ሺህ ያህል ሰዎች በኮሌራ በሽታ ተይዘው ወደ 90 ሰዎች መሞታቸውን ገልጠዋል።
የወባ ታማሚዎች ቁጥርም በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ብለዋል። ሰሞኑን በባሕር ዳር የተገኙት የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ተቋም ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ በአማራ ክልል የተከሰቱ የኅብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል።

መረጃው ያገኘነው ከናሁ ቲቪ ነው

አምቡላንስ ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የህክምና ባለሙያዎች ተገድለዋል 🚨‼️👉🏾አምቡላንስ የድሮን ጥቃት የተፈጸመባት ሐሙስ  ኃዳር 20 ከደሴ ከተማ ወደ ወገል ጤና-ደላንታ  የህክምና ባለሙያ...
03/12/2023

አምቡላንስ ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የህክምና ባለሙያዎች ተገድለዋል 🚨‼️

👉🏾አምቡላንስ የድሮን ጥቃት የተፈጸመባት ሐሙስ ኃዳር 20 ከደሴ ከተማ ወደ ወገል ጤና-ደላንታ የህክምና ባለሙያዎች እና መድኅኒት ጭና ስትጏዝ ነበር::

👉🏾በጥቃቱ ዶ/ር ሄኖክ ተስፋዬ : የአምቡላሱ ሹፌር እና ደስታው መረጮ የተባለ ሰው አምቡላንሱ ውስጥ እንዳሉ ህይወታቸው አልፏል::

👉🏾በመንገዱ ላይ የነበሩ 2 ያልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎችም ተገድለዋል::

👉🏾ዶ/ር ጌታቸው የተባለ የህክምና ባለሙያ ከጥቃቱ በተአምር ተርፎ በህክምና ላይ ይገኛል::

👉🏾ወደ ሆስፒታል እየተወሰደ የነበረው የህክምና ቁሳቁስም ሙሉ በሙሉ ወድሟል::

መረጃው የ VOA ነው

"ጤና ባለሙያዎች የሚደርስባቸውን በደል በተለያየ ቦታ  እየገለፁ ቢገኙም ምንም ፍትህ ባለማግኘት  የደፈሩ  ወደፍርድ ቤት ሌሎች ደግሞ  ቁጭ ብለው የወደፊቱን ያልማሉ ።   ጤና ሚኒስቴር በደ...
01/12/2023

"ጤና ባለሙያዎች የሚደርስባቸውን በደል በተለያየ ቦታ እየገለፁ ቢገኙም ምንም ፍትህ ባለማግኘት የደፈሩ ወደፍርድ ቤት ሌሎች ደግሞ ቁጭ ብለው የወደፊቱን ያልማሉ ። ጤና ሚኒስቴር በደል አድርሶባቸው ወደፍርድ ቤት ሄደው በክርክር ላይ ያሉ ጤና ባለሙያዎች እንዳሉ ከሰማን ቆይቷል። ሆኖም ለህግ አልታዘዝም ባይነቱ እንደቀጠለ የሚታወቀው ይህ መስሪያ ቤት በተለያየ ጊዜ በየክፍሎቹ ሃላፊዎች የስር ትዛዝ ቢወጣባቸውም አንድ ጊዜ እረፍት ሌላ ጊዜ ከሃገር ወተዋል እያለ ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ማድረጉን ቀጥሏል ። አሁንም ትዛዝ የወጣባቸው የፋይናንስ ክፍሉ ሃላፊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ድክመት ለፍርድ ቤት ታስረው ቀርበው እንዲያስረዱ ቢታዘዝም ።ጉዳዩን እንዲያስፈፅም የታዘዘው የፌደራል ፖሊስ መስሪያ ቤቱ ድርሰ በመሄድ ቢጠይቅም እረፍት እንደወጣና እስከሰኞ እንደሚመጣ አሳውቀዋል ይህ በንዲ እንዳለ የታዘዘው ፖሊስ በመጣ ጊዜ ግን በመስሪያ ቤቱ ሰዎች ዘንድ የነበረው ወከባና መርበትበት አለፍ ሲልም ጣት መጠቋቆሞች እንደነበሩ ከውጥ ከነማስረጃ ደርሶናል ።ይህ የሚያደርገው የተቋሙ የበላይ ሃላፊ እና ተከታዮቹ እንደሚሆን የታወቀ ነው ።እስከመች የጤና ባለሙያዎች በደል ይቀጥላል ።
በጣም አሳፋሪ ስራ የሚሰራ ነገር ግን ጤና ባለሙያውን እየጠቀምኩ ነው ብሎ በተለያየ ሚዲያ ሲደሰኩር ያሳዝናል ።ትግሉን ግን ሁሉም የስራውን እስኪያገኝ መቀጠል ግዴታ ነው።"
health sector

አንድ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ የሆነዉ ወንድማችን በነርስንግ ሙያ ተምሮ ከተመረቀ 4 ዓመት እንደሆነና የስራ ቅጥር በማጣቱ ምንም ሙያዊ አገልግሎት ሳይሰጥበት የወሰደዉ ሙያ ፈቃድ ጊዜ እያለ...
01/12/2023

አንድ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪ የሆነዉ ወንድማችን በነርስንግ ሙያ ተምሮ ከተመረቀ 4 ዓመት እንደሆነና የስራ ቅጥር በማጣቱ ምንም ሙያዊ አገልግሎት ሳይሰጥበት የወሰደዉ ሙያ ፈቃድ ጊዜ እያለፈ እንደሆነ በተናገረዉ መሰረት መዘገባችን ይታወሳል። ይህንን ወጣት "ስማችንን አጥፍተሃል" የምሉ አካላት ጉዳት እንዳደረሱበት ይናገራል። ጉዳቱም ከፍተኛ በመሆኑ ህክምና ላይ እንዳለ መልዕክቱን አድርሷል።
ቀጣይ በዝርዝር እንመለሳለን።
ምህረቱ ዱኮ ይባላል!
የሐኪሞች ድምፅ

01/12/2023
30/11/2023

#የታመመው የጤና ስርአት በጤና ባለሙያዎች መታከም አለበት
health sectors

29/11/2023

የጤና ባለሙያውን ያላከበረ የጤና ሴክትር አመራር ማለትም ሚ..ር ለህብረተሰቡ ጤና እየሰራው ነው ማለት ከፈረሱ ጋሪውን ማስቀድም አይነት ውሸት ነው።
#የታመመው የጤና ስርአት በጤና ባለሙያዎች መታከም አለበት
health sectors

29/11/2023

የጤና ባለሙያው ለረዥም ጊዜ የቆየበት ፍርሃቱን በማስወገድ በየቦታው በአመራሮች የሚደርሱበትን በደል እና ጤና ተቋማቱ የሚያምዱትን የፖለቲካ ሻጥር በአደባባይ መጋፈጥና መቃወም አለበት።
#የጤናው ዘርፍ እራሱ መታከም አለበት
sectors
የጤና ባለሙያዎች ድምፅ voice of health pfofessionals

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጤና ባለሙያዎች ድምፅ Voice of health professionals posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram