Medical Information

Medical Information በዚህ ገጽ ጤናን የተመለከቱ የሥራ ማስታወቂያዎች፤ ሕይወታዊ ቁም-ነገሮችና አጠቃላይ መረጃዎችን እንለዋወጥበታለን! Medical Media

ወገን መጥተናል!
30/12/2025

ወገን መጥተናል!

28/12/2025

ከግል ሆስፒታል ማስታወቂያዎች በስተጀርባ ያለው እውነት

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምንያየው ኮከብ ዶክተር ማስታወቂያ በእውነቱ ምን ይሸፍናል?

ሕክምና የቡድን ስራ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ብዙ ሆስፒታሎች በጣም ልምድ ያላቸው ዶክተሮቻቸውን እና ስፔሻሊስቶችን በሚያጎሉ አንጸባራቂ ማስታወቂያዎች ላይ ተመርኩዘዋል። እነዚህ ዘመቻዎች ብዙውን ጊዜ የፍፁምነት ስሜት ይፈጥራሉ ጥቂት ከፍተኛ ሐኪሞች ብቻ እንከን የለሽ የታካሚ እንክብካቤን እንደሚያረጋግጡ።
እውነታው ግን በጣም የተለየ ልሆን ይችላል። የጤና እንክብካቤ የአንድ፣ የሁለት ወይም የሶስት ሰዎች ስራ ብቻ አይደለም። ሁሉን አቀፍ፣ ሁለገብ ቡድን ውጤት ነው (ሐክሞች፣ ነርሶች፣ ሌሎች ባለሙያዎች፣ ቴክኒሻኖች እና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ሁሉም አብረው ይሰራሉ። ያለዚህ የጋራ ጥረት "ፍጹም እንክብካቤ" ተስፋ ሊኖረው አይችልም።

የተደበቀ ተቃርኖ

ሆስፒታሎች "ኮከብ ዶክተሮቻቸውን" በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲያሳዩ፣ ከትዕይንቱ በስተጀርባ አዲስ የተመረቁ ባለሙያዎችን በንቃት ይቀጥራሉ- ብዙን ጊዜ በዝቅተኛ ደሞዝ ! እነዚህ ወጣት ባለሙያዎች አንዳንድ ጊዜ በቂ ስልጠና ወይም ልምድ ሳይኖራቸው እንደ አይሲዩ፣ ድንገተኛ ክፍል ወይም ሌላ ክፍል ባሉ ወሳኝ ቦታዎች እንደ ሁነታው ልመደቡ ይችላሉ።
ይህ አካሄድ ከተዋወቀው የልህቀት ምስል ጋር የሚቃረን ብቻ ሳይሆን ለታካሚ ደህንነትም አደጋን ልፈጥር ይችላል። ልምድ ያካበቱ ጤና ባለሙያዎች በአንድ ጊዜ በብዙ ቦታዎች ላይ መገኘት አይችሉም። ይህን ክፍተት ለመሸፈን በበቂ ሁኔታ ለቦታው ያልሰለጠኑ ሰራተኞችን በወሳኝ ቦታዎች ላይ መድበው ማሰራት ለታካሚዎችም ሆነ ለባለሙያዎች ፍትሃዊ አይደለም።

የቡድን ስራ ለምን አስፈላጊ ሆነ?

የታካሚ እንክብካቤ አንድ አንዴ ውስብስብ ነው ።አንድ ሐኪም ብቻውን ሁሉን ነገር መስራት እንደማይችል ይታወቃል ።
ነገር ግን የቡድን ሥራ የታካሚን ጤንነትና ደህንነትን ያረጋግጣል( እያንዳንዱ ባለሙያ ታካሚዎችን ለመፈወስ የሚረዱ የተለያዩ አመለካከቶችን እና እውቀቶችን ያመጣል)።
አዳዲስ ክህሎቶችን፣ እውቀትን እና ትኩስ ጉልበትን ለቡድኑ የሚያመጡ አዳዲስ ባለሙያዎችም ያስፈልጋሉ። ነገር ግን ብቻቸውን ከመስራታቸው በፊት አቅም ግንባታ ስልጠናዎች እና የተዋቀረ የሥራ መመሪያ ልያስፈልጋቸው ይችላል።
ሁሉንም የቡድን አባላት ማክበር የጤና ባለሙያዎችን ሞራል እንዲሁም የታካሚ እንክብካቤን ጥራት ያጠናክራል።

ሐቀኝነት እና ግንዛቤ

የግል ሆስፒታሎች ማስታወቂያዎቻቸው እውነታውን የሚያንፀባርቅ መሆኑን ማረጋገጥ አለባቸው። በላቀ ደረጃ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን ካሉ በተገቢው ስርዓት፣ ስልጠና እና በጠንካራ ቡድን ስራ መደገፍ አለበት።
እርስዎ ማወቅ ያለባችሁ ነገር ሆስፒታል በሚመርጡበት ጊዜ በማስታወቂያ ሰሌዳዎች በቲቪ ወይም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚያዩዋቸው ተጽዕኖ ብቻ መሆን የለበትም ብየ አምናለሁ ።
እርስዎን ስለሚንከባከበው የሕክምና ቡድን በሙሉ ማወቅ ጠቃሚ ነው - ምክንያቱም ትክክለኛ እና ደህንነቱን የጠበቀ ሕክምና አገልግሎት የሚመጣው ከቡድን ስራ እንጂ ከግለሰቦች እውቅና አይደለም።
Dr. Lemi Bayisa

Medical Information

ነጋ ጠባ ስለስኳር የሚሰራጩ አሳች መረጃዎችን ለመግታት ምን እናድረግ? በየለቱ ስለስኳር እና መሰል ህመሞች የተሳሳቱ መረጃዎች ይለቀቃሉ። አንዳንዱ ከእውቀት ማነስ፣ ሌላው በሚያስጨንቀን ጤናች...
27/12/2025

ነጋ ጠባ ስለስኳር የሚሰራጩ አሳች መረጃዎችን ለመግታት ምን እናድረግ?

በየለቱ ስለስኳር እና መሰል ህመሞች የተሳሳቱ መረጃዎች ይለቀቃሉ። አንዳንዱ ከእውቀት ማነስ፣ ሌላው በሚያስጨንቀን ጤናችን አወጫብሮ ለማትረፍ፣ ሌላው ለእኩይ አላማው ብሎ ሃሰተኛ መረጃ ይለጥፋል። በተቻለን መጠን ቢያንስ ባለማወቅ ወይም በተሳሳተ መንገድ ከመረዳት የሚመጣን መረጃዎች ለማጥራት እንጥራለን። ነገር ግን ለእያንዳንዱ የይገባኛል፣ የአድናለሁ፣ የእፈውሳለሁ አሳቾች ምላሽ መስጠት የሚቻል አይደለም። የተሳሳተ መረጃ ዥረቱ ፈጣን ነው፣ ትኩረት ለመሳብ ተብሎ ታስቦበት የሚሰራ ስለሆነ በየለቱ ተግባር (የህክምና ስራ፣ የማስተማር ስራ፣ የምርምር ስራ፣ የግል ህይወት ወዘተ) ላለው ባለሙያ አይሆንም።

የእኔ የግል ምክሬ እንደሚከተለው ይሆናል፤

🔑 ለጤና ሚኒስቴር እና መሰል ባለድርሻ አካላት

ኢትዮጵያ የኦንላይን የጤና መረጃን በተመለከተ የህግ ማዕቀፍ ያስፈልጋታል። የጤና መረጃን ማጋራት የሚችለው ማነው? በሚለጠፉት መረጃዎች ጉዳት ቢደርስ ተጠያቂነት እንዴት ይሰፍናል? ለደረሰ ጉዳት እንዴት ይካሳል? አደገኛ ይዘቶች እንዳይታዩ ማገድ? የሚሉትን የሚመልስ ህግ እና ደንብ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ የደረስን ይመስለኛል። ካለም አሳውቁን!

ከዚህ ባሻገር በሳይንሳዊ ማስረጃ ላይ የተመሰረቱ የጤና ምክሮችን በሰፊው ማዳረስ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው። ሚኒስትሩ ሁሉንም መስራት ላይቻለው ስለሚችል የተረጋገጡ የባለሙያዎች ቻናሎችን ሁለገብ ድጋፍ በማድረግ እንዲጠናከሩ፣ የበለጠ ተደራሽ እንዲሆኑ ማገዝ ይገባል።

👨‍⚕️ ለጤና ባለሙያዎች

አፋጣኝ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ከፍተኛ ስጋት ያላቸውን የተሳሳቱ መረጃዎች ሲለቀቁ ወዲያዉኑ ምላሽ መስጠት ይገባል። አንዳንድ አሳሽ መረጃዎች ህይወት አድን መድሃኒቶችን ማቆም የሚገፋፉ ሲሆኑ በፍጥነት የሚያጸና ትክክለኛ መረጃ ማውጣት ይፈልጋል።

ሰዎች በተደጋጋሚ ሊጠቅሷቸው የሚችሏቸውን የጤና ጉዳዮች በአጀንዳነት ቀርጾ በየጊዜው ማብራሪያዎችን መስጠት ይገባል። እነዚህ አሳች ግለሰቦች እና ቡድኖች እንካስላንቲያ ከመመላለስ ይልቅ የህዝቡን የጤና እውቀትን ማጠናከር ላይ ማተኮር ይሻላል። እነዚህ ጽንፍ የያዙ አሳቾች በውይይት እና ክርክር አያምኑም። የሚያስቆማቸው ህግ ብቻ ነው። ቆንጣጭ ህግ እስኪመጣ ተመልካች ማስራብ ነው።

🧍‍♂️ 🧍‍♀️ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን

ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የማስተላልፈው መልእክት እንዲያው የቸገረህን ነገር በማነሳሳት ‘ለማመን የሚከብድ‘ የሚመስል ወሬ የሚነዙ ግለሰብ ወይ ተቋማት ስታገኝ መጀመሪያ ጠይቅ፣ ደጋግመህ መርምር። ቀጥሎ የተረጋገጠ የህክምና ባለሙያ ጋር በመነጋገር አሁናዊ የህክምና መረጃ ምን ይላል ብሎ ተጨማሪ መረጃ ሰብስብ። ከዚያ ይሻላል ያልከውን አማራጭ ማድረግ። አለዚያ በየማህበራዊ ሚዲያው የሚነዙትን ስራ ፈቶች በየቀኑ የባለሙያ መልስ መስጠት አይቻልም።

insurance
27/12/2025

insurance

Maraki Health Center has successfully transitioned all patient record-keeping to a fully digital system!
26/12/2025

Maraki Health Center has successfully transitioned all patient record-keeping to a fully digital system!

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ | አማራ ክልል ጤና ቢሮ  #341 ጤና ባለሙያዎች በዜሮ ልምድ የቅጥር ማስታወቂያየሙያው ዓይነት       ተፈላጊ ብዛትHealth officer   15Pharmacy pr...
26/12/2025

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ | አማራ ክልል ጤና ቢሮ #341 ጤና ባለሙያዎች በዜሮ ልምድ የቅጥር ማስታወቂያ

የሙያው ዓይነት ተፈላጊ ብዛት
Health officer 15
Pharmacy professional 20
Pharmacy technician 10
Laboratory technologist 20
Laboratory technician 10
Nurse professional 30
level 4 nurse 10
Midwifry professional 20
Midwifery level 4 10
Anesthetics professional 20
Anesthesia level 5 33
Environmental helth degree 10
Environmental health diploma 23
Radiographer degre 15
Radiographer diploma 10
Health extension 40
Psychiatry professional 10
Biomedical engineer 10
Health informatics degree 10
Health informatics diploma lo

የመመዝገቢያ ቀን ማስታወቂያው ከወጣ ጀምሮ ለ7 ተከታታይ የስራ ቀናት

ደመወዝ በአዲሱ የደመወዝ ካርየር
የመመዝገቢያ ቦታ በሁሉም ዞን ጤና መምሪያዎች
የፈተና ቀን 05/05/2018

Teda Health Science College‎በጎንደር ክላስተር የአካል ድጋፍ እያደረገ የሚገኘው የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የድጋፍና ክትትል ቡድን በጎንደር የሚገኘውን የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅን ተመ...
26/12/2025

Teda Health Science College

‎በጎንደር ክላስተር የአካል ድጋፍ እያደረገ የሚገኘው የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የድጋፍና ክትትል ቡድን በጎንደር የሚገኘውን የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅን ተመልክቷል።

‎የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አበበ ተምትሜ ከኮሌጁ አመራሮችና የማኔጅመንት አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት የክልሉ መንግሥት የጤና አገልግሎትን ለመስጠት በሚያደርገው ጥረት የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅ የበኩሉን ተቋማዊ ሃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

‎መንግስት ለህብረተሰቡ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የጠቁሙት አቶ አበበ፣ ለጤናው መስክ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

‎ኮሌጁ የተሻለ የጤና ባለሙያዎች ለማፍራት የሚያደርገው ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የክልሉ ጤና ቢሮ ሁሉን አቀፍ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

‎በመጨረሻም ኮሌጁ በውስጥ ገቢ፣ ማህበረሰቡን በማስተባበርና ሃብት በማፈላለግ የኮሌጁን ገጽታ ለመቀየር እያደረገ ላለው ጥረት የኮሌጁን አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላትንና መምህራንን አመስግነዋል።

‎የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ Zemene Habtu በበኩላቸው ኮሌጁ በጤናው ዘርፍ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማፍራት የሚጠበቅበትን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ኮሌጁ ከጎንደር ከተማ 27 ኪ/ሜ ርቀት ላይ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዲኑ ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን እውቀት በተግባር ማስደገፍ የሚያስችል የተሟላ ላብራቶሪ ማዕከል መኖሩንም ተናግረዋል።

‎የጤና ሙያ ሰብዓዊነትን የሚጠይቅ መሆኑን ያነሱት ዲኑ ተማሪዎች ችግር ፈች ምርምሮችን በማካሄድ ማህበረሰቡን እንዲያግዙ ማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

‎የመመሪያ ይሻሻልን፣ የመምህራን ጥቅማ ጥቅም፣ የመሰረተ ልማትና ሌሎች ጥያቄዎች እንዲፈቱ ያነሱት አቶ ዘመነ ቢሮው ለአሰራር አመቺ ያልሆኑትን ጉዳዮች አይቶ መልስ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

‎ባለፉት 21 ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች የመማር ማስተማርና የምርምር ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የጠቁሙት የኮሌጁ አካዳሚክ ዲን አቶ ታደለ ማሩ- Tade M Andargie ፣ የተለያዩ የልማት ዕቅዶች እንዲሳኩም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡

‎ሃብት በማሰባሰብ፣ በማህበረሰብ አገልግሎት እና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተቋማዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ የጠቆሙት አቶ ታደለ ኮሌጁ እያስተማራቸው ከሚገኙ 1750 ተማሪዎች መካከል ለ96 ተማሪዎች የነጻ የትምህርት ዕድል መሰጠቱን ገልጸዋል።

‎ኮሌጁ ለአጥር ግንባታ ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉንም አመልክተዋል።

‎በ1997 ዓ.ም መደበኛ ሥራውን የጀመረው ጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጤናው ዘርፍ በርካታ ባለሙያዎችን ማፍራቱን የገለጹት አቶ ታደለ በዲፕሎማ የጤና ዘርፍ ሲያበረክተው ከነበረው አስተዋጽኦ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅትም በጤናው ዘርፍ በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐ ግብር ተማሪዎቹን ተቀብሎ እያስተማረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

‎ኮሌጁ በነርሲንግ፣ በፋርማሲ ቴክኒሽያን፣ በሜዲካል ላብራቶሪ፣ በሚድ ዋይፈሪ ፣ በጤና መረጃ ቴክኒሽያን ጨምሮ በልዩ ልዩ የትምህርት ዘርፎች እያሰለጠነ ይገኛል።
- ዘገባው የክልሉ ጤና ቢሮ ነው፡፡

AI is no longer optional in higher education, it’s essential.This seminar is a timely step toward shaping how AI is taug...
26/12/2025

AI is no longer optional in higher education, it’s essential.
This seminar is a timely step toward shaping how AI is taught, governed, and applied in academia.

You are cordially invited!

የቀድሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፊዚዮሎጂ አስተማሪ ፕሮፌሰር የቆየ አበበ በሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። የቀብር ሥርዓት ቅዳሜ ታኅሣስ 18, 2018 በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማ...
26/12/2025

የቀድሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፊዚዮሎጂ አስተማሪ ፕሮፌሰር የቆየ አበበ በሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። የቀብር ሥርዓት ቅዳሜ ታኅሣስ 18, 2018 በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል። ለአገልግሎታቸው እናመሰግናለን። ለወዳጆቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

”በአዲሱ ደመወዝ ዲዩቲ ስለተከፈለ ከቀጣይ ወር ደወመዝ እንቆርጣለን" 🤔
25/12/2025

”በአዲሱ ደመወዝ ዲዩቲ ስለተከፈለ ከቀጣይ ወር ደወመዝ እንቆርጣለን" 🤔

24/12/2025

Just saw Safaricom Ethiopia’s new data prices... nearly double what Ethio telecom charges for similar packages! While improving service quality is important, such a huge increase is hard for regular users to swallow. To Ethio telecom 🏃‍♂️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Medical Information posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Medical Information:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Our Story

Feed Health Information