Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ፣ የነፃነት ተምሳሌት እና የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ማህተም ነው!ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻ...
01/03/2026

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ፣ የነፃነት ተምሳሌት እና የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ማህተም ነው!

ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን በደማቸውና በአጥንታቸው የፃፉት ታሪክ ዛሬም ድረስ በፅናት እንድንቆም ብርታት ይሆነናል።

እኛም በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት፣ ይህንን የአባቶቻችንን የድል አድራጊነት መንፈስ በመውረስ፣ የሕዝባችንን ጤና ለመጠበቅና ጥራት ያለው መድኃኒት በየደረጃው ለሚገኝ የጤና ተቋም በተመጣጣኝ ዋጋ ለማድረስ የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን።

የአድዋ ድል የሁላችንም ኩራት ነው!


የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለትን ለማዘመን እና ለአስተማማኝ የመድኃኒት የመገኘት ምጣኔ ገንቢ አስተዋፅኦ ያለው የጥናት ውጤት ለውይይት ቀረበ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የመድኃኒት እና...
28/02/2026

የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለትን ለማዘመን እና ለአስተማማኝ የመድኃኒት የመገኘት ምጣኔ ገንቢ አስተዋፅኦ ያለው የጥናት ውጤት ለውይይት ቀረበ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የመድኃኒት እና የህክምና ግብዓቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ፣ በበቂ መጠንና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማቅረብ የተካሄዱ የገበያ ጥናት (Market Shaping) ውጤቶች ላይ የሚወያይ ወርክሾፕ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄደ።

በወርክሾፑ ላይ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሂወት አበበ፣ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ፣ የጌትስ ፋውንዴሽን ተጠሪ ዶ/ር ቃልኪዳን ላቀው፣ የክልል ጤና ቢሮ ተወካዮች፣ አጋር ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ፍሬሂወት አበበ ባስተላለፉት መልእክት፣ በጥናቱ የተለዩ ግኝቶች በሚቀጥሉት 3 ዓመታት እቅድ ውስጥ ተካተው ተግባራዊ እንደሚሆኑ ገልጸው፣ የመረጃ ግልጽነትን በማረጋገጥ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን በማዘመን በኩል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

እንዲሁም የመድኃኒት የዋጋ መረጋጋትንና የግብዓት እጥረትን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራዊ እርምጃዎች ከውይይቱ እንደሚጠበቁ ተጠቁሟል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ በበኩላቸው፣ አገልግሎቱ የተረጋጋ የገበያ ስርዓት በመፍጠር ያልተቆራረጠ አቅርቦት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አስታውሰዋል።

በጥናቱ አቅራቢዎችም በዋጋ አወጣጥ፣ በአቅርቦት መረጋጋት፣ በጥራት እና በፍላጎት ትንበያ ስርዓት ላይ ያሉ ክፍተቶችና እድሎች ተብራርተዋል።


የጥናቶቹን ውጤቶች በውይይት ከዳበሩ በሗላ የመድኃት አቅርቦት ሰንሠለቱን አስተማማኝ ለማድረግ ግኝቶቹን እንጠቀምባቸዋለን ብለዋል።

በጥናቱ በመድኃኒት አቅርቦት ሠንሠለቱ ከላይ እስከ ታች ያሉ ክፍተቶች የተለዩ ሲሆን እነዚህን እጥረቶች ለመሙላት የሚረዱ ሳይንሳዊ መፍትሄዎችን አካቷል።

ተሳታፊዎች በጥናቱ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ በጋራ በተደረገው የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ድጋፍ Result for Development (R4D) ኢትዮጵያ አስተዋፅኦ ማድረጉ ተገልጿል።

#ማገልገል ክብር ነው!

አማኑኤል ወርቃየሁ

28/02/2026
የኩህኔ ፋውንዴሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትን ጎበኙ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በሕክምና ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ በርካታ ስራዎችን እያከ...
24/02/2026

የኩህኔ ፋውንዴሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትን ጎበኙ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በሕክምና ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኘው የኩህኔ ፋውንዴሽን (Kuehne Foundation) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶ/ር ኒክላስ ዊልምኪንግ፣ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ፤ ስለ ተቋሙ አወቃቀር፣ ስለ ኢትዮጵያ የጤና መረጃ ፍሰት እና ስለ አቅርቦት ሰንሰለቱ ከጫፍ እስከ ጫፍ (End-to-End) ሂደት ለጎብኚዎቹ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል። በተለይም ተቋሙ ተግባራዊ ያደረገው የተቀናጀ የዲጂታላይዜሽን ስርዓት በአሰራር ላይ ያመጣውን መሠረታዊ ለውጥ በዝርዝር አስረድተዋል።

የኩህኔ ፋውንዴሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶ/ር ኒክላስ ዊልምኪንግ በበኩላቸው፣ አገልግሎቱ ያለውን ተቋማዊ አቋምና ዘመናዊ አሰራር አድንቀው፤ በቀጣይም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችን ለይተው ትብብራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የፋውንዴሽኑ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተፈሪ ገንድፍ እንደገለጹት፤ ድርጅታቸው በ2026 በኢትዮጵያ የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ለመስራት ያቀዳቸው በርካታ ተግባራት አሉ። ይህ ጉብኝትም በቀጣይ በሚደረጉ ድጋፎች ዙሪያ ከበላይ ኃላፊዎች ጋር ለመወያየት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።

የልዑካን ቡድኑ በመጨረሻም የተቋሙን የመድኃኒት መጋዘኖች በአካል ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

!
ዘጋቢ፦ ማኅሌት አበራ

የሀገር ውስጥ አምራቾች ውል አፈፃፀማቸውን ሊያሻሽሉ ይገባል፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን ለማበረታት አዲሱን የ...
24/02/2026

የሀገር ውስጥ አምራቾች ውል አፈፃፀማቸውን ሊያሻሽሉ ይገባል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን ለማበረታት አዲሱን የግዥ መመሪያ መሰረት በማድረግ እስከ 7ዓመት የሚቆይ ውል በመፈፀም ዋስትና ያለው ገበያ እየፈጠረ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።

በዚህም የሀገር ውስጥ ምርት በተያዘው በጀት ዓመት 42% ማድረስ እንደተቻለ የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው ካውዛ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ አምራቾች ውል አፈፃፀማቸው የተወሰነ ክፍተት መኖሩን አንስተው ለአቅርቦት ሰንሰለቱ መሳለጥ ጊዜውን የጠበቀ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

አክለውም አምራቾች ውል በገቡት መሰረት ለአገልግሎቱ የህክምና ግብአቶችን በማቅረብ አጋርነታቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉ አቶ አቅናው መልዕክት አስተላልፈዋል።

#ማገልገል ክብር ነው!
ሰላም ይደግ

የተቀናጀ የአቅርቦት ዕቅድ ክለሳ መስራት አቅርቦትን ከፍላጎት ጋር ለማጣጣም ትልቅ ሚና አለዉ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የአትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ...
23/02/2026

የተቀናጀ የአቅርቦት ዕቅድ ክለሳ መስራት አቅርቦትን ከፍላጎት ጋር ለማጣጣም ትልቅ ሚና አለዉ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የአትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲያከናዉን የቆየዉን የ2018 ዓ.ም የ2ተኛ ሩብ አመት የጤና ፕሮግራም ፣ የተገላባጭ ፈንድ እና የክትባት ግብአቶችን የአቅርቦት እቅድ ክለሳ አዉደ ጥናት አጠናቋል፡፡

በአዉደ ጥናቱ ባለፉት 3 ወራት አቅርቦት ከፍላጎት ጋር የተጣጣመ ስለመሆኑ ፤ የህክምና ግብአቶች ቀደም ሲል በተተነበየላቸዉ ፍጆታ መጠን መሰረት ጥቅም ላይ መዋላቸዉን በመገምገም የክምችት ስጋት ላይ የሚገኙ መድኃኒቶች ተለይተዉ የመፍትሄ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

አቅርቦትን ከፍላጎት ጋር ለማመጣጠን በየሩብ አመቱ የእቅድ ክለሳ ማከናወን ትልቅ ሚና ይጫዎታል ሲሉ የአገልግሎቱ የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች ፍላጎት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ አበበ ተናግረዉ ፤ ብክነት እና የአቅርቦት መቆራረጥ እንዳይከሰት አስተዋጽኦ አለዉ ብለዋል፡፡

በቀጣይ ይህን የተቀናጀ የአቅርቦት ዕቅድ ክለሳ ለማጠናከር የሚያስችል ደረጃዉን የጠበቀ የዲጅታል ስርአት ለመዘርጋት ዘርፈ ብዙ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አቶ ወርቅነህ ጠቁመዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ!
ሰላም ይደግ

የሀዘን መግለጫ
21/02/2026

የሀዘን መግለጫ

Our respected customers
21/02/2026

Our respected customers

ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ አገልግሎት፤ በደሴ መድኃኒት አቅራቢ ቅርንጫፍ የሕፃናት ማቆያ ተመረቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የደሴ ቅርንጫፍ፣ የሠራተኞችን የሥራ...
20/02/2026

ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ አገልግሎት፤ በደሴ መድኃኒት አቅራቢ ቅርንጫፍ የሕፃናት ማቆያ ተመረቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የደሴ ቅርንጫፍ፣ የሠራተኞችን የሥራ ጫና ለመቀነስና ቀልጣፋ አገልግሎትን ለማረጋገጥ ያስገነባውን የሕፃናት ማቆያ ክፍል በዛሬው ዕለት በድምቀት አስመርቋል።

የማቆያው መገንባት ዋና ጥቅሞች፦
✅ እናቶች/ወላጆች ልጆቻቸውን በሥራ ቦታቸው አጠገብ ሆነው እንዲንከባከቡ ዕድል ይሰጣል።
✅ በሠራተኞች ላይ የሚፈጠርን የጭንቀት ጫና በመቀነስ የሥራ ተነሳሽነትን ይጨምራል።
✅ የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነት ያሻሽላል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው እንደገለጹት፣ መሥሪያ ቤቱ ለሕፃናት ማቆያ ክፍሉ የሚያስፈልጉ ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለማሟላት ድጋፉን ይቀጥላል።

የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምጸሐይ ዴታ በበኩላቸው፣ እንዲህ ዓይነት አሠራሮች የሴቶችን ጫና ለመቀነስ ያላቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አሳስበዋል።

ይህን ያውቁ ኖሯል?

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ካሉት 19 ቅርንጫፎች ውስጥ እስካሁን በደሴን ጨምሮ በ11ዱ ቅርንጫፎች የሕፃናት ማቆያ ገንብቶ አገልግሎት ላይ አውሏል።

#ማገልገል ክብር ነው!

ሰብአዊነት በሥራ ላይ፦ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለሰማዕት ሠራተኛው ቤተሰብ ቤት አስረከበ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክ...
20/02/2026

ሰብአዊነት በሥራ ላይ፦ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለሰማዕት ሠራተኛው ቤተሰብ ቤት አስረከበ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው እንደገለጹት፤ ተቋሙ ለጤና ተቋማት መድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶችን ከማቅረብ በተጨማሪ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በዚሁ መሠረት በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በሥራ ገበታቸው ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ላጡት የደሴ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ አቶ ቻለው ሸዋንግዛው፣ ተቋሙ የመኖሪያ ቤት ግንባታ በማከናወን ለቤተሰቦቻቸው አስረክቧል።

የተደረጉ ዋና ዋና ድጋፎች፦

#የመኖሪያ ቤት ስጦታ፦ የሟች ቤተሰቦች ከኪራይ ቤት ወጥተው የራሳቸው ቋሚ መጠለያ እንዲኖራቸው ተደርጓል ።

#የሥራ ዕድል ፈጠራ፦ የሟች ቤተሰቦች እንደ የትምህርት ደረጃቸውና እንደ ሙያቸው በተቋሙ ውስጥ የሥራ ዕድል እንደሚመቻችላቸው ቃል ተገብቷል ።
#ቀጣይነት ያለው ክትትል፦ ተቋሙ ለቤተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ተረጋግጧል።

አቶ ታሪኩ በላቸው አክለውም፣ ተቋሙ ለሠራተኞቹ የሚያደርገውን መሰል ድጋፎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በመኖሪያ ቤት ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የወረዳውና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ ዳይሬክተሮችና ሠራተኞች በተገኙበት ቤቱ ለወይዘሮ መሬማ ሀሰን ተረክቧል።
#ማገልገል ክብር ነው!

የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሳለጥ ያለመ የተቀናጀ የህክምና ግብአቶች አቅርቦት የእቅድ ክለሳ ወርክሾፕ በአዳማ እየተካሄደ ነው፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ...
19/02/2026

የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሳለጥ ያለመ የተቀናጀ የህክምና ግብአቶች አቅርቦት የእቅድ ክለሳ ወርክሾፕ በአዳማ እየተካሄደ ነው

፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት፣ ከየካቲት 12–14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የ2ኛ ሩብ ዓመት የተቀናጀ የአቅርቦት እቅድ ክለሳ ወርክሾፕ በአዳማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

ወርክሾፑ አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በየሩብ ዓመቱ የተተነተኑ ሳይንሳዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ሲሆን፣ የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች አቅርቦት በቀጣይነት እንዲረጋገጥ የሚያግዝ ነው።

አዲሱ አሰራር ቀደም ሲል የነበሩትን የፕሮግራም፣ የተገላባጭ ፈንድ መደበኛ መድኃኒቶችንና የክትባት መድኃኒቶችን ለየብቻ የማቀድና የማሰራጨት ልምድን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው። ሁሉንም የህክምና ግብዓቶች በአንድ አቀናጅቶ በመምራትም ወጪን፣ ጊዜንና ሀብትን በአግባቡ መጠቀም ያስችላል።

የአገልግሎቱ የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች ፍላጎት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ አበበ እንደገለጹት፤ ከመድረኩ ክፍተቶችን በመለየትና በማጥራት የአቅርቦት ስርዓቱን የሚያሳልጥ ውጤት ይጠበቃል። በተጨማሪም በጤና ተቋማት ውስጥ የመድኃኒት እጥረት እንዳይኖር ወርክሾፑ ትልቅ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።

በወርክሾፑ ላይ ከአገልግሎቱ፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከአጋር ድርጅቶች የተውጣጡና በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ ከፍተኛ ሚና ያላቸው ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።



አማኑኤል ወርቃየሁ

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram