Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) I feel I am still a student, a beginner journalist with a great zeal to learn more.

I am climbing up the ladder and register remarkable achievement in my profession. This page is dedicated to serve you with reliable news and voice for voiceless.

♦️10 ሚሊየን ብር ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ቡድን ተበረከተ   | የኢትዮጵያ ከ 17 ዓመት በታች ብሄራዊ  ቡድን ቀይ ቀበሮዎቹ የከኬንያ አቻቸውን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፈ ሶስተኛ ደረጃን...
02/12/2025

♦️10 ሚሊየን ብር ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ቡድን ተበረከተ

| የኢትዮጵያ ከ 17 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን ቀይ ቀበሮዎቹ የከኬንያ አቻቸውን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፈ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው ለሞሮኮው የአፍሪካ ዋንጫ በማለፋቸው የ10ሚሊየን ብር ሽልማት ተበረከተላቸው።

በአሁን ሠዓት ኢሊሊ ሆቴል እየተካሄደ ባለው ስነ ስርዓት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር በሚኒስትሯ ክቡር ሸዊት ሻንካ አማካይነት እንደገለፁት ከሁለት አስርት ዓመታት በኃላ ወደ አህጉሪቱ መድረክ ለመለሱት ትናንሾቹ ኮከቦችና በአጠቃላይ ለቡድኑ አባላት የ10 ሚሊየን ብር ስጦታ ማበርከታቸው ተረጋግጧል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ደምቀው ላበሩት ኮከቦች ሁለት ጊዜ በማሸነፋቸው 200 እና 300 በድምሩ የግማሽ ሚሊየን ብር የገንዘብ ሽልማት ማበርከቱ ይታወሳል።

ከዚሁ ከብሄራዊ ቡድኑ የድል ዜና ሳንወጣ ታዳጊ ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ የኢ.ፊ.ድ.ሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የተከበሩ አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና የአዲስ አበባ ከንቲባ ክብርት አዳነች አቤቤ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸው የሚታወስ ሲሆን የከንቲባ ፅ/ቤትም ሽልማት ያበረክታል ተብሎ ይጠበቃል።

👉ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የሴካፋ ዞን የማጣሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ 2025 አሸናፊዎች

🏆 የውድድሩ ሻምፒዮን የዋንጫና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ታንዛኒያ 🇹🇿

🥈 የውድድሩ ሁለተኛና የብር ሜዳልያ ተሸላሚ ኡጋንዳ 🇺🇬

🥉 የውድድሩ ሶስተኛና የነሐስ ሜዳልያ ተሸላሚ ኢትዮጵያ 🇪🇹

🎖 የውድድሩ የስፖርታዊ ጨዋነት ተሸላሚ ኢትዮጵያ 🇪🇹

🏆 የሻምፒዮናው ምርጥ ተጫዋች ኦዌን ሙኪሳ ኡጋንዳ 🇺🇬

🏆 የሻምፒዮናው ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ዳዊት ካሳው ኢትዮጵያ 🇪🇹 እና ሉክማን ምባላሱሉ ታንዛኒያ(እኩል 8 ጎል)🇹🇿

🏆 የሻምፒዮናው ምርጥ ግብጠባቂ ሀጂ አብደላህ ታንዛኒያ 🇹🇿

🏆 የሻምፒዮናው ምርጥ አሠልጣኝ አሊንዛ ንሳንጋንዘሉ ታንዛኒያ 🇹🇿

✍️✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

የቅጅና ተዛማጅ መብቶች  በአዋጅ ቁጥር 410/1996 እና አዋጅ ቁጥር 872/2007    ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው 0929101037,0983337690          መግቢያ   ...
02/12/2025

የቅጅና ተዛማጅ መብቶች
በአዋጅ ቁጥር 410/1996 እና አዋጅ ቁጥር 872/2007

ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው 0929101037,0983337690

መግቢያ
| በዚህ አጭር ጽሁፍ የቅጅና ተዛማጅ መብት ምን እንደሆነ የስራ ፈጠራ ባለቤት መብት እንዴት ሊገኝ እንደሚችል እንዲሁም የፈጠራው ባለቤት የህግ ከለላ እና መብቶችን እንመለከታለን።

1. የቅጅና ተዛማጅ መብት ምንድን ነው?

1.1 ቅጅ መብት ማለት የኪነ-ጥበብ፣ ዕደ-ጥበብ፣ የስነ-ጽሑፍና የሳይንስ መስክ የፈጠራ ሥራዎች ባለበፈጠራ ስራዎቻቸው ላይ የሚኖራቸው የአእምሯዊ ንብርት መብት ነ እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር 410/1996 አንቀጽ 2(8) ላይ ያስቀምጣል።“ አመንጪ የሆነው ሰው ከስራው የሚያገኘው ኢኮኖሚያዊ እና የሞራል መብት ነው፡፡ እነኚህ የስራው አመንጪ መብቶች በአንቀጽ 7 እና 8 ላይ ተገልፆ ይገኛሉ፡፡ የሚገኝስብከት፣ ድራማ፣ ድራማዊ ሙዚቃ ስራ፣ የመድረክ ውዝዋዜ፣ የኦዲዮቪዥዋል ስራ፣

1.2 ተዛማች መብት ምንድነው?

በአዋጁ አንቀጽ 2 (14) ላይ “ተዛማጅ መብት ማለት ከዋኝ፣ የድምጽ ሪከርዲንግ ፕሮዲውሰር፣ የብሮድካስቲንግ ድርጅት በስራው ላይ ያለው መብት ነው” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡ የተዛማጅ መብቶች ባለቤት በስራዉ ላይ የሁለተኛ ደረጃ መብት ነዉ ያላቸዉ፡፡

2. አንድ ስራ የፈጠራ ነው ለማለት ምን ማሟላት አለበት?
በአዋጅ ቁጥር 410/1996 አንቀጽ 6(1) መሠረት የስራው አመንጪ ለስራው ጥበቃ ለማግኘት ስራው 1ኛ ወጥ (ኦርጅናል) መሆን ያለበት መሆኑ እና 2ኛ ስራው ግዙፋዊነት ያገኘ መሆን እንዳለበት እንደ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጧል፡፡

2.1 ወጥ (ኦርጅናል) መሆን

የስራ አመንጪው የስራው ስራ ከሌሎች ስራዎች ላይ ያልተቀዳ መሆን ያለበት ሲሆን ስራው ሰው የአእምሮ ውጤት መሆን አለበት

2.2 ግዙፋዊነት (የተቀረፀ) መሆን
በአዋጅ ቁጥር 410/1996 በአንቀጽ 2(1) ላይ መቅረጽ ወይም ግዝፈት እንዲያገኝ ማድረግ ማለት አንድ ስራ፣ ምስል ድምጽ ወይም የአንደኛቸው አምሳያ ምትክ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ መሳያ አማካኝት እንዲታይ፣ እንዲባዛ፣ ወይም እንደሆነ ይገልፃል፡፡

3. የፈጠራ ስራ አመንጪ መብቶች
የፈጠራ ስራ ባለቤት የሆነ ሰው ከስራው ኢኮኖሚያዊና የሞራል መብት እንደሚያገኝ እሙን ነው፡፡ በስነ ፅሁፍ፣ የኪነጥበብ ወይም በሳይንሳዊ ፈጠራ ስራ ላይ የተሰማራ ማንኛዉም ሰው እነዚህ መብቶች እንደሚያኝ በአዋጀ ቁጥር 410/1996 አንቀፅ 7 እና 8 ላይ ተገልፆ ይገኛል፡፡

3.1/ ኢኮኖሚያዊ መብት

የስራ አመንጪው ኢኮኖሚያዊ መብት ማለት ከፈጠራ ስራው የሚያኘው በገንዘብ ሊለካ የሚችል መብት ማለት ነው፡፡ ይህ መብቱም በአዋጁ አንቀፅ 7 ላይ እንደተገለፀው ስራውን የማባዛት፣ የመተርጐም፣ የማመሳሰል፣ የማቀናበር ወይም ወደ ሌላ አይነት መቀየር፣ በሽያጭ ወይም በኪራይ ኦርጅናል ስራን ወይም ቅጂውን የማከፋፈል፣ ኦርጂናል ስራን ወይም ቅጂውን ለህዝብ የማሳየት፣ በይፋ የመከወን፣ ብሮድካስት ማድረግ እና በሌላ መልክ ማስራጨትን የመሳሰሉት መብቶች ያሉት መሆኑን ይገልፃል፡፡

3.2/ የሞራል መብት

ይህ መብት በገንዘብ የማይተመን መብት ነው፡፡ ይህም የስራው አመንጪ ለሰራው ስራ ተገቢው እውቅና እንዲሰጠው የሚያደርግ መብት ነው፡፡ በአዋጅ አንቀፅ 8 ላይ እንደተገለፀው የስራው አመንጪው የኢኮኖሚ መብት ባለቤት ቢሆንም ባይሆንም ወቅትዊ ሁኔታን በብሮድካስት አማካኝነት ለመዘገብ ባጋጣሚ ወይም በድንገት ከተካተተ ውጪ ስራው የእሱ ውጤት ስለመሆኑ ለአመንጪቱ እንዲታወቅ የመጠየቅ፣ ሳይታወቅ የመቆየት ወይም የብዕር ስም የመጠቀም፣ ክብሩንና መልካም ስሙን የሚያጎድፍ የስራ መባዛት፣ መቆራረጥ ወይም በሌላ መልክ መቀየርን በፈጠራው ላይ ሌላ ሰው ያለፍቃዱ የሚጠቀም ከሆነ የመቃወም መብትን ጭምር የሚያካትት ነው፡፡

https://www.facebook.com

ያልተዘመረለት ጀግና የማስታወቂያ ሞዴልና ኤቨንት ኦርጋናይዘርኤርሚያስ ከበደ ጉዞ    |  ላለፉት አመታት በስራው እናውቀዋለን ኢርሚያስ ከበደ የተለያዩ ከ30 በላይ የቴሌቭዥን ማስታወቂያዎችን...
02/12/2025

ያልተዘመረለት ጀግና
የማስታወቂያ ሞዴልና ኤቨንት ኦርጋናይዘር
ኤርሚያስ ከበደ ጉዞ

| ላለፉት አመታት በስራው እናውቀዋለን ኢርሚያስ ከበደ የተለያዩ ከ30 በላይ የቴሌቭዥን ማስታወቂያዎችን በሞዴልነት ሰርቷል፡፡ በመልካም ስነ-ምግባርና ትህትና ከቅንነት ጋር የተላበሰ ባለሙያ ነው፡፡

ኤርሚያስ ከበደ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጀውን MISS WORLD ETHIOPIA በመባል የሚዘጋጀውን አለም ዓለም አቀፍ የቁኝጅና ውድድር እ.ኢ.አ ከ 2014 እስከ 2025 ከ ETHIOPIAN BEUTY QUEENS ድርጅት ጋር በመሆን ሲያዘጋጅ ቆይቷል፡፡

የተለያዩ ኤቨንቶችን በማዘጋጀትና በማስተባበር ከ15 ዓመት በላይ መልካም ስሙን ገንብቷል፡፡

ከሚሰራቸው ስራዎች በጥቂቱ፡- የተለያዩ ባዛሮችን ኤግዚቢሽኖችን በማስተባበር እና በማዘጋጀት የተዋጣለት ባለሙያ ነው፤ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ጥንቅቅ አድርጎ ይሰራል፣ ባህላዊ እና ዘመናዊ አልባሳቶችንና እና የቆዳ ምርቶቻችንን የሚያስተዋውቅ ኢንተርናሽናል የፋሽን ትሪኢቶችን በማዘጋጀት እና በማስተባበር የተዋጣለት ባለሙያ ነው፡፡

ከብዙ መንግስታዊ እና አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ፕሮግራሞች በግንባር ቀደምትነት ያዘጋጃል፡፡ በምግባረ ሰናይ ስራዎች ላይም በመሰማራት የራሱን አሻራ አስቀምጧል፡፡

ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ ባህሎቿንና ትውፊቶቿን የሚያስተዋውቁ አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድሮችን በማዘጋጀት የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በአለም አደባባይ በማስጠራት የሚታወቁ ኤቨንቶች በማዘጋጀት አሻራውን በማስቀመጥ ለዘርፉ መጎልበትና ማደግ ትልቅ አስተዋፅኦ ካለችው ባለሙያዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡ የፓሽን ፕሮሞሽንና ኤቨንት ድርጅት ባለቤትና መስራች ነው፡፡

ለተለያዩ የፕሮዳክሽን ካምፓኒዎችና ድርጅቶች ሞዴሎችን በማቅረብ እና በማሰራት ለብዙ ሞዴሎች ህልማቸውን እንዲያገኙ የስራ እድል በመፍጠር ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡

የተለያዩ ኢንተርናሽናል ስራዎችን ለመስራት በማሰብ ከአለም አቀፍ ኤጀንቶችና አገሮች ጋር በተደረገው መግባባት እና አብሮ የመስራት እቅድ በመያዝ ወደ ሦስት አገሮች ጉዞ ጀምሯል

እነሱም፡-
 አሜሪካ ፣ ጣሊያን እና ፈረንሳይ አገር ይፋዊ ስራ ጉዞ ያደርጋሉ ይህም ጉዞ ታላላቅ አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ስራ እንደሚሰራ ገልጾልናል ከዚህ በፊት በሰራቸው ታላላቅ አገራዊ ኤቨንቶችና የአሁኑን የስራ ጉዞ በማስመልከት ለስራው መቃናትና መሳካት አስተዋጾ ያበረከቱ ተቋማት ይመስገኑልኝ ብሏል

እነሱም፡-
1. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲማ ጽ/ቤት

2. አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ዶ/ር ሂሩት ካሳው እና ምክትላቸው አቶ ሀፍታይ እና የሁል ጊዜ ተባባሪያችን ወ/ሮ አዳነች እና ሁሉም የስራ ኃላፊዎች ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

3. ባህልና እስፖርት ሚኒስትር ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ እና ልበቀናው አቶ ኩመራ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ምስጋና ይቅረብልኝ፡፡

4. ቱሪዝም ሚኒስተር ዶ/ር እንደገና አበበ የሁል ጊዜ ተባባሪ እና ቅንነትና መልካምነት የማይለያቸው ለዘርፉ ማደግ በማንኛውም ሰዓት ዝግጁ ሰው ናቸው፡፡

ለሁሉም ታላቅ ምስጋና ይድረሳቸው፡፡ በተጨማሪ ክቡር አቶ ገበየው ታከለ የኢትዮጵያ ጅምናስቲክ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የሁልጊዜ ተባባሪ እና ወዳጅ ያመስግኑልኝ፣ አቶ ዘውገ ጀማነህ እና ፎከስ ኢትዮጵያ ምስጋና ይቅረብልኝ ብለዋል፡፡

5. ኢፌድሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

መልካም የስራ ጊዜ እንመኛለን፡፡

ከዳውሮ፣ ኢሰራ የገጠር መንደር ተነስተው ኤርትራ አስመራ፣ጃፓን ፉኩሽማ እና አሜሪካ ኮሎራዶ በትምህርት የረገጠው እግር   | ከ30 ዓመታት በላይ በምርምር ስራ ያሳለፉት አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር...
02/12/2025

ከዳውሮ፣ ኢሰራ የገጠር መንደር ተነስተው ኤርትራ አስመራ፣ጃፓን ፉኩሽማ እና አሜሪካ ኮሎራዶ በትምህርት የረገጠው እግር

| ከ30 ዓመታት በላይ በምርምር ስራ ያሳለፉት አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)…

በሀገር ወስጥና በውጭ ሀገራት በርካታ ውጤታማ የምርምር ሰራዎችን የሰሩ አንጋፋ ተመራማሪ ናቸው አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)።

አፈወርቅ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት÷ ከ30 ዓመታት በላይ በምርምር ስራ ላይ አሳልፈዋል፡፡

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን እሰራ ወረዳ በሚገኝ የገጠር መንደር ተወልደው ያደጉት አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) የልጅነት ጊዜያቸው ውጣውረድ የበዛበት እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡

በተወለዱበት አካባቢ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስላልነበረ ከሚኖሩበት አካባቢ 40 ኪሎ ሜትር በላይ በመጓዝ ስንቅ ቋጥረውና ቤት ተከራይተው ትምህርታቸውን ይከታተሉ ነበር፡፡

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በከፍተኛ ውጤት ካጠናቀቁ በኋላ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ ለማወቅ ከተወለዱበት ቦታ 120 ኪሎ ሜትር ርቃ ወደ ምትገኘው ጅማ ከተማ መጓዝ ነበረብኝ ይላሉ፡፡

ጅማ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ መኪና ያየሁባት እና የተሳፈርኩባት፣ ኮካ የጠጣሁባት፣ ፎቅና መብራት ያየሁባት ለእኔ የቴክኖሎጂ ከተማ ናት ሲሉም በፈገግታ ያስታውሳሉ፡፡

ከዛም ለከፍተኛ ትምህርት አስመራ ዩኒቨርሲቲ መመደባቸውን በማረጋገጥ ጉዟቸውን ወደ አስመራ ከተማ በማድረግ ለአንድ ዓመት ትምህርታቸውን ከተከታተሉ በኋላ ሻቢያና ደርግ ጦርነት ላይ የነበሩበት ወቅት ስለነበር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመዘዋወር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በባዮሎጅ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በረዳት ተመራማሪነት ሥራቸውን የጀመሩት አፈወርቅ (ፕ/ር)÷ ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በመዛወር ከሲኒዬር ተመራማሪነት እስከ ምክትል የዩኒቨርሲቲ ዲን በመሆን አገልግለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ የስራ ኃላፊነት ቦታዎች ሰርተዋል።

በአሁኑ ወቅት በአርማዎር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በዋና ዳሬክተርነት ሀገራቸውን በማገልገል ላይ የሚገኙት ፕሮፌሰሩ÷ የመመራመር ፍላጎታቸው በተግባር መገለጽ የጀመረው የዶሯቸውን እድሜ ስንት ሊሆን እንደሚችል የማወቅ ፍላጎት ባደረባቸው የልጅነት ጊዜ ሳይሆን እንዳልቀረ ያስታውሳሉ፡፡

የእሳቸው አበርክቶ በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም በርካታ ውጤታማ የምርምር ውጤቶችን ከማሳተም ጀምሮ በተለያዩ የስራ ተልዕኮዎች በጃፓንና በአሜሪካ አገልግለዋል፤ በምርምር ስራዎቻቸውም በርካታ እውቅና ተችሯቸዋል፡፡

አፈወርቅ (ፕ/ር) በዓለም አቀፍ ደረጃ ካገኟቸው እውቅናዎች መካከል በጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር የተበረከተላቸው የንጉስ ሽልማት ለአብነት ይጠቀሳል፡፡

በአመለወርቅ ደምሰው

አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ይከታተሉ👇
https://www.youtube.com/watch?v=Is8aYaFkzUU

ልባችሁ ካዘነ ለእርዳታ እጃችሁን ዘርጉ! 📍 የ8 ዓመቷን ህጻን ቃልኪዳንን እንታደግ! 🙏  | ህጻን ቃልኪዳን ማረግ ከተወለደችስምንት አመቷ ነው። በተወለደች በሰባት ወሯ ከመንታ እህቷ ጋር የ...
02/12/2025

ልባችሁ ካዘነ ለእርዳታ እጃችሁን ዘርጉ!

📍 የ8 ዓመቷን ህጻን ቃልኪዳንን እንታደግ! 🙏

| ህጻን ቃልኪዳን ማረግ ከተወለደች
ስምንት አመቷ ነው። በተወለደች በሰባት ወሯ ከመንታ እህቷ ጋር የተወለደች ሲሆን፣ መንታ እህቷ በሙሉ ጤነኝነት ሁለተኛ ክፍል በመማር ላይ ይገኛል።

ሆኖም ግን ህጻን ቃልኪዳን ማረግ ከተወለደች ጊዜ አንስቶ ላለፉት ስምንት አመታት ባጋጠማት የጭንቅላት ህመም ምክንያት በህክምና እየታገዘች ትገኛለች።

ህጻን ቃልኪዳን የጭንቅላት ቀዶ ጥገና ሁለት ጊዜ ተደርጎላት የጭንቅላቷ ክፍል በጎማ እንዲተካ ተደርጓል። ህጿኗ አሁን ላይ የምትኖረው በመድኃኒት ኃይል ብቻ ነው።

ለመድኃኒት እና ለተያያዥ ጉዳዮች በየቀኑ ከ2,500 ብር በላይ እየተጠየቀች ይገኛል። ቤተሰቦቿ የገጠማቸውን ከባድ የገንዘብ ጫና መቋቋም አቅቷቸዋል። በፈጣሪ ስም ይህንን ሁሉ በምትችሉት አቅም ከፈጣሪ ጋር በመሆን እንድትረዷት በትህትና እንጠይቃለን!

💰 የእርዳታ ማሰባሰቢያ አካውንቶች:
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአካውንት ቁጥር
📍 1000128238887
አባይ ባንክ
📍 9431019469731190

📞 ለበለጠ መረጃ:
0913116966
0923298783

🙏 ሼር በማድረግ በምትችሉት አቅም አግዙን!

የኤል ቻፖ ልጅ በአሜሪካ የአደንዛዥ ዕፅ ክስ ጥፋተኛ ነኝ ሲል ተናገረ  | የሜክሲኮ የአደንዛዥ ዕፅ ንጉስ ልጅ የሆነው ጆአኩዊን "ኤል ቻፖ" ጉዝማን ልጅ ጆአኩዊን ጉዝማን ሎፔዝ በቺካጎ ፍር...
02/12/2025

የኤል ቻፖ ልጅ በአሜሪካ የአደንዛዥ ዕፅ ክስ ጥፋተኛ ነኝ ሲል ተናገረ

| የሜክሲኮ የአደንዛዥ ዕፅ ንጉስ ልጅ የሆነው ጆአኩዊን "ኤል ቻፖ" ጉዝማን ልጅ ጆአኩዊን ጉዝማን ሎፔዝ በቺካጎ ፍርድ ቤት በሁለት የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች እና የተደራጁ የወንጀል ክሶችን በሜክሲኮ ታዋቂው ሲናሎአ ካርቴል ውስጥ በፈጸመው ተግባር ጥፋተኛ ነኝ ሲል አምኗል።

ጉዝማን ሎፔዝ ጥፋተኛ ነኝ ሲል በቁጭት ተናግሯል። በችሎቱ መጀመሪያ ላይ ለሰሜን ኢሊኖይ አውራጃ የዩናይትድ ስቴትስ ዲስትሪክት ፍርድ ቤት ዳኛ ሻሮን ኮልማን ፊት ቀርቦ ምን እንደሰራ ተጠይቋል፡፡

ጉዝማን ሎፔዝ “የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ነዉ” ሲል መልሷል።በጉዝማን ሎፔዝ ላይ የጥፋተኝነት ክስ በመመስረቱ ከአሜሪካ አቃቤ ህግ ጋር በመተባበር የፈፀመውን ወንጀል የሚወክል የ80 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ በመክፈል ከህይወት ዘመን እስራት እንደሚያመልጥ ይጠበቃል ሲል ዘገባዎች አመላክተዋል።

ይህም ሆኖ ግን ቢያንስ የ10 አመት እስራት እንደሚጠብቀው የፌደራል መንግስት ጠበቃ የሆኑት አንድሪው ኤርስስኪን ተናግረዋል።ጉዝማን ሎፔዝ በዳኛ ቅጣት የሚተላለፍ ሲሆን ይግባኝ ለማለት ግን እድል አይኖረውም ሲል ዘገባዎች ያስረዳሉ።

የጉዝማን ሎፔዝ ተከላካይ ጠበቃ ጄፍሪ ሊችማን ከችሎቱ በኋላ “መንግስት እስካሁን ከጆአኩዊን ጋር በጣም ፍትሃዊ ነው” ብለዋል።ሊችማን “የሜክሲኮ መንግሥት ጣልቃ አለመግባቱን አደንቃለሁ” ብለዋል።

የቺካጎ ትሪቡን ዘገባ እንደሚያመለክተው በ35 ገፁ የይግባኝ ስምምነት ላይ ጉዝማን ሎፔዝና ወንድሞቹ ለባለሥልጣናቱ ጉቦ በመስጠት እና የጦር መሳሪያ እና ሌሎች መሳሪያዎችን በማሰማራት የህግ አስከባሪዎችን፣ ተቀናቃኝ አዘዋዋሪዎችን እና ሌላው ቀርቶ የራሳቸው ድርጅት አባላትን ያነጣጠረ ጥቃት እንዲፈጽሙ በማድረግ የአደንዛዣ እጽ ዝዉዉር ቡድን እንቅስቃሴ እንዳሳደጉ አምነዋል ያለው ዳጉ ጆርናል ነው።

የ10,000,000 (አስር ሚሊዮን) ብር ሽልማት ተበረከተላቸው   | የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ከ17 ዓመት በታች ብ/ቡድናችን የ10,000,000...
02/12/2025

የ10,000,000 (አስር ሚሊዮን) ብር ሽልማት ተበረከተላቸው

| የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ላለፈው ከ17 ዓመት በታች ብ/ቡድናችን የ10,000,000 (አስር ሚሊዮን) ብር ሽልማት አበርክቷል።

ይቀጥላል...

ሚስቱንና ጎረቤቱን ገድሎ የተሰወረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ  | የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ህዳር 04 እና 05 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው 23 ቀበሌ ...
02/12/2025

ሚስቱንና ጎረቤቱን ገድሎ የተሰወረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

| የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ህዳር 04 እና 05 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው 23 ቀበሌ መዝናናኛ ክበብ አካባቢ ነው፡፡

ተከሳሽ እሱያውቃል ቢያዝን ከባለቤቱ ከወ/ሮ ሐመልማል አለምነው ጋር በትዳር ተጣምረው መኖር ከጀመሩ አራት ወራትን አስቆጥረዋል፡፡

ተጠርጣሪው ባለቤቱን ከሌላ ወንድ ጋር ስልክ ትደዋወያለሽ ከሌላ ሰው ፍቅር ጀምረሻል በሚል አጉል ጥርጣሬ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 4 ሠዓት አንገቷን አንቆ በመግደል ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ በር ዘግቶባት ከአካባቢው ይሰወራል፡፡

በተጨማሪም ከአንድ ቀን በኋላ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ/ም ወደ መኖሪያ ግቢው ተመልሶ በመምጣት የ2 ልጆች አባት የሆነውን ወርቁ በቀለን ከምሽቱ 1ሰዓት በመኖሪያ ቤት ውስጥ በስምንት ጥይት ተኩሶ በመግደል ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ከአካባቢው ይሰወራል፡፡

የአቶ ወርቁ በቀለ በጥይት ተመተው መሞት መረጃ የደረሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና ክትትል ክፍል የወንጀል ስፍራው ላይ በመገኘት እና መረጃ በማሰባሰብ ላይ ባሉበት ሁኔታ የገዳይ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሰው መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሙከራ ሲደረግ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የሐመልማል አለምነው አስከሬንም ሊገኝ ችሏል፡፡

ወንጀል ፈፃሚውን በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞላሌ ከተማ ከተደበቀበት አልጋ ቤት ውስጥ የግድያ ወንጀሉን ከፈፀመበት ኢኮልፒ ሽጉጥ እና ከ23 ጥይቶች ጋር ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ሊያውለውም ችሏል፡፡

ግለሰቡ የወንጀል አፈፃጸሙን አስመልክቶ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ/ም መርቶ ማሳየቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

አ.አ ፖሊስ

ቻይና የወሊድ ምጣኔን ለመጨመር ሲባል በኮንዶምና በእርግዝና መከለካከያ ክኒኖች ላይ ግብር ልትጥል ነው  | ​ቻይና ከ30 ዓመታት በኋላ በወሊድ መቆጣጠሪያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ላይ ...
02/12/2025

ቻይና የወሊድ ምጣኔን ለመጨመር ሲባል በኮንዶምና በእርግዝና መከለካከያ ክኒኖች ላይ ግብር ልትጥል ነው

| ​ቻይና ከ30 ዓመታት በኋላ በወሊድ መቆጣጠሪያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ላይ ግብር ለመጣል ጫፍ ላይ ናት።

​ብሉምበርግ እንደዘገበው ከሆነ፣ ቻይና ለሶስት አስርት ዓመታት ያህል ለመጀመሪያ ጊዜ ኮንዶሞችን ጨምሮ በወሊድ መቆጣጠሪያ ክኒኖችና ምርቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ልትጥል ነው።

ይህ እርምጃ፣ እንደ ዘገባው ከሆነ፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ፍጥነት በእጅጉ ሊቀንስ ያለውን እየቀነሰ ያለውን የወሊድ ምጣኔ ለመግታት ቤጂንግ የወሰደችው የቅርብ ጊዜ ጥረት ነው።

​በተሻሻለው የተጨማሪ እሴት ታክስ ህግ መሠረት፣ ከ1993 ጀምሮ ከቀረጥ ነጻ በሆኑ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ላይ ሸማቾች አሁን 13 በመቶ ግብር ይከፍላሉ። በዚያን ጊዜ ቻይና ጥብቅ የሆነውን የ"አንድ ልጅ ፖሊሲ" ተግባራዊ ያደረገች ሲሆን፣ ለቤተሰብ እቅድ ፈንዶች የግብር ቅነሳን ጨምሮ፣ የወሊድ መቆጣጠርን በንቃት ታበረታታ ነበር።

​በተመሳሳይ ጊዜ፣ ማሻሻያዎቹ ለወደፊት ወላጆች አዳዲስ ማበረታቻዎችን ይሰጣሉ። የሕፃናት ማቆያ እና መዋለ ሕጻናት፣ እንዲሁም የአረጋውያን እንክብካቤ ተቋማት፣ ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጡ የድጋፍ አገልግሎቶች እና ከጋብቻ ጋር የተያያዙ ተግባራት ከግብር ነጻ ይሆናሉ።

​ለውጦቹ ተግባራዊ የሚሆኑት በመጪው ጥር ላይ ነው።

​የቻይና ህዝብ ቁጥር በተከታታይ ለሶስተኛ ዓመት እየቀነሰ ነው። እ.ኤ.አ. በ2024፣ 9.54 ሚሊዮን ሕፃናት ብቻ የተወለዱ ሲሆን፣ ይህም የአንድ ልጅ ፖሊሲ ከተወገደ በኋላ ከአሥር ዓመት ገደማ በፊት ከተመዘገቡት 18.8 ሚሊዮን አዲስ የተወለዱ ሕፃናት ቁጥር ከግማሽ በላይ ያነሰ ነው።

የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ   | የኢትዮጵያ U-17 አጥቂ ዳዊት ካሳው በስምንት ጎሎች የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቋል።የታንዛኒያው አጥቂ ምባላሳሉ በተመሳሳይ ስምንት ጎ...
02/12/2025

የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ

| የኢትዮጵያ U-17 አጥቂ ዳዊት ካሳው በስምንት ጎሎች የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን አጠናቋል።

የታንዛኒያው አጥቂ ምባላሳሉ በተመሳሳይ ስምንት ጎል አስቆጥሯል

02/12/2025

✨ ታላቅ የምሥራች መግቢያ ✨

🙏 እግዚአብሔር ለሕዝቦቹ ደስታ የፈጠራት
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በኪደተ እግሩ ወደ ባረካት፣ ወደ ቅድስቲቱ ሀገር በ 400 ብር ብቻ አብራችሁ ተጓዙ። ✈️⛪

⛪ በዚህ ትልቅ እድል
✔️ አንድ ቤተክርስቲያን ይሰራል
✔️ ባለእድል ከሆናችሁ ወደ ቅድስቲቷን ሀገር ከእኛ ጋር ትጓዛላችሁ። 🙏🌍

🎟️ የትኬቱ ገቢ
➡️ ለ በሻሌ ደብረ ፀሐይ ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ሕንፃ ቤተክርስቲያን ማሠሪያ
➡️ በ ቤተልሄም ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የተዘጋጀው የሰብአ ሰገል ምስጋና ፕሮግራም ላይ ባለእድለኞች እንዲሳተፉ ይደረጋል። 🌟

⏳ ስለዚህ፣ ፈጥነው ትኬቱን ይያዙ!

🙏 አገልግሎቱን ይደግፉ፣
🌟 እኛ ጋር ባለእድል ይሁኑ፣
✈️ ወደ ቅድስቲቷን ምድር ኢየሩሳሌም አብረን እንጓዝ።

💳 ትኬት የሚገኝበት:
📱 በቴሌብር
🏢 ወይም በድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት

አዘጋጅ፡
ሰመርነሃ ኩነቶች —
ፊጋ መብራቱ ጋር ሳይደርሱ ሄሊ፣ ሕንፃ 3ኛ ፎቅ

📞 ለበለጠ መረጃ:
📲 09 89 444 888

ፍቅር፣ እምነት፣ ተስፋ በአንድ መንገድ ይዛመዱ። ✨🙏

Address

Gabon Avenue (Washington DC Square/Sterling Buildg)
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን):

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

GETU TEMESGEN - (ጌጡ ተመስገን)

ጌጡ ተመስገን ውልደቱና እድገቱ አዲስ አበባ ነው። በጋዜጠኝነት ሙያው፤ ለአገር እና ለሕዝብ በሠራቸው አይረሴ ሥራዎቹ በርካታ ሽልማቶችን አግኝቷል። የፈረንሳይ ቴሌቪዥን ባሰባሰበው የተመልካቾች ምዘና መሠረት ‹‹ባለንሥሩ ጋዜጠኛ ~ A Journalist with an eagle eye›› የሚል ስያሜ አግኝቷል።

Getu Temesgen was born and raised in Addis Ababa. As a result of his unforgettable journalistic works/TV productions, he has won various recognitions. He was named “The Journalist with an eagle eye” in an audience poll conducted by French TV.

ሦስት ሥራዎቹም በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ቀርበውለታል። በአዘጋጁቹ ግብዣ አውሮፓ ፤ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ፈረንሳይና ቤልጅየም ተጉዞ፤ ትምህርታዊ ጉብኝት በማድረግ አገር ቤት ተመልሷል።

His three TV productions were also presented for European audience in French language and as a result was invited by the producers to visit France, Germany, Italy and Belgium.”