Amanuel mental specialized hospital

Amanuel mental specialized hospital Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amanuel mental specialized hospital, Addis Ababa ethiopia Addis ketema subcity at the vicinity of Mesalemeya, Addis Ababa.

Emmanuel mental specialized hospital is apionner one which provides mental health care and treatment for about people who are from all corners of the nation and mental health rehabilitation services since it has been established in 1938

የዕለቱ መልዕክት ከስነምግባርና ፀረሙስና ስራ አሰፈፃሚ
23/10/2025

የዕለቱ መልዕክት ከስነምግባርና ፀረሙስና ስራ አሰፈፃሚ

በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ተሰማርተው ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለተወጡ ወጣቶች ሆስፒታሉ እውቅና ሰጠአዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤ በ2017 ዓ.ም ክረ...
23/10/2025

በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ተሰማርተው ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለተወጡ ወጣቶች ሆስፒታሉ እውቅና ሰጠ
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤ በ2017 ዓ.ም ክረምት ወራት በአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በበጎ ስራ አገልግሎት ተሰማርተው ህሙማንን በመንከባከብና የምድረ ግቢፅዳት ስራዎችን በመስራት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለተወጡ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ወጣቶች የምስጋናና እውቅና የምስክር ወረቀት ተበረከተላቸው፡፡
ለወጣቶቹ የምስጋናና እውቅና የምስክር ወረቀት ያበረከቱት የሆስፒታሉ የፅ/ቤት ሃላፊ አቶ መኮንን አስፋው እኛ ኢትዮጵያውያን በችግርም ሆነ በደስታ ጊዜ መደጋገፍ፤ መረዳዳት ውብ የሆነ ባህላችን ነው፡፡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎትም ሰዎች በጋራም ሆነ በተናጥል ገንዘባቸውን፤ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን አሰባስበውና ተጠቅመው ከተረፋቸው ሳይሆን ካላቸው ላይ ቀንሰው የተቸገረውን ወገናቸውን ወይም ዜጎቻቸውን በመደገፍና በማበርታት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን የሚወጡበት ሲሆን እንደ ሃገርም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎችን ዋነኛ መልካም ባህል አድርጎ በመተግበር ለሃገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት መጠናከር ወጣቱ ትውልድ መደላድል ሊጥል ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ክረምትን ብቻ ጠብቆ ሳይሆን በማንኛውም ቦታና ጊዜ ሃገርና ህዝብ በሚጠይቀው ማህበራዊ ተሳትፎና አገልግሎት የምንተገብረው ብሄራዊ ተልዕኮ ሊሆን ይገባል በማለትም አክለዋል፡፡

የአራት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ብር የህሙማን አልጋ ድጋፍ ተደረገአዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤ የጤና ሚ/ር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተለያዩ የህክም...
22/10/2025

የአራት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ብር የህሙማን አልጋ ድጋፍ ተደረገ
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤ የጤና ሚ/ር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተለያዩ የህክምና ግብዓቶችን የጤና ተቋማት የታለመላቸውን አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያቀረበ የሚገኝ ሲሆን በዚህም ለአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአስተኝቶ ህክምናና ለፅኑ ህሙማን አገልግሎት የሚውሉ በአራት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ብር ገዝቶ በማቅረብ 100 አልጋዎችን ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉ ሆስፒታሉ በ2018 በጀት ዓመት የህክምና አገልግሎቱን ለማስፋትና ተደራሽ ለማድረግ ይዞት የተነሳውን እቅድ ከግብ ለማድረስ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል፡፡ በአጠቃላይ መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋትና ለማጠናከር ሚ/ር መ/ቤቱ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንዳለ አመላካች ነው፡፡

20/10/2025

ያለ አእምሮ ጤና ጤና የለም

ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና ማረጋገጥ ለሁለንተናዊ ልዕልና በሚል አጀንዳ ዙሪያ  ስልጠናዊ ውይይት ተካሄደ።አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)   የአማኤ...
17/10/2025

ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና ማረጋገጥ ለሁለንተናዊ ልዕልና በሚል አጀንዳ ዙሪያ ስልጠናዊ ውይይት ተካሄደ።
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) የአማኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አመራሮች ፤የጤና ባለሙያዎችና የክብካቤ ሠራተኞች ብሄራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በሚል አጀንዳ ዙሪያ ስልጠናዊ ውይይት አካሄዱ።
ስልጠናዊ ውይይቱን በንግግር በመክፈት ስልጠናውን የሰጡት የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ የአንድ ሃገር ጅኦስትራቴጂያዊ ቁመና መጎልበት የህልውናና የደህንነት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካዊ አቅምና የተፅዕኖ ፋጣሪነት ማሳያና የኢኮኖሚያዊ ብልፅግና መረጋገጥ መሰረት ነው በማለት አንስተዋል፡፡
ስልጠናው በይዘትነት አካትቶ ለውይይት ከቀረቡ ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመናና ብሔራዊ ጥቅም፣ የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ፈተናዎች፣ ለብሔራዊ ጥቅም መረጋገጥ ቁልፍ መፍትሔዎች፣ ለብሔራዊ ጥቅሞቻችን መረጋገጥ የሚጠበቅብን ሚና እና የተቋማት ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በተቋም ውጤታማነት ላይ እንዴት ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍ የሚሉት በዝርዝር ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል።
በመጨረሻም በመድረኩ በርካታ የጋራ ትርክት የሚፈጥሩና ህዝብን በጋራ የሚያስተሳስሩ ሃገራዊ ፕሮጀክቶች መሰራታቸውና መጀመራቸው እንዲሁም ኢትዮጵያ ከጂኦግራፊያዊ እስረኝነት ተላቃ መውጫ መግቢያ በሯን የምታበጅበት ጉዳዮች ላይ ጥልቅ የሆነ ውይይት ተደርጓል፡፡ የሀገር ብሔራዊ ጥቅምን ማስቀደም ከግለሰቦችም ሆነ ከቡድን ፍላጎትና ጥቅሞች በላይ መሆን እንደሚገባውና ይህንን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ለማስቀጠል ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር በጋራ መቆምና እንደ ተቋም ጠንካራ ተቋማትን ከመገንባት አንስቶ ህዝብን የማዳመጥ፤ ቅሬታን የመፍታት፤ ስራን በውጤታማነት የመፈፀምና መልካም አስተዳደርን የማስፈን ስራዎችን በውጤታማነት የመከወን የእያንዳዱ ዜጋ ሀላፊነት መሆኑም ተጠቁሟል።

18ኛው ብሄራዊ የሰንደቅ አላማ ቀንጥቅምት 3/2018 ዓ.ም
13/10/2025

18ኛው ብሄራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን
ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም

የአእምሮ ጤናን ያዋህዱ  የስነ-ልቦና ድጋፍ፤ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽን ቅድሚያ ሰጥቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ  ለአእምሮ ጤና ማህበራዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ ሕይወት አድን ጣልቃ ገ...
09/10/2025

የአእምሮ ጤናን ያዋህዱ የስነ-ልቦና ድጋፍ፤ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽን ቅድሚያ ሰጥቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ
ለአእምሮ ጤና ማህበራዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ ሕይወት አድን ጣልቃ ገብነት ነው።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤ የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን “በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብአዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት!” በሚል መሪ ቃል አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆሰፒታል ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት፤ሲቪል ማህበራትና የማህበረሰብ አደረጃጀቶች ከተውጣጡ የስራ ሃላፊዎች/ተወካዮች ጋር በፓናል ውይይትና በኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች በሰሜን ሆቴል በድምቀት አክብሯል፡፡
የዘንድሮው የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን ዋነኛ ዓላማው በዓለም ዙሪያ በአእምሮ ጤናና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤን ከማሳደግና በአእምሮ ጤና ክብካቤ ላይ የድጋፍ ስራዎችን ከማጠናከር ጎን ለጎን የአእምሮ ጤናን ያዋህዱ የስነ-ልቦና ድጋፍን፤ የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት እና ምላሽ ዋና አካል አድርጎ መተግበር እንደሚገባ አመላክቷል። በዚህም የአእምሮ ጤና አገልግሎቶችን ማስፋትና ማጠናከር፤ ለአእምሮ ጤና ጥራትና ተደራሽነት የገንዘብ ድጋፍን ማጎልበትና ማሻሻል፤ የሰዎች መብት እና ክብር መጠበቃቸውን ማረጋገጥ በተለይ በችግር ጊዜ ከባድ የአእምሮ ጤና ችግር ያለባቸውን ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ ማድረግን ይመለከታል።
በዕለቱም የፓናል ውይይትና በአእምሮ ጤና ዙሪያ የሚያጠነጥኑ የኪነጥበብ ስራዎች ቀርበዋል፡፡
የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ሃይሌ የአዕምሮ ጤና የግለሰቦች ብቻ ጉዳይ ሳይሆን የህብረተሰብ የጋራ ጉዳይ ነው፡፡ የአዕምሮ ጤናን መደገፍ ቤተሰብንና ህብረተሰብን መደገፍ ነው በማለት ገልፀዋል፡፡ ለአእምሮ ጤና ማህበራዊና ስነልቦና ድጋፍ ሕይወት አድን ጣልቃ ገብነት ነው። የረጅም ጊዜ ጉዳቶችን ይከላከላል፣ ራስን ማጥፋትን ይቀንሳል፣ ሰዎች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዲቋቋሙ እና እንዲያገግሙ ያስችላቸዋልም ብለዋል።
የተፈጥሮ አደጋዎች፣ ግጭቶች፣ ወረርሽኞች የመሳሰሉት ቀውሶች የስሜት ቀውስና ውጥረት ያስከትላሉ፡፡በዚህን ጊዜ ፍርሃት፣ ጭንቀትና የሃዘን ስሜት ማጋጠሙ የተለመደ ነው፡፡በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ወቅት ከምግብ፣ ውሃና መድሃኒት በተጨማሪ ፡፡ደረጃ በደረጃ የሚቀርብ የአዕምሮ ጤና አገልግሎት፣ ማለትም ሰዎች ራሳቸውን እንዲያግዙ ከማድረግ ጀምሮ የስነልቦና የመጀመሪያ እርዳታ፣ ከዚያም ስፔሻላይዝድ የሆነ አገልግሎት ማቅረብ ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
አቶ ጀማል ተሾመ በጤና ሚ/ር የአእምሮ ጤና ፕሮግራም አስተባባሪ በበኩላቸው በአእምሮ ጤናና ህመም ላይ በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ውስጥ የግንዛቤ ክፍተቶች፤ በህሙማኑ ላይ አድሎና መገለል መኖር የህክምናው ተደራሽነት ውስንነት መኖሩን አንስተው በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውሥጥ የአእምሮ ጤና ክብካቤና የአእምሮ ህመም ህክምና እንዲሰጥ እየተሰራ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው የጤና ባለሙያውና መንግስት በጋራ ተቀናጅቶ በመስራት በአእምሮ ጤና ጥራትና ተደራሽነት ላይ ለውጥ የምናመጣበት ሊሆን ይገባል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመጨረሻም የአዕምሮ ጤና ተገቢውን ክብካቤ እንዲያገኝ፣ ጥበቃ እንዲደረግለትና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን፣ በተለይም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ለተጎዱ ሰዎች ተደራሽ እንዲሆን በአዕምሮ ጤና እና ማህበራዊ ድጋፍ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ሰብአዊነትን ከማጎልበት ባሻገር በሃገር ኢኮኖሚ እድገት ላይም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ አካታች የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ለህጻናት፣ ለአረጋውያን፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለስደተኞች፣ የታወቀ የአዕምሮ ህመም ላለባቸው ሰዎች ማቅረብ ተገቢ መሆኑ በአፅንኦት ቀርቧል፡፡

08/10/2025

በህብረተሰብ ዘንድ የ ጤና መረጃ ግንዛቤ ሚና
የጤና እውቀት (Health Literacy) ማለት ጤናማ አኗኗርን የሚደግፍ መረጃ ማግኘት፣ አገናዝቦ መረዳት እና መጠቀም መቻል ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት የጤና እውቀትን በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ፣ በማህበራዊ መስተጋብር እና በትውልዶች እውቀት ሽግግር የሚመጣ እውቀት እንደሆነ ይገልጿል።

ዲጂታል የጤና እውቀት (Digital Health Literacy) የጤና መረጃን የማግኘት፣ አገናዝቦ የመረዳት እና የመተግበር ችሎታ እና ዲጂታል መሳሪያዎችን በመጠቀም ጤናን ለመጠበቅ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ማድረግ ማለት ነው።

የጤና እውቀትን ማሻሻል በአንድ ሀገር ሕዝብ ውስጥ ለዜጐች የሚከተሉትን መሠረት ይሰጣል፡-
• የራሳቸውን ጤና ለማሻሻል ንቁ ሚና ይጫወታሉ
• ከሌላው ማህበረሰብ ጋር ለጤና ተግባራት በተሳካ ሁኔታ ተሳታፊ ይሆናሉ
• ጤና እና የጤና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ መንግስታቸውን ጫና ማድረግ የ2030 የዘላቂ ልማት አጀንዳን ለማሳካት የጤና እውቀትን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት ወሳኝ ይሆናል።

በደንብ የሚያነቡ እና ቁጥራዊ መረጃ የሚጠቀሙ ሰዎች እንኳን በሚከተሉት ወቅቶች የጤና መረጃ ችግሮች ሊያጋጥሟቸው ይችላሉ።
• የሕክምና ቃላትን ትርጉም አለማወቅ
• ሰውነታቸውን አካላት ጥቅም ሲጠየቁ አለማወቅ
• በከባድ ሕመም እንደተያዙ በሃኪም ተነገሯቸው ፍርሃትና ግራ መጋባት ሲያጋጥማቸው
• ውጥረት ውስጥ ሆነው ወሳኝ የጤና ውሳኔዎችን ማድረግ ሲኖርባቸው
• ውስብስብ እንክብካቤ የሚፈልግ የጤና እክል ሲኖራቸው
በትክክለኛ፣ ወቅታዊ እና ተገቢ የጤና እና የሳይንስ መረጃዎች እንዲሁም ጤናን የሚያበረታታ ትምህርታዊ ስርአተ ከልጅነት ጀምሮ ተግባራዊ በማድረግ በቤት፣ በመሰሪያ ቤት፣ በትምህርት ቤቶች እስከ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ እና የጎልማሶች ትምህርት አካል በማድረግ የግል የጤና እውቀት ማጠናከር ይቻላል።

ምንጭ:- አለም የጤና ድርጅት (WHO)

በዶ/ር ሚኪያስ ታደለ: የቤተሰብ ህክምና እስፔሻሊስት እና M.Sc Population studies
www.efhoi.com
+251997394315 / +251911435406

06/10/2025
በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብአዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት      የአዕምሮ ጤና የግለሰቦች ብቻ ጉዳይ ሳይሆን የህብረተሰብ የጋራ ጉዳይ ነው             አዲስ አበ...
06/10/2025

በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብአዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት
የአዕምሮ ጤና የግለሰቦች ብቻ ጉዳይ ሳይሆን የህብረተሰብ የጋራ ጉዳይ ነው
አዲስ አበባ፤ መስከረም 26/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፤የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን “በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብአዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት!” በሚል መሪ ቃል አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከታዋቂ አርቲስቶች ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም " የእግር ኳስ ጫዎታ ውድድር በማካሄድ ቀኑን በድምቀት አክብሯል፡፡
የዘንድሮው የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን ዋነኛ ዓላማው በዓለም ዙሪያ በአእምሮ ጤናና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤን ከማሳደግና በአእምሮ ጤና ክብካቤ ላይ የድጋፍ ስራዎችን ከማጠናከር ጎን ለጎን በሰብአዊ ድንገተኛ አደጋዎች የተጎዱ ሰዎችን የአእምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ፍላጎቶችን መደገፍ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ይህ የሆነበት ዋነኛ ምክንያት ደግሞ አሁን ላይ የአለም ዜናዎች ቁጥር ስፍር የሌላቸውን አደጋዎች እና ድንገተኛ አደጋዎች ዘግበዋል እየዘገቡም ይገኛሉ። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችም በአደጋዎች እና በድንገተኛ አደጋዎች ተጎድተዋል፡፡ እነዚህ አደጋዎች እና ድንገተኛ አደጋዎች በሰው ልጆች የአእምሮ ጤና ላይ ምን አይነት ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩ መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፡፡
ቀኑን በንግግር የከፈቱት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ሃይሌ የአዕምሮ ጤና የግለሰቦች ብቻ ጉዳይ ሳይሆን የህብረተሰብ የጋራ ጉዳይ ነው፡፡ የአዕምሮ ጤናን መደገፍ ቤተሰብንና ህብረተሰብን መደገፍ ነው በማለት ገልፀዋል፡፡ ለአዕምሮ ጤና ቅድሚያ ስንሰጥ፤ ጤናማ የስራ ቦታን መፍጠር ስንችል፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራን መቀነስና ሁለገብ ብልጽግናን ማረጋገጥ እንችላለን ሲሉም አክለዋል፡፡
በ2020 በአለማችን በግምት 100 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ተጠቅተዋል፡፡ በነዚህ መሰል አደጋዎች ወቅት ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ለሆነ ውጥረት (stress) ይጋለጣሉ ብሎም ከ 3 እስከ 5 ሰዎች አንዱ የአዕምሮ ጤና ችግር ያጋጥማቸዋል ሲሉ ዳይሬክተሩ በአፀንኦት አንስተዋል፡፡
የተፈጥሮ አደጋዎች፣ ግጭቶች፣ ወረርሽኞች የመሳሰሉት ቀውሶች የስሜት ቀውስና ውጥረት ያስከትላሉ፡፡በዚህን ጊዜ ፍርሃት፣ ጭንቀትና የሃዘን ስሜት ማጋጠሙ የተለመደ ነው፡፡በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ወቅት ከምግብ፣ ውሃና መድሃኒት በተጨማሪ የአዕምሮ ጤና እና ማህበራዊ አገልግሎት ለተጠቂዎች ሊቀርብ ይገባልም ተብሏል፡፡
በመጨረሻም የአዕምሮ ጤና ተገቢውን ክብካቤ እንዲያገኝ፣ ጥበቃ እንዲደረግለትና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን፣ በተለይም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ለተጎዱ ሰዎች ተደራሽ እንዲሆን በአዕምሮ ጤና እና ማህበራዊ ድጋፍ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ሰብአዊነትን ከማጎልበት ባሻገር በሃገር ኢኮኖሚ እድገት ላይም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ አካታች የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ለህጻናት፣ ለአረጋውያን፣ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለስደተኞች፣ የታወቀ የአዕምሮ ህመም ላለባቸው ሰዎች ማቅረብ ተገቢ መሆኑ ተንፀባርቋል፡፡
የአርቲስቶች የጤና ቡድን አስተባባሪ አርቲስት ፍቃዱ ከበደ በበኩላቸው እኛ አርቲስቶችን ወክለን ከዚህ ተገኝተን ቀኑን በጋራ ስናከብር መነሻችን በአእምሮ ጤና ጉዳይ ላይ ማህበራዊ ሃላፊነታችንን መወጣት ግዴታችን በመሆኑና የአእምሮ እክል ማንኛውንም ሰው ያለ ልዩነት ሊያጠቃ የሚችል በመሆኑና ነገ ላይ በህመሙ ላለመያዝም ምንም መተማመኛ ያለን ባለመሆኑ ምንጊዜም ጉዳዩ ስለሚመለከተን ከሆስፒታሉ ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ ነን በማለት ገልፀዋል፡፡

የሚዲያ ጥቆማበየዓመቱ እ.ኤ.አ ጥቅምት 10 ቀን የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡የ2018 ዓ.ም የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን "የአገልግሎት ተደራሽነት-በአደጋዎች እና ...
04/10/2025

የሚዲያ ጥቆማ
በየዓመቱ እ.ኤ.አ ጥቅምት 10 ቀን የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡
የ2018 ዓ.ም የዓለም የአእምሮ ጤና ቀን "የአገልግሎት ተደራሽነት-በአደጋዎች እና በድንገተኛ አደጋዎች የአእምሮ ጤና!” በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን ቀኑን አስመልክቶ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የዓለም የአእምሮ ጤና ቀንን በተለያዩ ሁነቶች የሚያከብር ሲሆን ሰኞ በ26/1/2018 ዓ.ም ከ 3፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከታዋቂ አርቲስቶች ጋር በእግር ኳስ ጫዎታ ውድድር የመክፈቻ ፕሮግራም ያካሂዳል፡፡ በመሆኑም የሚዲያ አካላት በዕለቱ በቦታው በመገኘት ሁነቱን በመዘገብ የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡልን በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ለበለጠ መረጃ በ09 44 19 91 74 ደውሎ ማናገር ይቻላል፡፡

Address

Addis Ababa Ethiopia Addis Ketema Subcity At The Vicinity Of Mesalemeya
Addis Ababa

Telephone

251944199174

Website

http://WWW.amsh.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amanuel mental specialized hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram