04/12/2025
ዓለም አቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን "ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽን ዘላቂነት እናረጋግጥ!" በሚል መሪ ሀሳብ በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል በዛሬ ዕለት ተከብሯል።
በመርሃ-ግብሩ መክፈቻ ላይ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ኀይለገብርኤል ኪዳኔ ሆስፒታሉ በጸረ-ኤች አይ ቪ ኤድስ ዘመቻ አመርቂ ስራ መሰራቱን ገልጸዉ በተመሳሳይ መልኩ ለላቀ ዉጤት ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።
በተቋሙ ሰራተኞች ድጋፍ እየተደረገላቸዉ የሚገኙ 13 ወላጆቻቸዉን በቫይረሱ ያጡ ልጆችን በተመለከተ ወ/ሮ በዕምነት አድማሱ ዝርዝር ሪፓርት ያቀረቡ ሲሆን ተመሳሳይ የበጎ አድራጎት ተግባራት ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ከዘዉዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የመጡት ዶ/ር አስቴር ሸዋአማረ ባቀረቡት ጹሁፍ የቫይረሱ ስርጭት በከተሞች አካባቢ መጨመሩን እንዲሁም ባሳለፍነዉ አመት ብቻ 7962 አዲስ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸዉን ተናግረዋል።
ዶ/ር አስቴር በ 2030 ኤች አይ ቪን ለማቆም የተቀመጠዉን ግብ ለማሳካት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አበክረዉ ተናግረዋል።
የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ38ተኛ በሀገራችን ደግሞ ለ37ተኛ ግዜ መከበሩ ታዉቋል።
25/03/2018