10/11/2025
የአገልግሎቱ ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ የቀጥታ ስርጭት አድማሱን 96% ማድረሱን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ በ5ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 79ጤና ተቋማት እና 5ሆስፒታሎች የጤና ፕሮግራም መድኃኒቶችን በቀጥታ ስርጭት ማድረሱን የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱል ወሌ ሀሰን ተናግረዋል።
ቅርንጫፉ በ2016ዓ.ም የቀጥታ ስርጭት አደማሱን 48% ብቻ እንደነበር አስታውሰው በ2017 በጀት አመት የስርጭት ተሽከርካሪዎችን በመጨመር እና በአጋር አካሉ Fright ln Time(FIT) እገዛ ወደ 96% በማድረስ የደንበኞች እርካታ መጨመር እንደተቻለ ገልፀዋል።
አክለውም የስርጭት ወጭንከ4% ወደ 0.7% መቀንስ እንደተቻለ አንስተዋል።
# ማገልገል ክብር ነው!
ሰላም ይደግ