02/01/2026
በኢትዮጵያ የክትባት አስተዳደርን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሀገር አቀፍ ጥናት ተጀመረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀገሪቱን የቀጥታ የክትባት ስርጭት 63% እና የጤና ፕሮግራሞች የቀጥታ ስርጭት 75% እንደሚያሰራጭ ይታወቃል ፤ በመሆኑም የተቀናጀ ውጤታማ የክትባት አስተዳደር ፣ የክትባት ብክለት ቁጥጥር እና የሙቀት መጠን ክትትል ጥናት በኢትዮጵያ ለመስራት የማስጀመሪያ ስነስርዓት በአገልግሎቱ ግቢ ተካሂዷል ።
ኢትዮጵያ ለበርካታ አመታት መከላከል ላይ ያተኮረ የጤና ፖሊሲ ይዛ እየሰራች እንደምትገኝ በዚህም ጠንካራ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ያነሱት በጤና ሚኒስቴር የክትባት አገልግሎት ሀላፊ አቶ መልካሙ አያሌው ፤ በዚህም የጤና ፖሊሲውን ከሚያስቀጥሉት ተግባራት መካከል የምንሰጠው ክትባት ጥራቱን ጠብቆ እየተሰራጨ እንደሚገኝ መከታተል ሲሆን ይህንንም በዚህ ጥናት ለማረጋገጥ ያግዘናል ብለዋል ።
ለጥናቱ በዋነኝነት ከ GAVI
ለጋሽ ድርጅት ድጋፉ መገኘቱን አቶ መልካሙ ተናግረው ሌሎች አጋር ድርጅቶ አስተባብሮ ወደ ተግባር በመግባቱን Oxford Policy Management _OPN ን አመስግነዋል ።
ይህንን ጥናት ከማንም ተፅዕኖ ነፃ ሆናችሁ መስራት ይገባል ብለው ያሳሰቡት ሀላፊው ፤ ጥናቱ የተሳካ እንዲሆን የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናደርጋለን ብለዋል ።
የአገልግሎቱ የ78 አመታት ተቋሚዊ ጉዞ እና ስትራቴጂክ እቅድ የአገልግሎቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ያቀረቡ ሲሆን ፤ ጥናቱ በ2030 እንደ ተቋም የያዝነውን ግብ ለማሳካት ፣ አሁን ምን ላይ እንደደረስንና ማስተካከል ያሉብንን ጉዳዮች በጉልህ እንደሚያሳየን ትልቅ ተስፋ ይጣልበታል ሲሉ አቶ ሰለሞን ገልፀዋል ።
በዚህ ጥናት የሚሰራው አዲስ ነገር ምን ምን እንደሆነ ፣ ጥናቱ የሚዘጋጅበትን ዝርዝር ፣ መረጃ ለሚሰበስቡ አካላት ስልጠና መሰጠቱን እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን የስራ ሂደት አማካሪ እና ጥናት አስተባባሪ አቶ ወንድወሰን በዝርዝር አቅርበው ፤ ጥናቱ የቅርብ ጊዜ መረጃ እንዲኖር እንደሚያደርግና WHO በሚጠይቀው መሰረት ሪፖርተር ማዘጋጀት እንደሚያስችል አስረድተዋል ።
# ማገልገል ክብር ነዉ!
ዘጋቢ ማኅሌት አበራ