Medical Information

Medical Information በዚህ ገጽ ጤናን የተመለከቱ የሥራ ማስታወቂያዎች፤ ሕይወታዊ ቁም-ነገሮችና አጠቃላይ መረጃዎችን እንለዋወጥበታለን! Medical Media

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 167 ተማሪዎች አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል 16ቱ የሕክምና ዶክተሮች መሆናቸው ተገልጿል።የተቋሙ 12ኛ ዙር ተመራቂዎች 12...
29/03/2026

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 167 ተማሪዎች አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 16ቱ የሕክምና ዶክተሮች መሆናቸው ተገልጿል።
የተቋሙ 12ኛ ዙር ተመራቂዎች 121 በመጀመሪያ ዲግሪ እና 46 በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

  ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 907 ተማሪዎች አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው 17ኛ ዙር ተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ፣  በሕክምና ዶክትሬት እና በሁለተኛ ዲግሪ ...
29/03/2026



ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 907 ተማሪዎች አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው 17ኛ ዙር ተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሕክምና ዶክትሬት እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

🟥የጥራት ችግር ያለበትን መድኃኒት እንዲመለስ ስለማሳሰብ!
29/03/2026

🟥
የጥራት ችግር ያለበትን መድኃኒት እንዲመለስ ስለማሳሰብ!

  ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ 21 የስፔሻሊቲ ሐኪሞችን ለመጀመሪያ ጊዜ አስመረቀ።ዩኒቨርሲቲው በተጨማሪም በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 417 ተማሪዎችን አስመ...
28/03/2026



ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ 21 የስፔሻሊቲ ሐኪሞችን ለመጀመሪያ ጊዜ አስመረቀ።

ዩኒቨርሲቲው በተጨማሪም በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 417 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ተማሪ አቡጎሽ ተስፋዬ ከሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል 3.95 አጠቃላይ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ እና የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።

ዩኒቨርሲቲው የሴቶች የመብት ትግል ፋና ወጊ በሆነችው "የቃቄ ውርድወት" ስም የተሰየመ ዘመናዊ የመመረቂያ አዳራሽ ሥራ አስጀምሯል።

28/03/2026

የአማራ ክልል የሕክምና ማኅበር፣ የክልሉ የጤና ሙያተኞች በከፍተኛ ጫና ውስጥ ኾነው ከ7 ወር በላይ የሠሩበት የትርፍ ሰዓት ክፍያ እና የተጋላጭነት ክፍያ ባስቸኳይ አንዲከፈላቸው ጠየቀ። ማኅበሩ፣ መንግሥት ለጤና ባለሙያዎች ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎትና ነጻ የቤት መስሪያ መሬት ወይም የረጅም ጊዜ ብድር አገልግሎተ እንዲያመቻችም ጠይቋል። የባለሙያዎች የደሞዝና የጥቅማጥቅም መመሪያዎች ተግባራዊ ባለመኾናቸው ሙያተኞችን ለከፍተኛ "ማኅበራዊ" እና "ኢኮኖሚያዊ" ቀውስ አጋልጧል ያለው ማኅበሩ፣ ለጉዳዩ ኃላፊነት ወስዶ ምላሽ የሚሠጥ አካል የለም ሲል አማሯል።

  የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 255 የሕክምና ባለሙያዎችን አስመረቀ፡፡ዩኒቨርሲቲው 190 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 52 በስፔሻሊቲ እና 13 በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ...
28/03/2026



የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 255 የሕክምና ባለሙያዎችን አስመረቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው 190 በመጀመሪያ ዲግሪ፣ 52 በስፔሻሊቲ እና 13 በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በእኩል ነጥብ የሜዳሊያ ተሸላሚዎቹ 👏

ከአጠቃላይ ተመራቂዎች ተማሪ ፍቅር ገብሩ ከፊዚዮቴራፒ ትምህርት ክፍል እና ተማሪ ነብዩ ዳዊት ከነርሲንግ ትምህርት ክፍል እኩል 3.98 CGPA በማምጣት የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል።

 ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2,300 ተማሪዎች አስመርቋል። የዩኒቨርሲቲው 19ኛው ዙር ተመራቂዎች በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሐግብሮች  በ...
28/03/2026



ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2,300 ተማሪዎች አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው 19ኛው ዙር ተመራቂዎች በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሐግብሮች

በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD)፣ በስፔሻሊቲ እና በPGDT ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

25/03/2026
  ከአሰቃቂ የጅብ ጥቃት መትረፍ  የተቀናጀ የሕክምና ዕርዳታ ውጤት !አንድ ህጻን በጅብ ጥቃት ምክንያት በደረሰበት ከፍተኛ የፊት አካል ጉዳት ምክንያት ወደ አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆ...
25/03/2026



ከአሰቃቂ የጅብ ጥቃት መትረፍ የተቀናጀ የሕክምና ዕርዳታ ውጤት !

አንድ ህጻን በጅብ ጥቃት ምክንያት በደረሰበት ከፍተኛ የፊት አካል ጉዳት ምክንያት ወደ አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል በሪፈር ይላካል።

በጥቃቱ ምክንያት ህጻኑ ሁለቱንም ዓይኖቹን ያጣ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ማየት አይችልም። ከዚህ በተጨማሪ በዓይን አካባቢ፣ በግንባር እና በሁለቱ ጉንጮች ላይ ያለው ቆዳ በጣም ተጎድቶ ነበር። የላይኛው መንጋጋ (maxilla) ከፊል ጠፍቶ የቀሩት አጥንቶች ደግሞ ተሰባብረው ነበር።

ህጻኑ ወዲያውኑ ወደ ህጻናት ጽኑ ህክምና ክፍል (PICU) በመግባት የህይወት አድን ህክምና ተደርጓል። እንዲተነፍስ በአንገቱ በኩል ቀዳዳ በመክፈት (Tracheostomy) ተደርጓል።

በቀጣዮቹ ቀናት የቀዶ ጥገና ቡድኑ ኢንፌክሽንን ለመከላከል እና የሞቱ ቲሹዎችን ለማስወገድ ተከታታይ የጽዳት ሂደቶች (debridement) አከናውኗል።

ቁስሉ ለተሃድሶ ቀዶ ህክምና ዝግጁ ከሆነ በኋላ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ተጀምረዋል ፦

1. የቆዳና ቲሹ ንቅለ ተከላ (Free Tissue Transfer)

የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች ከህጻኑ ጭን ላይ 7 ሴ.ሜ x 17 ሴ.ሜ መጠን ያለው ቆዳና ስጋ ከነ ደም ስሩ በመውሰድ ወደ ፊት ተተክሏል። ይህም በጥቃቅን የደም ስር ቀዶ ጥገና (Microsurgery) ቴክኒክ ከፊት ያሉ የደም ስሮች ጋር ተገናኝቶ ተሰርቷል።

2. የአጥንት ተሃድሶ ህክምና

የተሰባበሩት የመንጋጋ አጥንቶች ተስተካክለው የፊት ቅርጽ እንዲመለስ በታይታኒየም ፕሌት እና ስክሩ ተደግፈዋል።

እስካሁን ድረስ ህጻኑ ቢያንስ 8 ቀዶ ጥገናዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ይፈልጋሉ። በአሁኑ ወቅት ህጻኑ በመሻሻል ላይ ይገኛል።

ይህ ክስተት የተቀናጀ የህክምና ቡድን (Multidisciplinary Team Approach) ያለውን ትልቅ ፋይዳ እንደሚያሳይ ተገልጿል።

የህጻናት ሐኪሞች፣ የጽኑ ህክምና ባለሙያዎች፣ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና እና የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስቶች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የህጻኑን ህይወት ለማዳን እና የፊቱን ቅርጽ ለመመለስ ተግተዋል።

ነገር ግን ይህ አደጋ ብቸኛው አይደለም፤ በአሁኑ ጊዜ በተመሳሳይ የጅብ ጥቃት ጉዳት የደረሰበት ሌላ ህጻን በሆስፒታሉ ተጨማሪ ቀዶ ህክምና በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።

ህፃናትን ከጅብ ጥቃት ለመጠበቅ ማህበረሰቡ ህፃናትን ብቻቸውን ባለመተው፣ ንቁ እንክብካቤ በማድረግ እና የመከላከያ እርምጃዎች መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የተሃድሶ ቀዶ ጥገና (Reconstructive Microsurgery) የጠፋውን መልክና ተግባር ሊመልስ ቢችልም፣ ከሁሉ በላይ ግን አደጋን ከመጀመሪያው መከላከል ነው ዋናው መፍትሄ።

በቀዶ ጥገናው የተሳተፉ ባለሙያዎች፦
• ዶ/ር አብዱረዛቅ አሊ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና ማይክሮሰርጅን (መሪ ሀኪም)
• ዶ/ር አታክልቲ ባራኪ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና የእጅ ቀዶ ጥገና ሀኪም
• ዶ/ር ዘቢባ መካ – የፕላስቲክ ሪኮንስትራክቲቭ ሀኪም
• ዶ/ር ተስፋሁን አሊ – ሬዚደንት
• ዶ/ር ዮሃንስ ኤሊያስ – ፌሎው
• ሲራጅ ሙሼ – ማደንዝዣ ባለሙያ
• ናትናኤል ብርሃኑ – ነርስ
• ጫልቱ ተገኔ – ነርስ
• አለሙ ቦጋለ – ነርስ
• ኪሩቤል እሸቱ – ፖርተር
• አባይነው ሰውነት – ፖርተር
• ዘቢደር ፈንቴ – ጽዳት
• እና ሌሎች በርካታ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

(አለርት ኮምፕረሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል)

25/03/2026

በጤና ዙሪያ የሚሠሩ የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበራት፣ አውሮፓ ኅብረትና የበለጸጉ አገራት ታዳጊ አገራትን የሚጠቅም ዓለማቀፍ የጤና ርትዕ እንዳይሠፍን እንቅፋት ኾነዋል በማለት ወቀሡ። ድርጅቶቹ፣ ኅብረቱና የበለጸጉ አገራት አዲሱን የዓለም ጤና ድርጅት የወረርሽኝ መከላከያ ስምምነት አንቀጽ 12 እንዲቀበሉ ጠይቀዋል። የስምምነቱ አንቀጽ 12፣ የወረርሽኝ ክትባቶችንና መድሃኒቶችን ለመስራት የሚረዱና የፓቶጅን ናሙናዎችና ክትባቶች በድርጅቱ በኩል ለሁሉም አገራት በፍትሃዊነት ተደራሽ እንዲኾኑና ጥቅሞችን የመጋራት "አስገዳጅ" ሥርዓት እንዲኖር የሚጠይቅ ነው። ድርጅቶቹ፣ የፓቶጅን ናሙናዎችን በሚስጢር በመያዝ የትርፍ ማካበቻ ብቻ ማድረግ ኢ-ፍትሃዊነት ነው በማለት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። የበለጸጉ አገራት የወረርሽኝ ክትባቶችና መድሃኒቶች አምራች ፋብሪካዎች፣ የፈጠራ መብታቸውን ለታዳጊ አገራት ኩባንያዎች እንዲሸጡና ታዳጊ አገራትም ክትባቶችንና መድሃኒቶችን እንዲያመርቱ እንዲፈቅዱም ድርጅቶቹ ጥሪ አድርገዋል። አባል አገራት በስምምነቱ አንቀጽ 12 ላይ ከመጪው ግንቦት በፊት መስማማት ይጠበቅባቸዋል።

Via ዋዜማ

25/03/2026

“When you use AI, think about it like this. Imagine you have a supervisor professor. You don’t meet him/her without having some results. You don’t call him/her frequently. You don’t ask him/her every move. Instead, you try first in your own way, then you go to him/her to refine and improve the important parts.

Again, imagine you need an important idea from an expert. Before you meet him/her, you should at least understand your challenges. Otherwise, even a good idea becomes useless. Don’t attach every daily activity to AI. Use it as an expert to maximize your productivity, and even then, only in specific areas where it is well-trained.

As we master AI in this way, our creativity improves. AI stops being a threat and becomes a strategic partner in our journey forward.”

Worku Abebe (PhD)
Dean, College of Informatics

“AI-ን ስትጠቀሙ ፕሮፌሰራችሁን አስቡ ፤ ውጤት ሳይኖራችሁ ፕሮፌሰር ጋር አትሄዱም ፤ በየደቂቃውም ስልክ አትደውሉም ፤ እንዲሁም እያንዳንዱን እንቅስቃሴ አታማክሩትም። ይልቁንም መጀመሪያ በራሳችሁ መንገድ ትሞክራላችሁ ፤ ከዚያም ዋና ዋና ነጥቦችን ለማረምና ከፍ ወዳለው ምዕራፍ እንዲያሸጋግራችሁ ወደ እርሱ ትሄዳላችሁ።

በድጋሜ አስቡት ፤ ከአንድ እውቅ ባለሙያ ጠቃሚ ሃሳብ ሲያስፈልጋችሁ መጀመሪያ የራሳችሁን ተግዳሮቶች በደንብ መረዳት አለባችሁ። ካልሆነ ግን ጥሩ ሃሳብ እንኳ ቢሰጣችሁ ዋጋ ቢስ ይሆናል።

ሁሉንም የዕለት ተዕለት ተግባራችሁን ከAI ጋር አታገናኙ። ውጤታማነቻችሁን ለማሳደግ እንደ አንድ ‘ከፍተኛ ባለሙያ' (Expert) ብቻ ተጠቀሙበት። ለዚያውም በተመረጡና በደንብ በሰለጠነበት ሁኔታ ላይ ብቻ፡፡

AI-ን በዚህ መንገድ በተጠቀምን ቁጥር የፈጠራ ክህሎታችን እያደገ AI-ም ስጋት መሆኑ ቀርቶ አጋርነቱን እየተረዳን እንቀጥላለን፡፡”

ወርቁ አበበ (ፒ.ኤች.ዲ)
የኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ዲን

  አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 946 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡ተመራቂዎቹ በቅድመ-ምረቃ (699) እና በድኅረ-ምረቃ (247) የትምህርት መር...
25/03/2026



አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 946 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በቅድመ-ምረቃ (699) እና በድኅረ-ምረቃ (247) የትምህርት መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ CGPA 3.98 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተመራቂ አብደላ ወርቁ የወርቅ ሜዳሊያ ከዩኒቨርሲቲው ተበርክቶለታል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Medical Information posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Medical Information:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Our Story

Feed Health Information