Medical Information

Medical Information በዚህ ገጽ ጤናን የተመለከቱ የሥራ ማስታወቂያዎች፤ ሕይወታዊ ቁም-ነገሮችና አጠቃላይ መረጃዎችን እንለዋወጥበታለን! Medical Media

28/02/2026
28/02/2026



የ Speciality ወይም/እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያ ቀናት እስከ የካቲት 29/2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡

የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) የመግቢያ ፈተና ውጤት መለቀቁ ይታወቃል፡፡

በማስተካከያው ወቅት ተጨማሪ የሬዚደንሲ ( Speciality ) ፕሮግራሞች ያሏቸው ሁለት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።

➫ የካቲት 12 ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ በ Clinical Radiology (ብዛት 4)
➫ የካቲት 12 ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ በ Otolaryngology-HNS (ENT) (ብዛት 4)
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ Wollo በ Clinical Radiology (ብዛት 4)

26/02/2026

ዚምባቡዌ ከአሜሪካ የቀረበላትን የ367 ሚሊየን ዶላር የጤና ድጋፍ እንደማትቀበል ገለጸች።

የዚምባቡዌ መንግስት ከትራምፕ አስተዳደር የቀረበለትን የ367 ሚሊየን ዶላር የጤና ድጋፍ እቅድ የዜጎችን የጤና መረጃንና ወሳኝ ማዕድናትን አሳልፎ ከመስጠት ጋር በተያያዘ እንዳልተቀበለና ከአሜሪካ ጋር ከሚደረገው ድርድር ራሱን እንዳወጣ አስታውቋል።

ዚምባቡዌ ያልተቀበለችው የጤና ድጋፍ አሜሪካ በቅርቡ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ16 የአፍሪካ ሃገሮች ጋር የተፈራረመችውና ከ18 ቢሊየን ዶላር በላይ የተለያዩ በሽታዎችን ለመከላከል ድጋፍ የሰጠችበት ስምምነት ነው።

ዙምባቡዌ የአሜሪካን ኢንሼቲቭ ያልተቀበለችው በፕሬዚዳንት ምናንጋግዋ ትዕዛዝ ሲሆን በሃገሪቱ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ዚምባቡዌ እንደ ኤድስ፣ ቲቢና ወባ ያሉ በሽታዎችን ራሷን ችላ እንደምትፋለም እንደገለጸች ገልጿል።

የኬንያ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የዜጎችን መረጃ አሳልፎ ከመስጠት ጋር በተያያዘ ኬንያ ከአሜሪካ ጋር የፈረመችውን ይህንኑ ስምምነት ማገዱ ይታወሳል።

[ውጤት በቴሌግራም ቻነል] የካቲት 10/2018 ዓ.ም በ16 የፈተና ማዕከላት የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) የመግቢያ ፈተና ውጤት ተለቋል፡፡ ለፈተናው...
24/02/2026

[ውጤት በቴሌግራም ቻነል]



የካቲት 10/2018 ዓ.ም በ16 የፈተና ማዕከላት የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) የመግቢያ ፈተና ውጤት ተለቋል፡፡

ለፈተናው ብቁ ከነበሩ 2,520 ዕጩዎች መካከል 2,246 ዕጩዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

በዕለቱ የተሰጡትን ክፍል I እና ክፍል II ፈተናዎች የወሰዱ ተፈታኞች ውጤት ብቻ ይፋ የተደረገ ሲሆን፤ ክፍል II ፈተናውን ያልወሰዱ ተፈታኞች Incomplete በመሆናቸው ለMatching ብቁ አለመሆናቸው ተገልጿል፡፡

በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተፈታኞች ከዛሬ የካቲት 17/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 26/2018 ዓ.ም ስም፣ መለያ ID፣ ውጤት እና የመፈተኛ ማዕከላችሁን በመግለፅ፤ በጤና ሚኒስቴር የጥሪ መስመር 952 በሥራ ሰዓት ቅሬታችሁን ማቅረብ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

የተገለፀው ውጤት ለሴቶች እና ሥራ አስኪያጆች የሚሰጠውን የአወንታዊ ድጋፍ አያካትትም፡፡ የ5% ድጋፉ በMatching ሶፍትዌሩ አማካኝነት የሚጨመር ይሆናል፡፡

የSpecialty ወይም/እና የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያ ማድረግ የምትፈልጉ ተፈታኞች ከየካቲት 19-26/2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ማስተካከያ ማድረግ እንደምትችሉ ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

ስለ ጨውና ስኳር ማወቅ የሚገባን ወሳኝ እውነታ!ብዙዎቻችን ለምግባችን ጣዕም ስንል የምንጠቀማቸው ጨው እና ስኳር፣ መጠናቸው ሲበዛ "ጸጥተኛ ገዳዮች" (silent killer) ሊሆኑ ይችላሉ። ...
23/02/2026

ስለ ጨውና ስኳር ማወቅ የሚገባን ወሳኝ እውነታ!
ብዙዎቻችን ለምግባችን ጣዕም ስንል የምንጠቀማቸው ጨው እና ስኳር፣ መጠናቸው ሲበዛ "ጸጥተኛ ገዳዮች" (silent killer) ሊሆኑ ይችላሉ። ዛሬ እነዚህን ሁለት ነገሮች በቀን ምን ያህል መጠቀም እንዳለብንና ለጤናችን ያላቸውን ተጽዕኖ በዝርዝር እንይ።
√ 1. ጨው፦ በቀን ስንት ማንኪያ?
ጨው ለሰውነታችን የፈሳሽ መጠንን ለማመጣጠን ቢጠቅምም፣ መጠኑ ሲበዛ ግን ለደም ግፊት ቀዳሚ ጠንቅ ነው።
ለጤናማ ሰው፦ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እንደሚመክረው፣ በቀን ከ 5 ግራም ወይም ከአንድ የሻይ ማንኪያ በላይ ጨው መጠቀም የለብንም።
ለደም ግፊት፣ ለልብ እና ለኩላሊት ታማሚዎች፦ ለእናንተ ጥንቃቄው ጠንከር ይላል! በቀን ከ ግማሽ የሻይ ማንኪያ (1.5 ግራም) በላይ ጨው በፍጹም አይመከርም።
ለምን? ጨው በሰውነት ውስጥ ውሃ እንዲከማች ስለሚያደርግ በልብና በኩላሊት ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል፤ ትንፋሽ መቆራረጥንና የእግር እብጠትንም ያመጣል።
√ 2. ስኳር (Sugar)፦ ጣፋጩ ጠላት!
ሰው ሰራሽ ስኳር ለጤናችን ጠቃሚ ንጥረ ነገር ባይኖረውም፣ ለውፍረትና ለልብ ህመም ግን ዋነኛው ምክንያት ነው።
የሚመከረው መጠን፦ አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከ 25 እስከ 30 ግራም (ከ6 እስከ 9 የሻይ ማንኪያ) በላይ ስኳር መውሰድ የለበትም።
ልብ በሉ፦ አንድ ጣሳ ለስላሳ መጠጥ ብቻ እስከ 10 የሻይ ማንኪያ ስኳር ሊኖረው ይችላል! ይህም ማለት አንድ ለስላሳ መጠጥ ብቻ የቀን ፍላጎታችንን ያጠናቅቃል ማለት ነው።
√ ምን እናድርግ? (ተግባራዊ መፍትሄዎች)
በቅመም ተኩ፦ በምግብ ላይ ጨው ከመጨመር ይልቅ እንደ ነጭ ሽንኩርት፣ ዝንጅብል፣ ሎሚና እርድ ያሉ ተፈጥሯዊ ቅመሞችን በመጠቀም ጣዕሙን ያጣፍጡ።
መለያዎችን (Labels) ያንብቡ፦ የታሸጉ ምግቦችን ሲገዙ "Sodium" እና "Sugar" መጠናቸው ዝቅተኛ መሆኑን ያረጋግጡ።
ውሃን ጓደኛ ያድርጉ፦ ጥማትን በጣፋጭ መጠጥ ሳይሆን በውሃ ይልመዱ።
ልጅዎን ያስለምዱ፦ ልጆች ገና ከጅምሩ በዝቅተኛ ጨውና ስኳር እንዲያድጉ ማድረግ ለወደፊት ጤናቸው ትልቅ ኢንቨስትመንት ነው።
????? እስቲ እንወያይ!
1. እናንተ በቀን በአማካይ ስንት ማንኪያ ስኳር በሻይ ወይም በቡና ውስጥ ትጠቀማላችሁ?
2. በቤተሰባችሁ ውስጥ የደም ግፊት ወይም የልብ ህመም ያለበት ሰው አለ? ጨው መቀነስ የረዳቸው አሉ?
ሃሳባችሁን በኮሜንት አጋሩን!
ይህ መረጃ ለሌሎች እንዲደርስ Like እና Share በማድረግ ጤናማ ማህበረሰብ እንገንባ!
ዶ/ር ዳዊት ዳርዛ ( ጠቅላላ ሐኪም)
Sources: 1. WHO Guideline: Sodium intake for adults and children
2. WHO Guideline: Sugars intake for adults and children
3. AHA- Added sugars and Sodium Limits

 If the path feels messy, unpredictable, and tough - you’re probably doing it right.Success isn’t linear. It’s earned th...
23/02/2026


If the path feels messy, unpredictable, and tough - you’re probably doing it right.
Success isn’t linear. It’s earned through persistence.
Keep showing up!

21/02/2026


1️⃣ Which of the following is the first-line treatment for uncomplicated malaria in Ethiopia according to national guidelines?
A) Chloroquine
B) Artemether–Lumefantrine
C) Quinine
D) Doxycycline

2️⃣ A patient presents with BP ≥140/90 mmHg on two separate readings. According to current hypertension classification, this is:
A) Normal
B) Elevated
C) Stage 1 Hypertension
D) Hypertensive crisis

3️⃣ Which of the following is the most common cause of chronic liver disease in sub-Saharan Africa?
A) Hepatitis B
B) Alcohol
C) Hepatitis C
D) Autoimmune hepatitis

4️⃣ In a patient with diabetic ketoacidosis (DKA), the initial management priority is:
A) Immediate insulin bolus before fluids
B) Rapid bicarbonate infusion
C) Aggressive IV fluid resuscitation
D) Oral hypoglycemics

5️⃣ Which antibiotic is recommended as first-line therapy for community-acquired pneumonia in otherwise healthy adults?
A) Ceftriaxone
B) Azithromycin
C) Vancomycin
D) Meropenem

👌
20/02/2026

👌

Open Fellowship Positions at the African Union(Application link: The First Comment)1. Data Analytics & Monitoring System...
20/02/2026

Open Fellowship Positions at the African Union
(Application link: The First Comment)

1. Data Analytics & Monitoring Systems – Water & Sanitation (AMCOW)
2. Digital Product & Programme Systems – AUDA-NEPAD Coordination Unit
3. Digital Communications – Cabinet of the Deputy Chairperson
4. ERP SAP & Business Intelligence – AU ERP Unit
5. ESTI Full-Stack Development – Science, Technology & Innovation Department
6. HR Digital Systems & Processes Analyst – Human Resources
7. ICD Full-Stack Developer – Information & Communication Directorate
8. MIS Business Analyst – Management Information Systems Directorate
9. MIS Full-Stack Developer – Management Information Systems Directorate
10. ODG Data Analyst – Office of the Director General
11. WGYD Data Analyst – Women, Gender, and Youth Directorate
12. WGYD Full-Stack Developer – Women, Gender, and Youth Directorate

Literally means፡ ‘የተረፈ ዓበል ስላለን በሥልክ ከምንነግራችሁ ብትመጡስ..."
20/02/2026

Literally means፡ ‘የተረፈ ዓበል ስላለን በሥልክ ከምንነግራችሁ ብትመጡስ..."

19/02/2026

ስለፖስት ቤዚክ ትምህርት በቴሌግራም ቻነል ይከታተሉ!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Medical Information posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Medical Information:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Our Story

Feed Health Information