Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) I feel I am still a student, a beginner journalist with a great zeal to learn more.

I am climbing up the ladder and register remarkable achievement in my profession. This page is dedicated to serve you with reliable news and voice for voiceless.

ያለምንም ወለድና የዋጋ ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር የሚዋዋሉት የመኖርያ ቤቶችና የንግድ ሱቆችን በ30%ታላቅ የበዓል ቅናሽ🏠እኛ ጋር ስትመጡ የምታገኟቸው አማራጮች1: ቡልጋርያ- ባለ1መኝታ 69ካሬ=...
30/03/2026

ያለምንም ወለድና የዋጋ ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር የሚዋዋሉት የመኖርያ ቤቶችና የንግድ ሱቆችን በ30%ታላቅ የበዓል ቅናሽ

🏠እኛ ጋር ስትመጡ የምታገኟቸው አማራጮች

1: ቡልጋርያ
- ባለ1መኝታ 69ካሬ=5.5ሚ ብር
- ባለ2መኝታ 82ካሬ=6.6ሚ ብር
- ባለ3መኝታ 126ካሬ=10.1ሚ ብር
2: አዋሬ
- ባለ3መኝታ 131ካሬ=9.3ሚ ብር
3: ሳርቤት
- ባለ3መኝታ 139ካሬ=9.9ሚ ብር
4:ፒያሳ
- ባለ3መኝታ 132ካሬ=10.6ሚ ብር
5: ጋርመንት
- ባለ3መኝታ139ካሬ=10.2ሚ ብር

ከላይ የተጠቀሰው ዋጋ 100% ለሚከፍሉ ሲሆን በቅድመ ክፍያ መጀመር ለምትፈልጉ ሌላ ዋጋ ሌላ አከፋፈል ማግኘት ትችላላቹ::

እንዲሁም የንግድ ሱቆችን በገላን እና በቡልጋርያ ከ900ሺ ብር ቅድመ ክፍያና ከ2.8ሚ ብር ሙሉ ክፍያ ጀምሮ ማግኘት ትችላላቹ::
ለበለጠ መረጃ 0904479493 ይደውሉ
https://wa.me/251904479493

እነኚህን ጉልህ የድህነት ነፀብራቅ በሽታዎችን ከሀገር ሳንነቅል ስለብልጽግና አፍን ሞልቶ መናገር ያዳግታል   | ትኩረት የተነፈጉ የሀሩራማ በሽታዎች (Neglected Tropical Diseas...
30/03/2026

እነኚህን ጉልህ የድህነት ነፀብራቅ በሽታዎችን ከሀገር ሳንነቅል ስለብልጽግና አፍን ሞልቶ መናገር ያዳግታል

| ትኩረት የተነፈጉ የሀሩራማ በሽታዎች (Neglected Tropical Diseases - NTD) ይሰኛሉ፡፡ ከ10 አመት ወዲህ ዓይን እያረፈባቸው በመምጣቱ ትኩረት የሚሹ የሚል ዳቦ ስም ተለጥፎላቸዋል፡፡

በድህነት መዘዝ ይከሰታሉ -ድህነትንም ያባብሳሉ - ሕብረተሰብንም በድህነት አዙሪት ለዘመናት እንዲቆይ ይዳርጋሉ፡፡ በሽታዎቹ የልማት ጥያቄን በየገጠሩ መንደሩ ከማዳረስ ጋር ይያያዛል።

በሽታዎቹ ከውሃ አቅርቦት ጋር በተያያዘ የግልና አካባቢ ንፅህና ችግር ባለባቸው፡ የጤና አጠባበቅ ግንዛቤ ባልዳበረባቸው፡ የጤና አገልግሎት ባልተስፋፋባቸው የዓለማችን የምስኪናን ገጠር ክፍሎች በተለይም በአፍሪካ፡ ኢሲያና ላቲን አሜሪካ ሀገራት ነው በብዛት የሚታየው።

ትኩረት የተነፈጉ የሀሩራማ በሽታዎች ተብለው የዓለም ጤና ድርጅት የለያቸው 21 በሽታዎች ሲሆኑ የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ደግሞ ትራኮማን፡ ቢሊሀርዚያ፡ ዝሆኔና ፎከትን ጨምሮ 13 በሽታዎችን የህብረተሰብ ጤና ችግሮቼ ናቸው ብሎ በቅድሚያ ትኩረትነት ለይቶ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ እያከነወነባቸው ይገኛል፡፡

ዛሬ ትራኮማና ኦንኮሰርኪያሲስ ላይ እናተኩርና በኢትዮጵያ ከ61 ሚሊዮን የሚልቁ ዜጎች ለትራኮማ አጋላጭ ቦታዎች የሚኖሩ ሲሆን ከ30 ሚሊዮን የሚልቁ ወገኖች ደግሞ ለኦንኮ ወይም ለፎከት በሽታ ችግር የተመቻቹ አካባቢዎች የሚኖሩ ናቸው፡፡

ትራኮማ አይናር በምትሻ ዝንብ አማካይነት የሚተላለፍ ሲሆን ኦንኮ ወይም በተለምዶ River Blindness ደግሞ በጥቁር ዝንብ ንክሻ አማካይነት በባክቴሪያና ጀርም ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎች ናቸው፡፡

መልካም አጋጣሚው ግን በሽታዎቹ እንዳሉባቸው በጥናት በተለዩ ወረዳዎች ላይ በሙሉ በዓለም ጤና ድርጅት የምክረ መፍትሄ ስትራቴጂ (WHO recommended strategy) አኳያ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ብሎም የህብረተሰብ ጤና ችግርነታቸው እንዲያከትም ወይ እንደ ሁኔታው ስርጭት ሙሉ ለሙሉ የሚያቆምበት ስራ መከናወን ቀጥሏል፡፡

ለዛሬው የላየንስ - ካርተር የዕይታ ጤና ትኩረት አጋርነት (Lions – Carter SightFirst Partnership) በተለይ በሁለቱ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ላይ በኢትዮጵያ ስራ ከቀጠለ ከ30 አመታት የተሻገረ ሲሆን በሽታዎቹ ከሚጠኑበት ምርምር (Baseline survey)፣ አድቮኬሲ፣ የተቀናጀ ስትራቴጂካዊ የአሰራር ዘይቤን መንደፍ፣ የሀብት ማሰባሰብና የድርጊት መርሀ ግብርን ወጥኖ መንቀሳቀስን አካቶ ክትትልና ግምገማ ድረስ የዘለቀ ስራን በማከናወን በሀገር ግንባር ቀደም ሚና ከሚጫወቱት ተርታ ይገኛል፡፡

39ኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጂሚ ካርተር ላየንስ ክለብን ለ70 አመታት ማገልገላቸው ብቻ ሳይሆን የጆርጂያ ክ/ግዛት የላየንስ ክለብ ገዢም መሆናቸው ለፕሬዚደንትነት የህዝብ አገልግሎት እሳቤ ያጫረባቸው ለመሪነት የተሰሩበት ተቋም እንደሆነ በህይወት ሳሉ አበክረው በፍቅር ያወሱ እንደነበር ይነገራል፡፡

የላየንስ ክለብ ዓለም አቀፍ ፋውንዴሽን ከአንድ መቶ አመታት የተሻገረ ታሪክ ያለው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ205 ሀገራት የሚሰራ፡ 50 ሺህ ክለቦች በስሩ የሚገኙና 1.4 ሚሊዮን አባላት ያሉት የዓለማችን አንዱ ታላቅ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡

በዚህ ውስጥ ጂሚ ካርተርን ከዓለም አቀፍ ብንጠቅስ፡ በኢትዮጵያችን ደግሞ ላየኖቹ (Lions) የተከበሩ የዓለም ሎሬት ዶ/ር ጥበበ የማነብርሃን፡ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ እና ሚስተር ራሜንድራህ ሻህ ሳይጠቀሱ አይታለፍም፡፡

ላየንስ ክበብ ስለምን የዕይታ ጤና ላይ አተኮረ ሲባል የዛሬ 103 አመት በአሜሪካ ኦሀዮ 9ኛው የላየንስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ጉባኤ ላይ የተገኘችው ማየት ባትችልም ልበ ብርሃኗ የዕይታ መብት ተምጋች (advocate) ሄለን ኬለር ባደረገችው ንግግር ከጭለማ የተላቀቀች ዓለም ትኖረን ዘንድ የመኖር ራዕዬን ተቀላቅላችሁ የብርሃን አርበኛ ጭለማ ላይ ዘማቾች (Knights of the Blind Crusading against Darkness) ሁኑኝ ብላ ያቀረበችውን ተማጽኖ ላየኖቹ ከልብ ተቀብለው ከጥንት እስከዛሬ ይዘውት ቀጥለዋል፡፡

የዓለም አቀፍ ላየንስ ክበብ እ.አ.አ በ1917 ለሕብረተሰብ ኑሮ መሻሻል ልባቸው በቀና የንግድ ሰዎች በሜልቪን ጆንሰን አነሳሽነት በአሜሪካ የቺካጎ ነው የተመሠረተው።
የካርተር ማዕከል ደግሞ እ.አ.አ በ1982 በጂሚ ካርተርና በባለቤታቸው ሮዛሊን ካርተር በኤመሪ ኒቨርስቲ አጋርነት የዓለም አቀፍ ጤናን እና የሰብአዊ መብት አከባበርን ለማሻሻል በማለም በአትላንታ ጆርጂያ ነዌ የተመሠረተው።
ሁለቱ የግብረ ሰናይ ተቋማት የስራቸው ትይዩነት ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ አጋርነታቸውን የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች የሚል ስያሜ አሰጥቶታል፡፡

ወደ ኢትዮጵያ ደጋግመው ከመጡ የአሜሪካ መሪዎች ተጠቃሹ ጂሚ ካርተር ከግብረ ሰናይ ማዕከሉ ስራ ጋር በተያያዘ የጊኒ ዎርም፣ የዓይን ማዝ የሚባለው ትራኮማና ኦንኮ ወይም የፎከት በሽታዎች አብይ የጤና ችግር ጉዳዮቻቸው ነበሩ፡፡

ሊጠፋ ጫፍ ደርሶ ዛሬም በጋምቤላ ዋነኛ የሕብረተሰብ ችግር የሆነው የጊኒ ዎርምን በመስክ ማየት ሲቀራቸው በተረፈ የቀድሞው ፕሬዚደንት ካርተር የምዕራብ ኢትዮጵያ ማና ወረዳን እና የሰሜኗን ባህርዳር ከህብረተሰብ ጋር ባገናኛቸው መልኩ በቅርበት ጎብኝተዋቸዋል፡፡

እሳቸው የገንዘብ ድጋፍ አመቻችተው ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ወቅት ደግሞ የወባ መከላከልና ቁጥጥር ስራ ያየለበትና የወቅቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩት ደግሞ የአሁኑ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ነበሩ።

ወባን ከሀሩራማ በሽታዎቹ ጋር አጣምሮ የቁጥጥር ስራው ተያይዞ በምዕራብ ኢትዮጵያ ኦንኮሰርኪያሲስን ከወባ ጋር (MalOncho- malaria & Onchocerciasis)፡ በሰሜን ኢትዮጵያ አማራ ክልል ደግሞ ወባን ከትራኮማ ጋር ተጣምሮ (MalTra – malaria & trachoma) የሕብረተሰብ አቀፍ የመድሀኒት ስርጭቱ የተሰጠበት ነበር፡፡

በአማራ ክልል የትራኮማ በሽታ ቁጥጥርን በ166ቱም ወረዳዎች ላይ የላየንስ ካርተር አጋርነት ሲሰራ፡ በምዕራብ ኢትዮጵያ ደግሞ በኦንኮሰርኪያሲስ በሽታ ስርጭትን ለማስወገድ ደግሞ በ228 ወረዳዎች ላይ ከ20 አመታት ላለፈ ጊዜ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና የክልላት ጤና ቢሮዎችን ጥረቶች እየደገፈ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአማራ በ58 ወረዳዎች የዔይን ማዝ የሕብረተሰብ ጤና ችግርነቱ እያከተመ ሲሆን ይህም 7 ሚሊዮን ያህል ሰዎች ከእንግዲህ የጀማ መድሀኒት ስርጭት ከመውሰድ ውጪ ተደርገዋል።

ይህ የላየንስ ካርተር አጋርነት የኦንኮ በሽታ ተጠቂዎች ባሉበት 228 ወረዳዎች ውስጥ የቁጥጥር ስራን በማጠናከር በአሁኑ ወቅት በ29 ወረዳዎች የኦንኮ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ተሳክቶ ተወግዶ ወረዳዎቹ ከሕብረተሰብ አቀፍ የመድሀኒት ስርጭት ወጥተዋል፡፡

አጋርነቱ ከሚሸፍናቸው 23 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 61 በመቶው ባሉበት 137 ወረዳዎች የበሽታው ስርጭት እንደተቋረጠ (suspected transmission interrupted) ይጠረጠራል ወይም በሽታው በቁጥጥሩ ጫና ስር (suppressed) ሆኗል።

የላየንስ ክበብ ኢትዮጵያ ግራንት አድሚኒስትሬተር ላየን ዶ/ር ተሾመ ገብሬ እና የካርተር ሴንተር ከፍተኛ የኢትዮጵያ ተጠሪ ላየን ዶ/ር ዘሪሁን ታደሰ ደግሞ በሽታዎቹን የመቆጣጠር ጥረቱ ዛሬ ላይ ከመጨረሻው ማይል ላይ ደርሶ እ.አ.አ በ2030 ከማስወገድ አንፃር እጅግ ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ላይ እንገኛለን ይላሉ።

(Written by: Eshetu Geletu - National Champion of Public Health esp. for NTD)

ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ለሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ያላቸውን አክብሮት ገለጹ  | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ግዙፉ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ፈረሰኞቹ) ላለፉት 30 ዓመታት ላደረጉላቸው ወደር...
30/03/2026

ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ለሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ያላቸውን አክብሮት ገለጹ

| የኢትዮጵያ እግር ኳስ ግዙፉ ክለብ ቅዱስ ጊዮርጊስ (ፈረሰኞቹ) ላለፉት 30 ዓመታት ላደረጉላቸው ወደር የለሽ ድጋፍ ለታዋቂው ባለሀብት ሼህ መሀመድ አሊ አልአሙዲ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ክለቡ ባወጣው መግለጫ፣ ሼህ አላሙዲ ያለምንም የግል ጥቅም ፍላጎት ሀብታቸውን ለክለቡ ስኬት በማዋላቸው ደጋፊው በርካታ የደስታ ጊዜያትን እንዲያሳልፍ ምክንያት መሆናቸውን አስታውሷል። "እስካሁን በተገቢው መልኩ ምስጋና አላቀረብንልዎትም" ያለው ክለቡ፣ አሁን ግን ታሪካዊ ውለታቸውን በይፋ እውቅና ሰጥቷል።

ባለሀብቱ ላለፉት 30 ዓመታት ያላሰለሰ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል።

ከየትኛውም ክለብ በተለየ መልኩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ስኬት የነበራቸው አስተዋጽኦ ተወድሷል።

ክለቡ በአሁኑ ወቅት ባለበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥም ሼህ አላሙዲ "አለሁ" ማለታቸው ለክለቡ ትልቅ ብርታት መሆኑ ተጠቁሟል።

"ውለታዎን ታሪክ አይዘነጋውም፤ እኛም ጊዮርጊሳውያን በሚገባ እናስታውሰዋለን" በሚል ጥልቅ መልዕክት የታጀበው ይህ ምስጋና፣ በፈረሰኞቹ ቤት የባለሀብቱ ስፍራ ምን ያህል የላቀ መሆኑን ዳግም አረጋግጧል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)


#ፈረሰኞቹ #ቅዱስጊዮርጊስ

"የአፍሪካ ታሪክ በአፍሪካውያን እጅ እንጂ በሌሎች ሊጻፍ አይገባም"- ፕንገተራይ አን ሙጓጓ   | የአፍሪካ ታሪክ በሌሎች ሳይሆን በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ ሊጻፍ እንደሚገባና ወጣቶች ለዚህ...
30/03/2026

"የአፍሪካ ታሪክ በአፍሪካውያን እጅ እንጂ በሌሎች ሊጻፍ አይገባም"
- ፕንገተራይ አን ሙጓጓ

| የአፍሪካ ታሪክ በሌሎች ሳይሆን በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ ሊጻፍ እንደሚገባና ወጣቶች ለዚህ ትብብራቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው 6ኛው የአፍሪካ ወጣቶች የዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ በተካሄደበት ወቅት ነው።

ኮንፈረንሱ እያንዳንዱ ወጣት ድምፁ ዋጋ እንዳለውና ሀሳቡ ኃይል እንደሆነ እንዲያውቅ የሚደረግበት መድረክ መሆኑን የአህጉር አቀፍ የወጣቶች ትስስር ተወካይ ፕንገተራይ አን ሙጓጓ ገልጸዋል።

ለረጅም ጊዜ የአፍሪካ ድምፅ በዓለም መድረክ ዳር ላይ ተገፍቶ መቆየቱን ያነሱት ተወካይዋ፤ ዛሬ ግን በአንድነት ቆመን የራሳችንን ታሪክ በራሳችን እንጂ በሌሎች እጅ ሊጻፍ አይገባም ብለን በአንድ ድምፅ ልንናገር ይገባል ብለዋል።

ወጣቶች ትውልዶችን የሚያገናኙ ድልድይ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የምንመኛት ሰላማዊና የበለጸገች አፍሪካ ከሰማይ የምትወርድ ሳትሆን በገዛ እጃችን የምንገነባት ናት ሲሉ አስገንዝበዋል።

ከፖሊሲ ወደ ተግባር የምንሸጋገርበት ወቅት አሁን በመሆኑ፣ ቋንቋና ባህል ሳይለየን ከተለያዩ የአህጉሪቱ ክፍሎች የመጣን ወጣቶች ትብብራችንን ማጠናከር ይጠበቅብናል ሲሉም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጫላ አሰፋ በበኩላቸው፤ አፍሪካውያን ወጣቶች አንድነታቸውን በማጠናከር የአህጉሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በራስ አቅም ለመወሰን መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

አፍሪካ ከአሁን በኋላ በችግር የምትታወቅ ሳትሆን የቴክኖሎጂ እና የኢኮኖሚ ማዕከል እየሆነች ያለች አህጉር መሆኗን ያነሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የአህጉሪቱን ዕድገት አጠናክሮ ለማስቀጠል የወጣቶች ትብብር እና አንድነት ወሳኝ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)



እየሄዱበት የነበረው መኪና ነዳጅ በመጨረሱ የተሳፈሩበት ሲኖትራክ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት አለፈ📌በቄለም ወለጋ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ  | በቄለም ወለጋ ዞን...
30/03/2026

እየሄዱበት የነበረው መኪና ነዳጅ በመጨረሱ የተሳፈሩበት ሲኖትራክ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት አለፈ

📌በቄለም ወለጋ በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

| በቄለም ወለጋ ዞን ሰዮ ደንታ ወረዳ፣ ነዳጅ በጨረሰ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ምክንያት ወደ ጭነት መኪና ተዛውረው ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች በደረሰባቸው የመገልበጥ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ተሰማ።

መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡30 ላይ ከደንቢ ዶሎ ከተማ ወደ አሺ ሙጌ ወረዳ ከ20 በላይ ተጓዦችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ "ዶልፊን" ተሽከርካሪ መንገድ ላይ ነዳጅ ይጨርሳል። በዚህም ምክንያት ተጓዦቹ ጉዟቸውን ለመቀጠል አሸዋ ጭኖ ወደ ሙጊ ከተማ ይጓዝ በነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-35460 ኢቲ በሆነ "ሴኖ ትራክ" የጭነት መኪና ላይ ለመሳፈር ተገደዋል።

የጭነት መኪናው ደንታ ቀበሌ "አባ ጃራ ቀረብቾ" ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ላይ ሲደርስ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ የሚከተሉት ጉዳቶች ደርሰዋል፦

የ8 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ 6 ወንዶች እና 2 ሴቶች (ሁለቱ ሕፃናት ናቸው) ይገኙበታል።

በ12 ሰዎች ላይ (7 ወንዶች እና 5 ሴቶች) ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሷል።

የዞኑ ፖሊስ ዋና መምሪያ የትራፊክ ደህንነት ቁጥጥር አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ሞቲ ጉዲሳ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት ጉዳት የደረሰባቸው ተጓዦች በደንቢ ዶሎ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

አደጋውን ያደረሰው የሴኖ ትራኩ አሽከርካሪ ለጊዜው ከአካባቢው ቢሰወርም፣ ፖሊስ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከፍተኛ ክትትል እያደረገ መሆኑ ተገልጿል ሲል የዘገበው ብስራት ኤፍ ኤም ነው።

እንዲህ ያሉ አሳዛኝ አደጋዎች እንዳይደገሙ አሽከርካሪዎች የቴክኒክና የነዳጅ ዝግጅታቸውን አስቀድመው እንዲፈትሹ፣ ተጓዦችም ለጭነት ተብለው በተዘጋጁ መኪኖች ላይ ከመሳፈር እንዲቆጠቡ መልእክት ተላልፏል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)


#ቄለምወለጋ #ትራፊክአደጋ

30/03/2026

ማነው የእመቤታችን ወዳጅ? ኑ በገዳም ለምትገኘው ቤተክርስቲያን የ21,000 ብር ቻሌንጅ እንጀምር!

ጎንደር ጎርጎራን ስናስብ ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የጣና ሞገስ የሆነውን የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳምን በዓይናችን ላይ አለመሳል ከባድ ነው::

ይህ ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ክቡር ስጋውንና ቅዱስ ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::

እናቶቻችና እህትቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::

አባቶችችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት ልንመስላቸው ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት::

ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134

ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653

Tiktok: https://www.tiktok.com/?_r=1

Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donation/view/DN-SqgVWKQOT38c

የአጋርነት እና የኢሚግሬሽን ሥርዓቶችን ለማቀናጀት የሚያስችል አዲስ መመሪያ በኢትዮጵያ ድንበሮች ላይ ሊተገበር ነው​   |  የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅ...
30/03/2026

የአጋርነት እና የኢሚግሬሽን ሥርዓቶችን ለማቀናጀት የሚያስችል አዲስ መመሪያ በኢትዮጵያ ድንበሮች ላይ ሊተገበር ነው

​ | የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) እና ከጃፓን መንግሥት ጋር በመተባበር የድንበር ተሻጋሪ ንግድ ማመቻቻ የሥልጠና መመሪያን በዚህ ሳምንት በይፋ አስመርቋል።

ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የንግድ መሠረተ ልማት ለማዘመን እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር ያለመ ትልቅ እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።

​መመሪያው ለድንበር ባለሥልጣናት፣ ለጉምሩክ ወኪሎች እና ለነጋዴዎች እንደ ወጥ መሪ ዕቅድ ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን፣ መደበኛ ያልሆነ የንግድ ልውውጥን እና የተቀናጀ የድንበር አስተዳደር እጥረቶችን ለመፍታት ታስቦ የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

ይህ ተነሳሽነት ወጥ የሆነ የሥራ ማዕቀፍ በማቅረብ፣ የሸቀጦች እና የሰዎች እንቅስቃሴን ቀልጣፋ ለማድረግ፣ እንዲሁም ደህንነትን፣ የሕዝብ ጤናን እና ሰብዓዊ መብቶችን በኢትዮጵያ የድንበር ሥራዎች ላይ ግንባር ቀደም ትኩረት እንዲያገኙ ለማድረግ እንደሚሰራ ተመላክቷል።

 ፦1. ቤት አለህ2. በልተሃል3. ትተነፍሳለህ4. ደግ ልብ አለህ5. ውኃ ጠጥተሃል6. ሕልም አለህ7. አጥበህ ለብሰሃል8. ጥሩ ወዳጆች አሉህ 9. ለሌሎች ቅን ትመኛለህ አሁኑኑ ተመስገን በለ...
30/03/2026



1. ቤት አለህ
2. በልተሃል
3. ትተነፍሳለህ
4. ደግ ልብ አለህ
5. ውኃ ጠጥተሃል
6. ሕልም አለህ
7. አጥበህ ለብሰሃል
8. ጥሩ ወዳጆች አሉህ
9. ለሌሎች ቅን ትመኛለህ

አሁኑኑ ተመስገን በለው!!

መጽሐፍ
እና
መጽሐፍ

ሁለት አዳዲስ የአቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ

የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ

👇🎀👇

👉
👉
👉
👉
👉
👉
👉
👉
👉
👉 #እስከማዕዜኑ
👉
👉
👉 #ኦርቶጵያ
👉
👉 (በእንግሊዝኛ)

ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።

📕📕📕

ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/profile.php?id=61558620807833
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-94XzfBd42YK

"ሊሪያ 3 ፕሮ" የተባለ አዲስ የኤ.አይ ሞዴል ይፋ ተደረገ | ጉግል እስከ 3 ደቂቃ የሚረዝም ሙዚቃን የሚያቀናብር ሊሪያ 3 ፕሮ (Lyria 3 Pro) የተባለ አዲስ የኤ.አይ ሞዴል ይፋ አደ...
30/03/2026

"ሊሪያ 3 ፕሮ" የተባለ አዲስ የኤ.አይ ሞዴል ይፋ ተደረገ

| ጉግል እስከ 3 ደቂቃ የሚረዝም ሙዚቃን የሚያቀናብር ሊሪያ 3 ፕሮ (Lyria 3 Pro) የተባለ አዲስ የኤ.አይ ሞዴል ይፋ አደረገ።

ጉግል የሊሪያ 3 (Lyria 3) ሞዴልን ባወጣ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እጅግ የላቀ ችሎታ ያለውን ሊሪያ 3 ፕሮ (Lyria 3 Pro) የተባለ የሙዚቃ ማቀናበሪያ ይፋ አድርጓል።

ይህ አዲሱ ሞዴል ተጠቃሚዎች እስከ ሶስት ደቂቃ የሚረዝሙ የሙዚቃ ስራዎችን እንዲያቀናብሩ የሚያስችል ሲሆን ይህም በሊሪያ 3 ሞዴል ይቀርብ ከነበረው የ30 ሰከንድ ገደብ በእጅጉ የላቀ ነው።

ሞዴሉ ከቀድሞው ሊሪያ 3 ይልቅ የሙዚቃ አወቃቀርን በተሻለ ሁኔታ ስለሚረዳ ተጠቃሚዎች በትእዛዝ መስጫቸው (prompt) ላይ እንደ መግቢያ፣ አዝማች እና ሌሎችም የተለያዩ የሙዚቃ ክፍሎችን ለይተው ማዘዝ ይችላሉ።

አዲሱ የሊሪያ 3 ፕሮ ሞዴል በጀሚናይ መተግበሪያ ላይ የሚገኝ ቢሆንም የሚሰራው ግን በክፍያ ብቻ ነው። ሞዴሉ የትኛውንም ድምፃዊ ወይም አርቲስት ቀጥታ እንደማያስመስል ኩባያው ገልፃል።

ከቅጂ መብት ጋር በተያያዘ በዚህ ሞዴል የሚሰሩ ሙዚቃዎች በልዩ ምልክት የሚለዩ ሲሆን ይህም የሰው ስራ እና የኤ.አይ የስራ ውጤት ለይቶ ለማወቅ ይረዳል።

Via የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ

​ ​
​ ​

​ ​

የውል ግዴታ ቀሪ የሚሆንባቸው መንገዶች   በኢትዮጵያ የፍትሀብሄር መሠረታዊ የውል ጉዳዮችፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ   0929101037,0983337690                ...
30/03/2026

የውል ግዴታ ቀሪ የሚሆንባቸው መንገዶች
በኢትዮጵያ የፍትሀብሄር መሠረታዊ የውል ጉዳዮች

ፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ
0929101037,0983337690

መግቢያ
| በተዋዋይ መካከል ያለ ውል እንደ ህግ ሆኖ ይቆጠራል። የፍ/ህ/ቁጥር 1731/1/ ውል ሲመሠረትም በፍ/ህ/ቁጥር 1678 ላይ በተደነገገው መሠረት መሟላት የሚጠበቅበትን ሊያሟላ ያስፈልጋል።

ይሁን እንጂ በተለያየ ምክንያት ውሎች ቀሪ ይሆናሉ። እነዚህም በፍ/ህጋችን ስለ ውል በተደነገገው ክፍል ላይ ተቀምጦ ይገኛል።ይህን ማወቁ አስፈላጊ በመሆኑ ይህን አጭር ጽህፍ እንደሚከተለው ተቀምጧል።

የውል ግዴታ ቀሪ የሚሆንባቸው መንገዶች

1. ውል ቀሪ ከሚሆንባቸው መንገዶች አንዱ የውል መፍረስ( invalidation of contract) ነው።1808(1)

1696፥1711፥1716፥ 1719 ለውል መፍረስ ምክንያት የሚሆነው ውሉ ከጅምሩ በተዋዋዮች መካከል ሲደረግ ሟሟለት የሚጠበቅበትን መሠረታዊ ነገሮች ሳያሟላ ሲቀር ነው። የፍ/ህ/ቁጥር 1678 እነዚህም 1. የተዋዋዮች ፍቃድ 2. የህግ ችሎታ ያለው ተዋዋይ ወገን(በተለየ ሁኔታ ካልሆነ በቀር እድሜ 18) 3. የውለታው ነገር(ሊፈጸም የሚችል) 4. የውሉ አቀራረጽ(form) (ውሉ በተለየ ሁኔታ ሲጠይቅ) ከእነዚህ አራት ነገሮች አንዱ እንኳን ሳይሟሏ ቢቀር ውሉ ከጅምሩ ፈራሽ ነው።

2. ሌላው ውል ቀሪ ከሚሆንባቸው መንገዶች ሁለተኛው የውል መሠረዝ ( Cancellation of the contract) ነው።1808 (2/ ፍ/ህ/ቁጥር 1771

ይህ ተዋዋይ ወገኖች በገቡበት የውል ግዴታ መሠረት ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀሪ የሚሆንበት መንገድ ሲሆን በተዋዋይ ወገኖች መካከል ውል ከተመሰረተ በኋላ በውል አፈጻጸም ጉድለት ምክንያት የሚከሰት ነው። ይህ ውል ሲሰረዝ ተዋዋይ ወገኖች ወደ ነበሩበት የሚመለሱ ሆኖ ለኪሳራና ጉዳት የዳረገ ወገን ይህን ሊተካ በህግ ይገደዳል

3. የውል መቋረጥ(Termination of contract) 1819

ይህ ውል ቀሪ የሚሆንበት መንገድ ከተዋዋይ ወገኖች አንዱ ወይም ሁለቱ ውሉ እንዲቋረጥ ሲፈልጉ ውሉ ከተቋረጠበት ጊዜ በፊት ያለው የውል አፈጻጸም እንደተጠበቀ ሆኖ የወደፊቱን በተመለከተው ላይ ውጤት የሚኖረው ነው።

4. መቻቻል(Set off) 1831

ተዋዋይ ወገኖች አንዱ በአንዱ ላይ እያንዳንዳቸው ላይ
እዳ ባለ ጊዜ የአንዱ እዳ ለአንዱ ገንዘብ በሆነ ጊዜ በማቻቻል
ውሉ ቀሪ እንዲሆን ይደረጋል

5. ውሉ በተፈጸመ ጊዜ 1806

ይህ የውል ግዴታ ቀሪ የሚሆነው በተዋዋይ ወገኖች መካከል ያሉት ግዴታዎች በመፈጸማቸው ምክንያት ቀሪ ሲሆኑ ነውደ ይህም ማለት እንደ ውል ስምምነታቸው መሠረት ተፈጻሚ ሲሆን ነው።

6. እዳ መተው 1825

በለገንዘቡ የባለ እዳውን እዳ በተወ ጊዜ ውሉ ቀሪ ይሆናል። ይህም ማለት በአንድ ውል ውስጥ ተነጻጻሪ ግዴታዎች በተዋዋይ ወገኖች መካከል ቢኖሩም አንዳንድ ጊዜ አንድኛው ወገን ግዴታውን ፈጽሞ ሌላኛው ወገን ግዴታውን ሳይፈጽም የሚቀርበት ጊዜ ይኖራል በዚህን ጊዜ ባለመብቱ እዳን የተው እንደሆነ የውሉ ግዴታ ቀሪ ይሆናል።

7. የመብት እና እዳ መቀላቀል

የመብት እዳ መቀላቀል በሚያጋጥምበት ጊዜ ውሉ ቀሪ ይሆናል
ይህ የሚያጋጥመው ብዙ ጊዜ በአውራሽ እና በወራሽ መካከል በሚኖራቸው የውርስ ደንብ ሲሆን ቀድሞ የግዴታ መፈጸም ውል በአውራሹ ወይም በወራሹ ላይ ሲኖር በውርስ ክፍፍል ድርሻ አማካኝነት መብት እና እዳ መቀላቀል የሚከሰት ሲሆን በዚህ ጊዜ በውርሱ ክፍፍል ድርሻ ምክንያት ቀሪ የሚሆኑበት ነው።

8. ስለ ግዴታ መተካት 1826

የባለእዳው የውል ግዴታ በሌላ ግዴታ እንዲተካ ከባለመብቱ ጋር ስምምነት ሲያደርጉ የመጀመሪያው የውል ግዴታ ቀሪ የሚሆንበት ነው።

9. በይርጋ/በጊዜ መቆየት ምክንያት/

ውልን በተመለከተ በይርጋ ወይም በጊዜ ገደብ ምክንያት ቀሪ ይሆናል። በውል አለመፈጸም ምክንያት ወይም መሠረታዊ የውል መቋቋም ምክንያት በሚጠየቁ የውል ይፍረስልኝ፣ይሰረዝልኝ ወይም እንደ ውሉ ይፈጸምልኝ በፍርድ ቤት የሚጠየቁ መብቶች የጊዜ ገደብ ያላቸው ሲሆን ይህም ይርጋ በመባል ይታወቃል። በዚህም ጊዜ መጠየቅ ያለበት ጊዜ በማለፉ ምክንያት የባለእዳው ተዋዋይ ግዴታ ቀሪ የሚሆንበት ነው።

10. ማጠቃለያ የህግ ምክር

ከላይ የተመለከትናቸው በተዋዋይ ወገኖች መካከል የተደረጉ ውሎች በመካከላቸው የተደረጉ ግዴታዎች ቀሪ የሚሆንባቸው የህግ ምክንያት ሲሆን እነዚህ መታወቅ ያለባቸው መሠረታዊ የውልን ግዴታ ቀሪ የሚያደርጉ ነገሮች ናቸው።

ማጣቀሻዎች
1. የኢትዮጵያ ፍተሀብሔር ህግ
2. ፕሮፈሰር ጥላሁን ተሾመ ፥ የኢትዮጵያ መሠረታዊ የውል ህጎች

የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ (Brent Crude) በአንድ በርሜል 115.7 ዶላር ገብቷል   | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ለየለት ምድር ላይ ወረራ እያመራ ነው መባ...
30/03/2026

የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ (Brent Crude) በአንድ በርሜል 115.7 ዶላር ገብቷል

| በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ለየለት ምድር ላይ ወረራ እያመራ ነው መባሉን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ገበያ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ወድቋል።

አሜሪካ በሺዎች የሚቆጠሩ እግረኛ ወታደሮቿን ወደ ኢራን ለማስገባት የምድር ላይ ዘመቻ እቅድ እያዘጋጀች ነው የሚሉ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ። ይህንን ተከትሎ የኢራን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባገር

"ጠላት በግልጽ ስለ ድርድር እያወራ በጓሮ ወረራ እያቀደ ነው፤ እኛ ግን የአሜሪካ ወታደሮች መሬታችንን እስኪረግጡ በጉጉት እየጠበቅን ነው፤ መጥተው በእሳት እንዲነዱና እንዲቃጠሉ እናደርጋቸዋለን" ሲሉ ዝተዋል።

ይህ ወታደራዊ ውጥረት በነዳጅ ገበያው ላይ እሳት ጭሯል። በዚህም መሠረት፦

* የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ (Brent Crude): በአንድ በርሜል 115.7 ዶላር ገብቷል።

* የአሜሪካ ዌስት ቴክሳስ (WTI): ዋጋው ወደ 102 ዶላር ከፍ ብሏል።

የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚተነብዩት ከሆነ፣ ውጥረቱ ሳይረግብ እስከ ሰኔ ወር ድረስ የሚቀጥል ከሆነ የአንድ በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 200 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ይህም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ጭማሪ ሊሆን ይችላል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)


#የነዳጅዋጋ #ኢራንእናአሜሪካ #የዓለምኢኮኖሚ #ሰበርዜና

Address

Gabon Avenue (Washington DC Square/Sterling Buildg)
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን):

Share

GETU TEMESGEN - (ጌጡ ተመስገን)

ጌጡ ተመስገን ውልደቱና እድገቱ አዲስ አበባ ነው። በጋዜጠኝነት ሙያው፤ ለአገር እና ለሕዝብ በሠራቸው አይረሴ ሥራዎቹ በርካታ ሽልማቶችን አግኝቷል። የፈረንሳይ ቴሌቪዥን ባሰባሰበው የተመልካቾች ምዘና መሠረት ‹‹ባለንሥሩ ጋዜጠኛ ~ A Journalist with an eagle eye›› የሚል ስያሜ አግኝቷል።

Getu Temesgen was born and raised in Addis Ababa. As a result of his unforgettable journalistic works/TV productions, he has won various recognitions. He was named “The Journalist with an eagle eye” in an audience poll conducted by French TV.

ሦስት ሥራዎቹም በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ቀርበውለታል። በአዘጋጁቹ ግብዣ አውሮፓ ፤ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ፈረንሳይና ቤልጅየም ተጉዞ፤ ትምህርታዊ ጉብኝት በማድረግ አገር ቤት ተመልሷል።

His three TV productions were also presented for European audience in French language and as a result was invited by the producers to visit France, Germany, Italy and Belgium.”