Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

የመጋዘኖች ወለል ደረጃዉን የጠበቀ ለማድረግ የጥገና ስራ እየተከናወነ ይገኛል፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ደረጃዉን በጠበቀ መጋዘን እንዲቀመጡ ለማስቻል በ...
03/12/2025

የመጋዘኖች ወለል ደረጃዉን የጠበቀ ለማድረግ የጥገና ስራ እየተከናወነ ይገኛል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ደረጃዉን በጠበቀ መጋዘን እንዲቀመጡ ለማስቻል በዋና መጋዘን 6 እና 7 እንዲሁም በነገሌ ቦረና ቅርንጫፍ የኢፖክሲ ወለል ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የመጋዘን እና የፍሰት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ጀማል ተናግረዋል፡፡

ደረጃዉን የጠበቀ ወለል የህክምና ግብአቶችን ከአቧራ እና ከእርጥበት ለመከላከል ፣ ምቹ የስራ ቦታ ለመፍጠር እንዲሁም የቀን ተቀን ስራ ፍሰት ቀልጣፋ እንዲሆን ለማስቻል እንደሚያግዝ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ ኢፖክሲ ወለል የሌላቸዉ መጋዘኖች ተለይተዉ የጥገና ስራዉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዉ ፤ ስራዉ በለጋሽ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ እንደሚከናወን አቶ መሀመድ ጠቁመዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ!
ሰላም ይደግ

03/12/2025
የሐዘን መግለጫ፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ  የመድኃኒት  አቅራቢ አገልግሎት  የሐዋሳ  ቅርንጫፍ  ከፍተኛ  የቅዝቃዜ ሰንሰለት  ባለሙያ  በሆኑት  አቶ እሸቱ  የሱፍ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን  ...
02/12/2025

የሐዘን መግለጫ
፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሐዋሳ ቅርንጫፍ ከፍተኛ የቅዝቃዜ ሰንሰለት ባለሙያ በሆኑት አቶ እሸቱ የሱፍ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን በተቋማችን ስም እየገለፅን ለመላው ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ ለመላው የተቋማችን ማህበረሰብ መጽናናትን እንመኛለን ።

አቶ እሼቱ የሱፍ ከሐገር ውጪና ሐገር ውስጥ በወሰዷቸው የ Cold Chain equipments installation and Maintainace ስልጠናዎችና ባካበቱት የዳበረ ልምድ ለህፃናትና እናቶች የሚሰጡት ክትባቶች ደህንነትና ፈዋሽነት እንዲጠበቅ ወሳኝ የሆነው የተቋማችን የቅዝቃዜ ሰንሰለት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ጉልህ ሚና የተጫወቱ ከፍተኛ ባለሙያ/Senior expert/ ነበሩ።

አገልግሎቱ በ12ኛው የኢትዮጵያ  #የጥራት ሽልማት ላይ በመወዳደር  ሦሰተኛ ደረጃ የልህቀት ዋንጫ ተሸላሚ ሆነ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በታላቁ ቤተ መን...
01/12/2025

አገልግሎቱ በ12ኛው የኢትዮጵያ #የጥራት ሽልማት ላይ በመወዳደር ሦሰተኛ ደረጃ የልህቀት ዋንጫ ተሸላሚ ሆነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በታላቁ ቤተ መንግሥት በተከናወነው 12ኛው የኢትዮጵያ የጥራት ሽልማት ላይ 3ኛ ደረጃ የልህቀት ዋንጫ ተሸላሚ በመሆኑ ለቀጣዩ ወድድር የላቀ መነሳሳትን የፈጠረ ሰንቅ ሆኗል።

ይህ ታላቅ ዕውቅና የአገልግሎቱ የላቀ የሥራ አፈጻጸም በማስመዝገብ፣ ለአገልሎት ጥራት ያለንን ፅኑ እምነት አና ቁርጠኝነት እንዲሁም የሠነቅነውን የጋራ ራዕይ ትክክለኝነት የሚያሳይ ነው ሲሉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃደር ተናግረዋል ።

"ሁላችንም እንኳን ደስ አለን። ይህ ስኬት የጋራ ትጋታችን፣ ቁርጠኝነታችንና ለልህቀት ያለን እምነት ግልጽ መገለጫ ነው።

ይህ ምዕራፍ በአገልግሎቱ ውስጥ የምትሰሩ እያንዳንዱ ሰው ያላችሁን ተሰጥኦ እና ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው።

ሁላችሁም መልካም ሰርታችኋል! ለስኬታችን ድጋሚ ደስታዬን መግለጽ እወዳለሁ።

ይህ ውጤት የተጠራቀመ ጥረት እና የመናበብ ውጤት ነው።" ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ

የሽልማቱ ስኬት
በዳይሬክተሮች ና በሥራ አስኪያጆች ከፍተኛ አድናቆትን አግኝቷል።

ሽልማቱን አስመልክተው የስራ ሀላፊዎቹ "ይህ ለሁላችንም ታላቅ ምዕራፍ ነው። ለዶክተር ዓብዱልቃድር ገልገሎ እና የአመራር ቡድናቸው ለየት ያለ ስራ ስራችሁ ስላሳያችሁን እንኳን ደስ አላችሁ።
በሁላችሁም እኮራለን! ለዋናው መ/ቤት ሰራተኞችም እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን! ትጋታችሁና ቁርጠኝነታችሁ በእውነት የሚደነቅ ነው፣ እናም እጅግ በጣም እንኮራባችኋለን።
" በማለት በማህበራዊ ሚድያ የትስስር ገፆች ላይ መልካም ምኞታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ ።

ይህ ሽልማት ከተቋቋመበት ዋና ዓላማ አንፃር ሲታይ፣ "ደህንነታቸው፣ ፈዋሽነታቸው የተረጋገጠ መሠረታዊ መድኃኒቶችን ቀጣይነት ባለው እና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ለተያዝነው ጉዞ እምርታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚረዳ ስንቅ ነው" ተብሎ ታምኖበታል።

በተጨማሪም፣ ሽልማቱ በቅርቡ የህዝቡን የመድኃኒት አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ ከጤና ተቋማት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓትን(CDSS) በላቀ ውጤት ለመፈፀም ከምንጊዜም በላይ የሚያነሳሳን ነው።

#ማገልገል ክብር ነው!!

30/11/2025

አገልግሎቱ በ12ኛው የኢትዮጵያ የጥራት ሽልማት የላቀ ስኬት በማስመዝገብ ዳግም የጥራት ሻምፒዮን ሆኗል።

#እንኳን ደስ ያለን!

#ማገልገል ክብር ነው!!

ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት(CDSS) የአቅርቦት ሰንሰለት ምሰሶ ነዉ፨፨፨፨፨፨፨፨የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ እንዳሉት የተጀመረዉን ሀገራዊ ማክሮ ኢኮኖሚክ ሪፎርም ...
30/11/2025

ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት(CDSS) የአቅርቦት ሰንሰለት ምሰሶ ነዉ
፨፨፨፨፨፨፨፨
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ እንዳሉት የተጀመረዉን ሀገራዊ ማክሮ ኢኮኖሚክ ሪፎርም ተከትሎ አገልግሎቱ በርካታ አመርቂ ክንዉኖችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት ወደ ስራ መግባቱ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዉ በኢ.መ.አ.አ በኩል በሩብ አመቱ ግምገማ አገልግሎቱ የአቅርቦት አቅሙን ማሳደግና ለጤና ተቋማት የቅድመ ዋጋ ጥቆማ መስጠት እንዳለበት ፤ የተራዘመ የግዥ ሂደትን ለማሳጠር ርብርብ መደረግ እንደሚገባ ፤ የተገባዉ ዉል በአግባቡ መፈፀም እንደሚኖርበት ገልፀዋል።

ጤና ተቋማት በበኩላቸዉ የማህበረሰብ እርካታ ላይ መስራት እንዳለባቸዉ ያሳሰቡት ሚኒስትር ድኤታዋ በብድር የሚገዙ ግብዓቶች በጊዜ ክፍያቸዉ መፈፀም እንዳለበትም ተናግረዋል።

የጤና ተቋማት ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርአትን(CDSS) ተግባራዊ ለማድረግ እያሳዩት ያለዉ ምላሽ እንደ ጅማሮ ጥሩ እንደሆነ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ የአንደኛ ሩብ አመት ዉል የተገባለት የህክምና ግብዓት አቅርቦት ስርዓት አፈፃፀም ግምገማ ላይ የገለፁ ሲሆን ፤ የመረጃ ግልፀኝነት ስርዓት ከጊዜ ወደ ጊዜ በማሻሻል የህክምና ግብዓት የግዥ ሂደትን ማሳጠር መቻልና የመድኃኒት መገኘት ምጣኔን ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

ለ3 ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት(CDSS) የ1ኛ ሩብ አመት የግምገማ መድረክ የተጠናቀቀ ሲሆን የጤና ተቋማት ተወካዬች እንዳሉት የዉይይት መድረኩ የግብዓት ስርጭት ተግዳሮቶችን ለመፍታት ወሳኝ እንደሆነ አስታዉሰዉ መድኃኒት የመገኘት ምጣኔ አቅምን ከፍ ለማድረግና ተገልጋዩን ክፍል በበቂ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን ሀላፊነት መወጣት እንዳለበት ገልፀዋል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

28/11/2025
የግሎባል ፈንድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰንበአገልግሎቱ ጉብኝት አደረጉ።፨፨፨፨፨፨፨፨የግሎባል ፈንድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እና ዶ/ር ጆርጅ ሳክቫርሊዴዝ ...
28/11/2025

የግሎባል ፈንድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን
በአገልግሎቱ ጉብኝት አደረጉ።
፨፨፨፨፨፨፨፨

የግሎባል ፈንድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እና ዶ/ር ጆርጅ ሳክቫርሊዴዝ አገልግሎቱ እያከናወነ ያለዉን አመርቂ ስራ የጎበኙ ሲሆን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ እንዳሉት በተደረገዉ ተቋማዊ ሪፎርም ዘመናዊ የመረጃ ስርዓት መፍጠር እንደተቻለ ገልፀዋል።

አገልግሎቱ አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት (ERP) ተግባራዊ ከማድረግ ባለፈ በተሻለ ደረጃ ተቋማዊ ራዕዩን ማሳካት የሚያስችለዉን የመድኃኒት ፈንድ አዋጅ 1354/2017 ዓ.ም ማፀደቅና ልዩ የግዥ መመሪያ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉ የአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ ያለዉ አዎንታዊ ሚና የላቀ እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ አስታዉሰዋል።

ERP በመተግበሩ የአገልግሎቱ የማኔጅመንት አባላት ስራዎችን በተሻለ መልኩ መገምገምና ዉሳኔ ማስተላለፍ እንዲችሉ ከማድረግ ባለፈ ዲፓርትመንቶች ቅንጅታዊ አሰራርን ማዳበር እንዲችሉ እንደረዳቸዉ ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል ።

በተጨማሪም አገልግሎቱን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን የባርኮዲንግ አሰራር እንደሚተገበር ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ የቀጥታ ስርጭት ሂደት እየተፈጠረ እንደሆነ ፤ የመጋዘን አያያዝና አስተዳደር ሂደቱም እየተሻሻለ መምጣቱን ዋና ዳይሬክተሩ ለግሎባል ፈንድ ከፍተኛ ሀላፊዎች አመላክተዋል።

የግሎባል ፈንድ ከፍተኛ ሃላፊዎች አገልግሎቱ በ7 አመታት ዉስጥ እያሰራጨ ያለዉን የፕሮግራም መድኃኒቶች የመረጃ ግልፀኝነት በማጤን ያደነቁ ሲሆን ፤ አገልግሎቱ የቀጥታ ስርጭት አቅሙን በማሳደግ በመላዉ ሀገሪቱ በስፋት ተደራሽ መሆኑ አበረታች እንደሆነ ተናግረዋል።

በተያያዘም ከፍተኛ ሀላፊዎቹ በዋና መስሪያ ቤቱ የሚገኙ መጋዘኖች ላይ የተሰሩ የማሻሻያ ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን የመረጃ ግልፀኝነትን ለማምጣት ተቋሙ ያስመዘገበዉን እመርታ በመደገፍ በቀጣይም በቅርበት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት  የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም እየተገመገመ ይገኛል ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የጤና ሚንስትር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፣ የአገልግሎቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር ...
27/11/2025

ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም እየተገመገመ ይገኛል

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የጤና ሚንስትር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፣ የአገልግሎቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው ካውዛ፣የክልል ጤና ቢሮ አመራሮች፣የጤና ሚንስቴር ከፍተኛ ኤክስፐርቶች ፣ የፌደራል ሆስፒታል ፋርማሲ ክፍል ሀላፊዎች ፣የጤና ተቋማት ሀላፊዎች፣የአገልግሎቱ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች ፣ የአገልግሎቱ ዳይሬክተሮች ፣ የአገልግሎቱ ውል የተገባለት የአቅርቦት ሰርዓት አስፈፃሚ የኮማንድ ሴንተር አባላት በተገኙበት የአቅርቦት ስርዓቱ(Committd Demand & Supply system _CDSS) ምን እንደሚመስል ከህዳር 18 - 20 / 2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ እየገመገመ ይገኛል ።

የጤና ሚንስትር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ እንዳሉት አሁን ላይ የምንመለከተው ውጤታማነቱን ብቻ ሳይሆን የአሰራር ሂደቱ ምን ይመስላል እንዴት ማስቀጠል እንችላለን እንዲሁም የገጠሙንን ችግሮች ለቀጣይ መማሪያ በማድረግ ስርዐቱን እንዴት እናስቀጥል የሚለውን በትኩረት መወያየት ይገባል ብለዋል ።

ይህንን ስርዓት በመተግበራችን ምን አይነት የህክምና ግብዓት ለየትኛው አካባቢ እንደሚያስፈልጉ መለየት መቻሉን ሚኒስቴር ድኤታዋ አንስተው ፤ ለበርካታ አመታት ማነቆ የነበረውን የትንበያ ትክክለኝነት ማስፈን ችለናል ብለዋል ።

የጤናውን ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት እየሰራን እንገኛለን ያሉት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው አገልግሎቱ በአዋጅ ውስጥ ተካቶ የራሱን መመሪያ በማዘጋጀት ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓትን ዘርግተን መተግበራችን የለውጥ ምዕራፍ ላይ መሆኑን አንስተው ፤ ስርዓቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የጋራ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

በቀጣይ ቀናት ከአገልግሎቱ እና ከጤና ተቋማት በሚነሱ ጉዳዩች ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል ።

# ማገልገል ክብር ነዉ!
ዘጋቢ ማኅሌት አበራ

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram