26/11/2025
ህፃናት እንደ ተወለዱ የሚሰጥ የጉበት በሽታ መከለከያ ክትባት
__________
ከወሊድ በኋላ የሚሰጥ የሄፐታይተስ ቢ ክትባት ወይም የጉበት በሽታ መከለከያ ክትባት ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍና ሕፃናት ወደፊት እንደ የጉበት ጠባሳ እና የጉበት ካንሰር ያሉ ሥር ለሰደዱ የጤና ችግሮች እንዳይጋለጡ ይከላከላል።
በተለይም እናት የቫይረሱ ተሸካሚ ከሆነች፥ ከወሊድ በኋላ ክትባቱን መስጠት ኢንፌክሽኑን ለመከላከል በጣም ውጤታማው መንገድ ነው።
የሄፐታይተስ ቢ ክትባት ህፃናት ከተወለዱ በኋላ ባሉት የመጀመሪያዎቹ 24 ሰዓታት ውስጥ ይሰጣል። በመጀመሪያዎቹ 24 ሰዓት ውስጥ ክትባቱ መስጠት አስተማማኝ እና ውጤታማ ነው ።
ከሆስፒታል ውጭ ለተወለዱ ህጻናት ክትባቱን ከተወለዱ በኋላ ባሉት 14 ቀናት ውስጥ መከተብ አለባቸው።
ክትባቱ በሁሉም የመንግስት ጤና ተቋማት እና በተወሰኑ የግል ጤና ተቋማት ውስጥ ይሰጣል!
Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB