03/12/2025
የመጋዘኖች ወለል ደረጃዉን የጠበቀ ለማድረግ የጥገና ስራ እየተከናወነ ይገኛል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ደረጃዉን በጠበቀ መጋዘን እንዲቀመጡ ለማስቻል በዋና መጋዘን 6 እና 7 እንዲሁም በነገሌ ቦረና ቅርንጫፍ የኢፖክሲ ወለል ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የመጋዘን እና የፍሰት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ጀማል ተናግረዋል፡፡
ደረጃዉን የጠበቀ ወለል የህክምና ግብአቶችን ከአቧራ እና ከእርጥበት ለመከላከል ፣ ምቹ የስራ ቦታ ለመፍጠር እንዲሁም የቀን ተቀን ስራ ፍሰት ቀልጣፋ እንዲሆን ለማስቻል እንደሚያግዝ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
በቀጣይ ኢፖክሲ ወለል የሌላቸዉ መጋዘኖች ተለይተዉ የጥገና ስራዉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዉ ፤ ስራዉ በለጋሽ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ እንደሚከናወን አቶ መሀመድ ጠቁመዋል፡፡
#ማገልገል ክብር ነዉ!
ሰላም ይደግ