Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) I feel I am still a student, a beginner journalist with a great zeal to learn more.

I am climbing up the ladder and register remarkable achievement in my profession. This page is dedicated to serve you with reliable news and voice for voiceless.

ለሠላድንጋይ ትምህርት ቤት የቤተ-መጽሐፍት ግንባታ​"የዛሬው አሻራችን የነገው ትውልድ ብርሃን ነው!"  | ​የሠላድንጋይ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች፣ የአካባቢው ተወላ...
01/01/2026

ለሠላድንጋይ ትምህርት ቤት የቤተ-መጽሐፍት ግንባታ

​"የዛሬው አሻራችን የነገው ትውልድ ብርሃን ነው!"

| ​የሠላድንጋይ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች፣ የአካባቢው ተወላጆች እና የትምህርት ወዳጆች በሙሉ፤ ትምህርት ቤታችን በአሁኑ ወቅት ቤተ-መፅሐፍቱ በጊዜያዊ መጠለያ (ቆርቆሮ) ውስጥ ይገኛል። ይህንን ሁኔታ ለመቀየር እና ተተኪ ተማሪዎችን በዕውቀት ለማነጽ የሁላችንንም እጅ ይፈልጋል።

​🎯 የንቅናቄው ዋና ዓላማዎች፡-

​ቋሚ ግንባታ፦ ዘመናዊ እና ምቹ የቤተ-መፅሐፍት ህንፃ መገንባት።

​የመፅሐፍት አቅርቦት፦ ለአዲሱ የትምህርት ሥርዓት (Curriculum) የሚመጥኑ መፅሐፍትን ማሟላት።
​ዲጂታል ትምህርት፦ የኮምፒውተር ላብራቶሪ በማደራጀት ተማሪዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር ማስተዋወቅ።

​💰 የድጋፍ ማድረጊያ መንገዶች (የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች)
​በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአቢሲኒያ ወይም በአባይ ባንክ በኩል ድጋፍዎን ማድረግ ይችላሉ፡-

የባንክ አካውንቶች

የሠላድንጋይ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት

➖ንግድ ባንክ-1000737203666
➖አቢሲኒያ ባንክ-246098824
➖አባይ ባንክ-4571112673084017

ማሳሰቢያ፦ ድጋፍ ካደረጉ በኋላ ለትምህርት ቤቱ እውቅና እና ምስጋና እንዲመች ደረሰኝዎን ከታች ባሉት ስልኮች በቴሌግራም ወይም በዋትስአፕ ይላኩ።

​📞 ለበለጠ መረጃ፡-

​+2519 13 50 92 99
​+2519 13 39 91 68
​+2519 11 39 96 86

​"የአንድ ቀን ምሳ ወጪያችን ለአንድ ትውልድ ዕውቀት ይተርፋል!"

​ይህ መልዕክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩ።

"ደራሲ ለምን ድሃ ይሆናል?" በተስፋአብ ተሾመ   | አገራችን ድሃ ናት። በድሃ አገር የምንኖር ድሆች ነን። ማጣት በቡጢ ይነርተናል፥ የቤት ኪራይ በአግባብ መክፈል ወደ ተራራ የመሮጥ ያህል ...
01/01/2026

"ደራሲ ለምን ድሃ ይሆናል?" በተስፋአብ ተሾመ

| አገራችን ድሃ ናት። በድሃ አገር የምንኖር ድሆች ነን። ማጣት በቡጢ ይነርተናል፥ የቤት ኪራይ በአግባብ መክፈል ወደ ተራራ የመሮጥ ያህል ፈታኝ ነው።

እዚህ አገር የልፋቱን ያህል የሚያገኝ ሰው ማግኘት ከባድ ነው። ዶክተሮች ለቤት ኪራይ ይቸገራሉ። መምህራን ይራባሉ። ጋዜጠኞች ደሞዛቸው አያኖራቸውም። ሁሉም ሰው ይቸገራል።
ከእጅ ወደ አፍ ለመኖር እንኳን መከራ ነው።

ድህነት በጨካኝ አለንጋ ከሚገርፋቸው መካከል ደራሲያን አሉ።

ደራሲያን ለምን ይደኸያሉ?

አምስት መጽሐፍትን የፃፈ ሰው ለቤት ኪራይ ሲቸገር ማየት አይገርምም። ደራሲያን መጽሐፍ ባሳተሙ ማግስት ብድር ፍለጋ ሊሰማሩ ይችላሉ። የዚህ ሰበቡ ብዙ ነው።

ደራሲያንን ለችግር ከሚዳርጉ ብዙ ምክኒያቶች መካከል አንዱ ሲስተም ነው። የተበላሸ ሲስተም...

በገዛ ገንዘብ መጽሐፍ ማሳተም እጅግ ፈታኝ ነው። የህትመት ዋጋ ውድ ነው። በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ መጽሐፍ ለማሳተም ወጪ ማድረግ ቀላል አይደለም። ባለጠጋ መሆን ይጠይቃል። ለመጽሐፍ ስራ ስፖንሰር ማግኘትም አይቻልም። ደራሲን ማበረታታት የሚታሰብ አይደለም።

ነገር ግን በብድር ፥ ወይንም ንብረት በመሸጥ አሊያም በሌላ መንገድ ገንዘብ አግኝቶ መጽሐፍ ያሳተመ ሰው አደገኛ ቁማር እየተጫወተ ነው። የመክሰር እድሉ ከፍተኛ ነው።

1 ሺ ኮፒ ብቻ ለመሸጥ ሁለት አመት የሚፈጅባቸው ደራሲያን ብዙ ናቸው። ገዢ የለም። አንባቢው መጽሐፍ ለመግዛት ስለ መጽሐፉ ማወቅ ይፈልጋል። ለማስተዋወቅ ትክክለኛው ቦታ ደግሞ ሚዲያ ነው።

ሚዲያው ግን ደራሲያንን እንግዳ ማድረግ አይፈልግም። ለቲክቶከር ፥ ለኮሜዲያን ፥ ለተሳዳቢ ፥ ለሰባኪ ፥ ለጠንቋይ ፥ ለሹመኛ ወዘተ ሚዲያው የተትረፈረፈ ጊዜ አለው። ደራሲውን ለማቅረብ ግን ጊዜ የለውም። (ለነገሩ የማያነቡ ጋዜጠኞችም አሉ)

መጽሐፍት ቤት ገንዘብ በአግባቡ አይከፍሉም። መቶ ሺ ብር ያለበት መጽሐፍ ነጋዴ ለደራሲው 5 ሺ ብር ብቻ ይከፍል እና የ3 ወር ቀጠሮ ይሰጠዋል። በየሶስት ወሩ ደጅ እየጠኑ 5 ሺ ብር መቀበል ምን ይበጃል?

እኔ እንኳን ገንዘቤን ወስደው ተስፋ ቆርጬ የተውኳቸው ነጋዴዎች አሉ። በቸገረኝ ወቅት መጽሐፌን ሸጦ የጨረሰ ነጋዴን ብሬን ጠየቅኩት። ከለከለኝ። ግራ ቢገባኝ ከ Bilal M Guwale ብር ተቀበልኩ።
ሌሎቹን "በቃ ብሬን ውሰዱት" ብዬ ትቼላቸዋለሁ።

ብዙ ሰው መጽሐፉ ጀርባ ላይ ያለው ገንዘብ በሙሉ ለደራሲው የሚደርስ ይመስላቸዋል። ይህ ስህተት ነው።

መጽሐፍ ማተሚያ ቤቱ እስከ 1/3ኛውን ገንዘብ ይወስዳል። የጀርባ ዋጋው 300 ብር የሆነ መጽሐፍ እስከ መቶ ብር ድረስ ለህትመት ወጥቶበታል። ችግሩ ይህ ብቻ አይደለም። አከፋፋይ ከ35- 50 ፐርሰንት ድረስ ይቆርጣል። በራስ ማሳተም ከባድ ስለሆነ አሳታሚ መጠቀም የግድ ነው። ስለዚህ የአሳታሚውም ድርሻ አለ።

በቀላል ሂሳብ ላስረዳችሁ።

አንድ መጽሐፍ የጀርባ ዋጋው 300 ብር ነው። እንበል።
ለማሳተም 100 ብር ወጣ።
አካፋፋይ 35 በመቶ ይቆርጣል። የ 300 ብር 35 በመቶ 105 ብር ነው።
ስለዚህ 100 +105 =205። የመጽሐፉ ትርፍ 95 ብር ሆነ ማለት ነው።
የአሳታሚ ገንዘብ ይቀነሳል። አሳታሚ ከትርፉ እስከ 50 ፐርሰንት ይወስዳል። የ95 ብር ግማሽ 47 ብር ከ50 ሳንቲም ሆነ።

እንግዲ የጀርባ ዋጋው 300 ብር ከሆነ መጽሐፍ ላይ ደራሲው 47 ብር ይደርሰዋል።

ችግሩ ይህ ብቻ አይደለም። በርካታ ስጦታ ፈላጊ ሰዎች አሉ። ደራሲው በኪሳራ ስጦታ ይሰጣቸዋል።
ይህ ሳያንስ 47 ብር ትርፉን በአመታት ተከፋፍሎ ይወስደዋል።

ላስረዳ... ሁለት ሺ ኮፒ ቢታተም የደራሲው ትርፍ 95 ሺ ብር ይሆናል። (በነገራችን ላይ 2 ሺ ደፍሮ የሚያሳትም ሰው ጥቂት ነው። ብዙ ሰው አንድ ሺ ኮፒ ነው የሚያሳትመው)

ያቺን ብር ለመቀበል ሲሄድ ደጅ ያስጠኑታል። በብዙ መንከራተት 5 ሺብር ይሰጠዋል። ቀሪውን ለመውሰድ ምናልባት ሁለት ወር ሊጠብቅ ይችላል። ከወራት ጥበቃ በኋላ 10 ሺ ብር ይቀበል ይሆናል። እንዲህ እንዲህ እያለ ይሰለቸዋል። ስለዚህ የገዛ ልፋቱን ይተወዋል።

ደራሲውን ያደኸየው ሲስተሙ ነው። ማንም ለደራሲው ግድ የለውም። ደራሲው መከራ በልቶ ያሳተመውን ማንም መንገደኛ በ Pdf ያሰራጭበታል።

ሚዲያው ለደራሲው ግድ የለውም። መንግስት ስለ ደራሲ አያስብም። የደራሲያን ማህበር እንኳን የደራሲን መብት አያስከብርም።

ደራሲ ቢደኸይ አይገርምም።

ታዋቂው የሙዚቃ ጣቢያ MTV ስርጭት አቆመ📌የዲጂታሉን ዓለም መገዳደር አልቻለም  | ለተከታታይ አራት አስርት ዓመታት የዓለምን የሙዚቃ ኢንዱስትሪና የፖፕ ባሕል (Pop Culture) ሲመራ የ...
01/01/2026

ታዋቂው የሙዚቃ ጣቢያ MTV ስርጭት አቆመ

📌የዲጂታሉን ዓለም መገዳደር አልቻለም

| ለተከታታይ አራት አስርት ዓመታት የዓለምን የሙዚቃ ኢንዱስትሪና የፖፕ ባሕል (Pop Culture) ሲመራ የቆየው ታዋቂው MTV፣ የቴሌቪዥን ስርጭቱን ስለማቆሙ መረጃዎች እየወጡ ነው።

ጣቢያው በተለይም በፈረንጆቹ 1980ዎቹ እና 90ዎቹ የሙዚቃ ቪዲዮዎችን ለዓለም በማስተዋወቅና የበርካታ ታዋቂ አርቲስቶችን ስም በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ነበረው።

ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተመልካቾች ወደ ዲጂታል አማራጮች እንደ YouTube እና TikTok መዞራቸው ለጣቢያው መዳከም ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ተመልክቷል።

የስርጭቱ መቋረጥ ምክንያቶች፡-

* የዲጂታል አማራጮች መስፋፋት፡ ተመልካቾች የሙዚቃ ቪዲዮዎችን በቴሌቪዥን ከመጠበቅ ይልቅ በማንኛውም ሰዓት በኢንተርኔት ማግኘታቸው።

* የተመልካች ቁጥር መቀነስ፡ የወጣቱ ትውልድ ትኩረት ከባህላዊ የኬብል ቴሌቪዥን ወደ ማህበራዊ ሚዲያዎችናየቀጥታ ስሬጭቶች አገልግሎቶች መሸጋገሩ።

* የይዘት ለውጥ፡ MTV ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሙዚቃ ይልቅ በሪያሊቲ ሾው (Reality Shows) ላይ ማተኮሩ የነበረውን ተቀባይነት እንዲቀንስ አድርጎታል።

MTV እ.ኤ.አ. ነሐሴ 1 ቀን 1981 ስርጭቱን ሲጀምር የመጀመሪያው የቪዲዮ ሙዚቃ "Video Killed the Radio Star" እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይ ደግሞ የኢንተርኔት ዓለም በቴሌቪዥን ስርጭቱ ላይ ተመሳሳይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።

ምንም እንኳን ቴሌቪዥን ስርጭቱ ቢቆምም፣ ብራንዱ በዲጂታል መድረኮች እና በተለያዩ ዝግጅቶች (እንደ MTV VMAs ሽልማት) ህልውናውን ሊቀጥል እንደሚችል ይገመታል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

01/01/2026

ኦርቶዶክሳውያን የጀመራችሁትን አስጨርሱልን !!!

ለገላን ሰሚ በዕለቱ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እንድረስለት !!!

✝️ ከአዲስ አበባ በ32 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ጥንታዊ ቤተክርስቲያን ከተመሠረተ ከመቶ ዓመታት በላይ ሆኖታል።

✝️ ይሁንና በዚህ ሰዓት ግድግዳው በሙሉ በምስጥ እየተበላ ቤተክርስቲያኑ ከፍተኛ አደጋ ላይ ወድቋል

✝️ በሀገር ውስጥም በውጪ ሀገራትም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ተባብረን ቤተክርስቲያኑን ከመፍረስ እናድነው

✝️ አሁን ላይ በ5ወር ጊዜ በፍጥነት እየተሰራ የጣራ ስራ ላይ ስለደረሰ ለጣራ ስራ እጃችሁን ዘርጉልን።

✝️ የገዳሙ የባንክ አካውንት
1000265718063 - ኢ.ን. ባ /CBE/

✝️ ለበለጠ መረጃ በ +251950008283 ይደውሉ

በዚህ ጥሪ ላይ በመሳተፍ የበረከት ተካፋይ እንሁን። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጥበቃና ተራዳኢነት አይለየን።




#ቅዱሳን
#ተዋህዶ
#ድንግል

#ኢትዮጵያ

   | በአዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 40 ፕሮ ፕላስ ድምቅ ይበሉ!!
01/01/2026

| በአዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 40 ፕሮ ፕላስ ድምቅ ይበሉ!!

ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ቤተ-መጻሕፍቱን በዓለም አቀፉ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ ስም ሰየመ📌ታዋቂው የግብርና ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ የአፍሪካ ወጣቶች ለአህጉሪቱ ለውጥ በ...
01/01/2026

ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ቤተ-መጻሕፍቱን በዓለም አቀፉ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ ስም ሰየመ

📌ታዋቂው የግብርና ሳይንቲስት ፕሮፌሰር
ፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ የአፍሪካ ወጣቶች ለአህጉሪቱ ለውጥ በፈጠራና በትምህርት እንዲነሱ ጥሪ አቀቅርበዋል

| በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ-ጥሩ የሆኑት የዕፅዋት ተመራማሪና የዓለም የምግብ ሽልማት ተሸላሚው ፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ፣ የአፍሪካ ወጣቶች የዕውቀትና የፈጠራ ባለቤት በመሆን የአህጉሪቱን ትንሳኤ እንዲያረጋግጡ አሳሰቡ።

ፕሮፌሰሩ ይህንን ያሉት በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው "የአፍሪካ ወጣቶች ለአፍሪካ ለውጥ" በሚል ርዕስ ለተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ባደረጉት አነቃቂ ንግግር ነው።

🏫 የዕውቀትና የቴክኖሎጂ አስፈላጊነት

ፕሮፌሰር ገቢሳ በንግግራቸው ወቅት እንደ አሜሪካ፣ አውሮፓ እና የእስያ ነብሮች (Asian Tigers) ያሉ የበለጸጉ ሀገራት ለስኬት የበቁት በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በፈጠራ መሆኑን ጠቅሰዋል። "ከ400 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የአፍሪካ ወጣት ትምህርት ላይ በማተኮር የሚጠበቅበትን ሚና ሊወጣ ይገባል" ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ወጣቱ ዓለም አቀፍና አካባቢያዊ ችግሮችን ለመፍታት ራሱን በቴክኖሎጂ ማስታጠቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

⌛️ "ስኬት በስነስርዓት ይገኛል"

ፕሮፌሰሩ በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በነበሩበት ወቅት የነበራቸውን የጥናትና የጊዜ አጠቃቀም ልምድ ለወጣቶቹ አካፍለዋል።

"ትኩረቴን ትምህርቴ ላይ አደርግ ነበር፣ በትርፍ ጊዜዬም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሰርቼ ተጨማሪ ገቢ አገኝ ነበር፤ ለራስ ማዝናኛ ደግሞ ቅርጫት ኳስ እጫወት ነበር" በማለት ስኬት የሚገኘው ጊዜን በአግባቡ በመጠቀምና በጠንካራ ስራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ለፕሮፌሰሩ የተሰጠ ታላቅ ክብር🎖

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጀማል የሱፍ፣ ፕሮፌሰሩ ልምዳቸውን ለወጣቱ ለማካፈል በመምጣታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዩኒቨርሲቲው ለፕሮፌሰር ገቢሳ እጄታ ያለውን ክብር ለመግለጽም፡-

* የቤተ-መጻሕፍት ስያሜ፡ የዩኒቨርሲቲው ማዕከላዊ ቤተ-መጻሕፍት በፕሮፌሰሩ ስም እንዲሰየም ተደርጓል።

* ዲጂታል ኤግዚቢሽን፡ የፕሮፌሰሩን ከ260 በላይ የምርምር ጽሑፎች፣ ከአሜሪካ ፕሬዝዳንትና ከዓለም የምግብ ፕሮግራም ያገኟቸውን ሽልማቶች እንዲሁም የህይወት ታሪካቸውን የሚያሳይ ዲጂታል ኤግዚቢሽን ተመርቋል።

ፕሮፌሰር ገቢሳ እና ቤተሰቦቻቸው በስሟቸው የተሰየመውን ቤተ-መጻሕፍት ይበልጥ ለማዘመንና ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። "ይህ ቤተ-መጻሕፍት ብቁ ዜጎችን ለማፍራት ወሳኝ ነው፤ እኔና ቤተሰቤም እንዲሻሻል በጋራ እንሰራለን" ብለዋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

🤲 🤲የድረሱልን ጥሪ 🤲 🤲የገና ስጦታችንን ለእናታችን ለቅድስት ኪዳነ ምሕረት ።ይቺህ ከላይ 👆የምትመለከቷት እ የቦንጋ ደብረ ፍስሀ ቅዱ ስት  ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ነው...
01/01/2026

🤲 🤲የድረሱልን ጥሪ 🤲 🤲
የገና ስጦታችንን ለእናታችን ለቅድስት ኪዳነ ምሕረት ።

ይቺህ ከላይ 👆የምትመለከቷት እ የቦንጋ ደብረ ፍስሀ ቅዱ ስት ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ነው።
በ ከፋ ሀገረ ስብከት በቦንጋ ከተማ የምትገኝው የስዕለት ሰሚዋ የቦንጋ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ናት ምን ይህሎቻችን የኪዳነ ምህረት ውለታ አለብን ታድያ ልጆቼ ስትለን አቤት አለን ልጆችሽ ልንላት ይገባል
ውድ ኦርቶዶክሳውያን፤
ወንድም እህቶቻንን በመላው ዓለም ያላችሁ የእናታችን ቤተመቅደስ ጣሪያው እያፈሰሰ ግርግዳው የፈረሰ ለአገልግሎት በጣም ተቸግረናል ።

ሁላችንም የበረከቱ ተካፋይ እንሁን !

[ 200 ብር ለኪዳነ ምሕረት ]

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደብሩ አካውንት
1000224170126

ቦንጋ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን
ቅድስት ኪዳነ ምህረት አለው ልጆቼ ትበላቹ
እግዚአብሔር ይስጥልን ።

ለበለጠ መረጃ
ለገዳሙ አስተዳዳሪ
+251917824439

20% ቅናሽ የተደረገበት የጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓል የሽያጭ ኤክስፖ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል! *********የጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓል የሽያጭ ኤክስፖ በለገሃር መንደሩ...
01/01/2026

20% ቅናሽ የተደረገበት የጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓል የሽያጭ ኤክስፖ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል!
*********
የጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓል የሽያጭ ኤክስፖ በለገሃር መንደሩ በድምቀት ቀጥሎ እስከ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም. ለደንበኞቹ ክፍት ይሆናል፡፡

በዓሉን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ መንደሮቻችን በቅንጡ አፓርትመንቶችና የንግድ ሱቆች በ5% ቅድመ ክፍያ እስከ 20% ቅናሽ ተደርጎባቸዋል፡፡

እንዳያመልጥዎ!

መኖር በጊፍት መንደር!

ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!

ለበለጠ መረጃ:-
Website: https://www.giftrealestate.com.et
+251984 65 65 65 / +251979 65 65 65

የሽያጭ ዉል-ሕጉ እና አተገባበሩአለምሰገድ አብርሃም-፡- በማናቸዉም ፍርድ ቤት ጠበቃ ና የህግ አማካሪ ስልክ 0910 211365/0931775959/     |  ትርጉም፡-  ሽያጭ እና የሽያጭ ...
31/12/2025

የሽያጭ ዉል-ሕጉ እና አተገባበሩ

አለምሰገድ አብርሃም-፡- በማናቸዉም ፍርድ ቤት ጠበቃ ና የህግ አማካሪ ስልክ 0910 211365/0931775959/

| ትርጉም፡- ሽያጭ እና የሽያጭ ዉል ምንነት

በሀገራችን ሽያች እና የሽያች ዉል በህግ-ተበጅቶ ወደ ተግባር ከመገባቱ 1952 ዓ.ም ቀድሞ የለዉጥ ዉል እንድ ዕቃ በሌላ እቃ የመለወጥ ሂደት (የእንካ በእንካ) ለዘመናት ሲተገበር ኖሯል፡፡ ነገር ግን ይህንን የለዉጥ ዉል በህግ አግባብ ስርዓት ማስያዝ ግቡ በማድረግ የፍታብሄር ህግ በ1952 ዓ.ም ተረቆ በስራ ላይ ዉሏል፡፡

በዚሁ ህግ መሰረት የሽያጭ ዉልን ትርጓሜ ከመመልከታችን አስቀድሞ “ሽያች” ምን ማለት እንደሆነ ከፍ/ህ/ቁጥር 2266 ድንጋጌ አንፃር ስንመለከት “ሽያች ማለት ሻጭ የሆነዉ አንዱ ገዢ ለሆነዉ ሌላ ወገን ዋጋዉ በገንዘብ የተወሰነዉን አንድ ንብረት/ነገር/ ገዢዉ ሊከፍለዉ ግዴታ በገባበት መሰረት ሊያስረክብ ና ባለቤትነቱን ሊያስተላልፍ የሚገደድበት ነዉ::” በሌላ በኩል "የሽያች ዉል” ማለት ደግሞ “ ሁለት እና ከሁለት በላይ የሆኑ ተወዳዳሪ ግንኙነት ያላቸዉ ወገኖች በመካከላቸዉ የሽያጭ ዉል ህግ ሊቀበላቸዉ የሚችሉ ተነፃፃሪ ግዴታዎችን ለመፍጠር ያለመ ስምምነት ባለ ግዜ የሽያጭ ዉል አለ ብሎ ማለት የሚቻል ነዉ” ፡፡ ሰዎች የሽያች ዉልን በሚያደርጉበት ግዜ ዉሉም የፀና ይሆን ዘንድ በፍ/ህ/ቁጥር 1678 መሰረት ተዋዋይ ወገኖች ችሎታ ያላቸዉ መሆን፤ጉድለት የሌለበት ስምምነት ማድረግ፤የዉሉ አይነተኛ ሆነዉ ጉዳይ (ነገር) የሚቻል እና ህጋዊ መሆን እና ህግ የሚፈልገዉ ልዪ ፎርም መኖር የዉል ህግን ለማቋቋም የሚረዱ ናቸዉ፡፡

1/ የሽያች ዉል መፈፀምን ተከትሎ በተዋዋይ ወገኖች የሚኖሩ መብት እና ግዴታዎችን
ሻጭ እና ገዢ እርስ በእርሳቸዉ ነፃ ፈቃድ ላይ ተመስርተዉ የፈጠሩትን ተነፃፃሪ ግዴታ በዉል በማሰራቸዉ ወይም ወደ ዉል ስርዓት በመግባታቸዉ ህግ የሚጥልባቸዉ መብቶች እና ግዴታዎች እንደሚኖር ከሀገራችን የሽያጭ ህግ መረዳት ይቻላል፡፡
በዚህም የገዢዉ መብቶች የሻጭ ግዴታዎች ሆነዉ ሲቆሙ የገዢዉ ግዴታዎች ደግሞ የሻጭ መብቶች ሆነዉ መነሳታቸዉ የመብት ና ግዴታ ፍልስፍና መርህ በመሆኑ በዚሁ አግባብ ወደ ዝርዝር ነጥቦች እንቀጥል፡፡

1.1/ የሻጭ መብቶች እና ግዴታዎች

ሻጭ ንብረቱን ወደ ገዢ በሽያጭ ለማስተላላፍ ወደ ዉል ስርዓት ሲገባ አስቀድሞ መገንዘብ ያለበት በፍ/ህ/ቁጥር 1731 መሰረት ዉል በህግ አግባብ የተቋቋመ እንዲሆን ዉሉን ባቋቋሙት ተዋዋይ ወገኖች ላይ ህግ መሆኑን (ግራ ቀኙን አሳሪ ስምምነት ነዉ ማለት ማላታችን ነዉ) በመረዳት መሆን አለበት፡፡

የሻጭ ግዴታዎች

ሀ/ የተሸጠዉን ንብረት የማስረከብ ግዴታ፤
በፍታብሄር ህጋችን፤ሻጩ በማስረከብ ግዴታ ዉስጥ ስሚያስረክበዉ ነገር፤የማስረከቢያ ግዜ እና የማስረከቢያ ቦታ እና ተያያዥነት ያላቸዉን ግዴታዎች ስንመለከት ንብረትን ማስረከብ ትልቁ የሻጭ ግዴታ መሆኑን የፍ/ህ/ቁጥር 2266 እና 2273 ያስገነዝቡናል፡፡ ንብረትን /ዕቃን/ ማስረከብ የሚገለፅበትን መንገድ ስንመለከት ንብረቱን ወይም እቃዉን ለገዢዉ በመስጠት (Actuall Delevery)፤ ወይም እቃዉን ወይም ንብረቱን የሚወክለዉን ሰነዶች በማስረከብ (By Delivering the documents) የሚከናወን ነዉ፡፡ ከማስረከብ ጋር በተያያዘ በተጨማሪነት ህጉ ተጨማሪ ግዴታ ሊጥል ይችላል ለአብነትም ያህል፤
በንብረቱ/ዕቃዉ/ ርክክብ ወቅት ትብብር የማድረግ ግዴታ ( የፍ/ህ/ቁጥር 2313 እና 1757)
የንብረቱ ገዢ ንብረቱን ለመረከብ በዉሉ በተስማሙበት ቀን፤ቦታ እና ሰዓት ተገኝቶ ንብረቱ ወይም እቃዉን ለመረከብ ፍቃደኛ ባልሆነ ግዜ በፍ/ህ/ቁጥር 2349፤1779 እና 1780 መሰረት ንብረቱን/እቃዉን/ መልሶ ሻጭ መረከብ የሚገባዉ ነዉ፡፡
የማስረከብ ወጪዎች ያሉ እንደሆነ ሻጭ በመርህ ደረጃ ወጪዎችን የመሸፈን ግዴታ ያለበት ስለመሆኑ የፍ/ህ/ቁጥር 2316(1)፡፡

ለ/ ባለሀብትነት/ስመ-ንብረትን/ የማስተላለፍ ግዴታ
ሻጭ ባለሀብትነትን የማስተላለፍ ግዴታዉን ለመወጣት ማስረከብ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ በፍ/ህ/ቁጥር 1186(1) የተመለከተ ሲሆን፤በፍ/ህ/ቁጥር 1186(2) መሰረትም ልዩ ተንቀሳቃሽ የሆኑ (መኪና፤አዉሮፕላን፤መርከብ..ወዘተ) እና የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን ከማስረከብ በሻገር ንብረቶቹን ይዞ መገኘት እና ልዩ ህጎች የሚጠይቋቸዉን ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት የሚገባቸዉ ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ የቤትን ሽያችን በተመለከተ ሽያጩ ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ አካል ፊት መደረግ ያለበት ስለመሆኑ እና በሚመለከተዉ የመንግስት ተቋምም ዉሉ ሊመዘገብ የሚገባ ስለመሆኑ የፍ/ህ/ቁጥር 1723 እና 2878 ያስገነዝቡናል፡፡

ሐ/ በተሸጠ እቃ ወይም ንብረት ላይ ጉድለት የተገኘ እንደሆነ ሻጭ ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ፤

ሌላዉ የሻጭ ግዴታ በተሸጠዉ ንብረት ወይም እቃ ላይ ሊኖር የሚችልን መበላሻት፤ ወይም የንብረቱ በዉሉ ላይ ከሰፈረዉ ጋር አለመጣጣም ሲኖር ሻጭ ኃላፊነት ያለበት ስለመሆኑ እንረዳለን፡፡ በሌላ መልኩ ሻጩ እቃዉን ከማስረከብ እና ባለቤትነትን በማስተላለፍ ብቻ የሚወሰን ግዴታ የሌለበት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ሻጭ ለገዢዉ ዋቢ የመሆን ሀላፊነት የሚኖርበት እንደ ጉድለቱ መጠን ነዉ (የፍ/ህ/ቁጥር 2344(1)፤ 2289)፡፡ ጉድለቱም ከፍተኛ በሆነ ግዜ በግራ ቀኙ መካካል ዉሉን ሊያሰርዝ የሚችል ይሆናል፡፡ በሌላ በኩል የመርሁ ልዩ ሁኔታ ገዢ ዉሉ በተደረገ ግዜ በንብረቱ ላይ ጉድለት ያለበት መሆኑን እያወቀ ዉሉን የፈፀመ እንደሆነ ሻጭ ለጉድለቱ ተጠያቁ የሚሆንበት የሕግ መሰረት የለም (የፍ/ህ/ቁጥር 2295)፡፡

መ/ የሻጭ ተጨማሪ ግዴታ፤

በፍ/ህ/ቁጥር 2301 እና 2302 መሰረት፡- የተሸጠዉን እቃ በተመለከተ አስረጂ ማስረጃዎችን የማስረከብ ግዴታ ያለበት መሆን ናቸዉ፡፡

1.1.2/ የገዢ መብቶች እና ግዴታዎች
ከላይ በዝርዝር እንዳየነዉ የሻጭ ግዴታዎች የገዢ መብቶች ስለመሆናቸዉ ተመልክተናል፡፡ የገዢ ግዴታዎች በዋናነት በዉሉ መሰረት ዋጋን የመክፈል እና የገዛዉን ንብረት ወይም እቃ የመረከብ ናቸዉ ( የፍ/ህ/ቁጥር 2303)፡፡

1.3/ የሻጭ እና የገዢ የጋራ ግዴታዎች
የተዋዋይ ወገኖቹ የጋራ ግዴታዎችን በተመለከተ በፍ/ብ/ህ/ቁጥር 2314-2328 የተመለከተ ሲሆን፡-
የጋራ ወጪዎችን የመሸፈን ግዴታ (የፍ/ህ/ቁጥር 2314-2319)
የተሸጠዉን ንብረት ወይም እቃ የመጠበቅ ግዴታ ( Preservation of the Thing) ( የፍ/ህ/ቁጥር 2320-2322)
ሊደርስ የሚችል አደጋን መኖሩ በተረጋገጠ ግዜ ማስተላለፍ የሚቻልበት አግባብ ያለ ስለመሆኑ (የፍ/ህ/ቁጥር 2323-2328) በሽያች ዉል ግዜ የሚኖሩ የጋራ ግዴታዎች ናቸዉ፡፡

ማጠቃለያ፡-
ህጉ በሚጠይቀዉ አግባብ የሽያች ዉሉን የሚፈፅሙ ተዋዋዮች በመካከላቸዉ የሚመሰርቱት ዉል ህግ መሆኑን (የፍ/ህ/ቁጥር 1731 ልብ ይሉኃል) ይህም መብት እና ግዴታን በመካከላቸዉ የሚፈጥር መሆኑን በመረዳት የዉሉን አይነተኛ የሆነዉ ጉዳይ በእርግጥም ለህግ እና ለሞራል ተቃራኒ አለመሆኑ ጭምር በማረጋገጥ ግብይት መፈፀም የተገባ ነዉ፡፡

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታታህሳስ 22/ 2018Marburg Virus Disease Daily update Ethiopia December 31/ 2025 Ministry of Health,Et...
31/12/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ ሁኔታ
ታህሳስ 22/ 2018

Marburg Virus Disease Daily update
Ethiopia
December 31/ 2025

Ministry of Health,Ethiopia
Ethiopian Public Health Institute

የኃይል መቆራረጥ ማሳሰቢያነገ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም   | ​የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በአካባቢ...
31/12/2025

የኃይል መቆራረጥ ማሳሰቢያ
ነገ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም

| ​የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና በአካባቢዋ በሚገኙ አንዳንድ ስፍራዎች ላይ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።

​⏰ የጊዜ ሰሌዳ እና የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦

​1. ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 ድረስ፦
​ለገሐር አካባቢ፦ ቤተዛታ ሆስፒታል፣ የኦሮሚያ ባሕል ማዕከል ጀርባ፣ ጊዮን ሆቴል፣ በእስጢፋኖስ ድልድይ አካባቢ።
​ሕንጻዎችና ሆቴሎች፦ ኃይለ ዓለም ሕንጻ፣ ገነት ሆቴል፣ አይናለም በዜ ሕንጻ፣ አልሳም ፒኤልሲ።

​ፈረንሳይ እና እንጦጦ፦ ፈረንሳይ ኤምባሲ፣ ወደ ጉራራ፣ ብሎኬት ገበያ፣ ኪዩር ሆስፒታል፣ ራሳ ካሳ ክሊኒክ፣ አቦ ቤ/ክ፣ እንጦጦ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን።

​አቃቂና ሰበታ፦ ሰበታ ከተማ፣ አቀበና ውሃ ማምረቻ፣ ዲማ ሆስፒታል፣ አርባ ምንጭ ጨርቃጨርቅ፣ ኮካኮላ ፋብሪካ፣ ዲማ አካባቢ ያሉ ፋብሪካዎች፣ አቃቂ ቄራ፣ መንህስት ት/ቤት፣ ተኩሼ እንጨት ቤት፣ አቃቂ ጨው ተራ፣ አቃቂ ታክሲ ተራ።

​ሌሎች፦ ቤጂንግ ሆስፒታል፣ ወረዳ-1፣ አበበ ጎንፋ ሰፈር፣ ብሩህ ተስፋ ት/ቤት፣ ተፍኪ እና ተጂ።

​2. ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 9:30 ድረስ፦
​ገላን አካባቢ፦ ገላን ማዘጋጃ ቤት፣ ገላን ከተማ፣ ፒኤልሲ፣ ነጮ፣ ኖክ ማደያ እና አካባቢው።

​📢 መልዕክት፦ በእነዚህ አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ ተቋሙ በትህትና ጠይቋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታን እንደምትወልድ ብስራቱን የነገረበት ቀን 🙏በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት ታህሳስ 22 ቀን ብስራተ ገብርኤል ይባላል፡፡ይህም ቅዱስ ገብርኤል ለእመ...
31/12/2025

ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታን እንደምትወልድ ብስራቱን የነገረበት ቀን 🙏

በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት ታህሳስ 22 ቀን ብስራተ ገብርኤል ይባላል፡፡

ይህም ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታን እንደምትወልድ ብስራቱን የነገረበት ቀን ነው፡፡ እንዴት ብስራቱንማ የነገራት መጋቢት 29 ቀን ካሉ ትክክል ነው፡፡ ብስራቱን የነገራት መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሁድ ከቀኑ ሦስት ሰዓት ላይ ነው፡፡ ዛሬ የሚከበርበት ምክንያት ወርሃ መጋቢት ታላቁ ዓቢይ ጾም የሚውልበት ወር በመሆኑ ነው፡፡

በፍትሐ ነገስት አንድምታ አንቀጽ 15 እንደሰፈረው በዚህ በዓቢይ ጾም ደግሞ ሐዘን፤ ለቅሶ፤ ጾም፤ ጸሎት እንጂ ደስታ፤ እልልታ፤ ጭብጨባ የለም ፍጹም የሐዘን ወራት ነውና ታቦት አውጥቶ በዓል ማክበርም ስህተት ነው፡፡ ታዲያ ቅዱሳን አባቶቻችን እንደዚህ ዓይነት ስርዓት ሰሩ፡፡ የመጋቢት 27 ስቅለቱን ጥቅምት 27 ቀን እንዲሁም የመጋቢት 5 አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍት ቀን ወደ ጥቅምት 5 ቀን ዞሮ እንዲከበር አደረጉ፡፡

የመጋቢት 29 ቀን ብስራቱ ታህሳስ 22 ቀን ዞሮ እንዲከበር ያደረገው ታላቁ አባት የጥልጥልያ ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ደቅስዮስ ነው፡፡ በእመቤታች ፍቅር ልቡ የነደደው ይሕ ታላቅ ጻድቅ ነው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ተአምራት ከተለያዩ መጻሕፍት ሰብስቦ በአንድ ላይ የጻፈ አባት ነው፡፡ የምእመናን ክብር የምትሆን አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንም በእጅዋ መጽሐፍ ይዛ ተገለጸችለት።

ወዳጄ ደቅስዮስ ሆይ ባንተ ደስ አለኝ ይህንን መጽሐፍ ስለጻፍክለኝ አመሰግንሁ ብላው ተሠወረች። ደቅስዮስም ይህን ራእይ ባየ ጊዜ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንን ከመውደዱ የተነሣ ፈጽሞ ደስ አለው፣ ፍቅሯም ይበልጥ በልቡ ውስጥ እንደ እሳት ነደደ። ለክብሯም መገለጫም እንደሚያደርግ ያስብ ጀመር።

ቅዱስ ደቅስዮስ ኤጲስ ቆጶስነት በተሾመበት ዘመን ታህሳስ በባተ በ22ኛው ቀን ቅዱስ ገብርኤል ባበሰራት ቀን በዓሏን አከበረ። በበዓሉ የተገኙ ሰዎችም ሁሉ ደስ አላቸው፡፡ ይህ በዓል አሁንም ይከበራል፡፡ ደግነትን ምሕረትን ቸርነትን የምትወድ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችንም በእጅዋ የከበረ ልብስ ይዛ ተገለጸችለት።

በእውነት አገልጋዬ ወዳጄ ደቅስዩስ ሆይ እኔ አመሰገንኩህ ባንተም ደስ አለኝ ሥራህንም ወደድሁ፡፡ በእኔ ደስ እንዳለህ ያበሰረኝ ገብርኤል የሚባል መልአክ ባበሰረበት ቀን በዓሌን አክብረሃልና ስለኔም ሰውን ሁሉ ደስ አሰኝተኽኛልና። እኔም ዋጋህን ልሰጥህ፣ አንተ በዚህ ዓለም በሰው ሁሉ ፊት እንዳከበርከኝ አከብርህ ዘንድ እወዳለሁ። ይህን የከበረ ልብስና ይህንን ወንበርም አመጣሁልህ። የዚህ ታላቅ አባት እረፍቱ ታህሳስ 22 ነው፡፡

ከእርሱ በኃላ ሌላ ኤጲስ ቆጶስ ተሾመ ልብሱን እለብሳለው በወንበሩም እቀመጣለው አለ ተው ይቅርብህ እመቤታችን እንዲህ ብላ ተናግራለች ይሉታል እርሱም ሰው እኔም ሰው እርሱም ኤጲስ ቆጶስ እኔም ኤጲስ ቆጶስ ብሎ በትዕቢት ልብሱን ለበሰው በወንበሩም ተቀመጠ ክፉኛ አወዳደቅ ወደቀ ሞተም ይህን ያዩ እመቤታችንን በጣም ፈሯት ይላል ተአምረ ማርያምን ላይ፡፡

ደቅስዮስ ሰርቶልን ያለፈውን ስርዓት ቤተክርስቲያን ተቀብላ ይኸው ዛሬም ድረስ ታከብረዋለች፡፡ የእመቤታችን ፍቅር የበዛላቸው ገዳማውያንም በዓሏን በደስታ ያከብሩታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፤ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

Address

Gabon Avenue (Washington DC Square/Sterling Buildg)
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን):

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

GETU TEMESGEN - (ጌጡ ተመስገን)

ጌጡ ተመስገን ውልደቱና እድገቱ አዲስ አበባ ነው። በጋዜጠኝነት ሙያው፤ ለአገር እና ለሕዝብ በሠራቸው አይረሴ ሥራዎቹ በርካታ ሽልማቶችን አግኝቷል። የፈረንሳይ ቴሌቪዥን ባሰባሰበው የተመልካቾች ምዘና መሠረት ‹‹ባለንሥሩ ጋዜጠኛ ~ A Journalist with an eagle eye›› የሚል ስያሜ አግኝቷል።

Getu Temesgen was born and raised in Addis Ababa. As a result of his unforgettable journalistic works/TV productions, he has won various recognitions. He was named “The Journalist with an eagle eye” in an audience poll conducted by French TV.

ሦስት ሥራዎቹም በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ቀርበውለታል። በአዘጋጁቹ ግብዣ አውሮፓ ፤ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ፈረንሳይና ቤልጅየም ተጉዞ፤ ትምህርታዊ ጉብኝት በማድረግ አገር ቤት ተመልሷል።

His three TV productions were also presented for European audience in French language and as a result was invited by the producers to visit France, Germany, Italy and Belgium.”