Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

በኢትዮጵያ የክትባት አስተዳደርን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሀገር አቀፍ ጥናት ተጀመረ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀገሪቱን የቀጥታ የክትባት ስርጭት ...
02/01/2026

በኢትዮጵያ የክትባት አስተዳደርን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሀገር አቀፍ ጥናት ተጀመረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀገሪቱን የቀጥታ የክትባት ስርጭት 63% እና የጤና ፕሮግራሞች የቀጥታ ስርጭት 75% እንደሚያሰራጭ ይታወቃል ፤ በመሆኑም የተቀናጀ ውጤታማ የክትባት አስተዳደር ፣ የክትባት ብክለት ቁጥጥር እና የሙቀት መጠን ክትትል ጥናት በኢትዮጵያ ለመስራት የማስጀመሪያ ስነስርዓት በአገልግሎቱ ግቢ ተካሂዷል ።

ኢትዮጵያ ለበርካታ አመታት መከላከል ላይ ያተኮረ የጤና ፖሊሲ ይዛ እየሰራች እንደምትገኝ በዚህም ጠንካራ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ያነሱት በጤና ሚኒስቴር የክትባት አገልግሎት ሀላፊ አቶ መልካሙ አያሌው ፤ በዚህም የጤና ፖሊሲውን ከሚያስቀጥሉት ተግባራት መካከል የምንሰጠው ክትባት ጥራቱን ጠብቆ እየተሰራጨ እንደሚገኝ መከታተል ሲሆን ይህንንም በዚህ ጥናት ለማረጋገጥ ያግዘናል ብለዋል ።

ለጥናቱ በዋነኝነት ከ GAVI
ለጋሽ ድርጅት ድጋፉ መገኘቱን አቶ መልካሙ ተናግረው ሌሎች አጋር ድርጅቶ አስተባብሮ ወደ ተግባር በመግባቱን Oxford Policy Management _OPN ን አመስግነዋል ።

ይህንን ጥናት ከማንም ተፅዕኖ ነፃ ሆናችሁ መስራት ይገባል ብለው ያሳሰቡት ሀላፊው ፤ ጥናቱ የተሳካ እንዲሆን የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናደርጋለን ብለዋል ።

የአገልግሎቱ የ78 አመታት ተቋሚዊ ጉዞ እና ስትራቴጂክ እቅድ የአገልግሎቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ያቀረቡ ሲሆን ፤ ጥናቱ በ2030 እንደ ተቋም የያዝነውን ግብ ለማሳካት ፣ አሁን ምን ላይ እንደደረስንና ማስተካከል ያሉብንን ጉዳዮች በጉልህ እንደሚያሳየን ትልቅ ተስፋ ይጣልበታል ሲሉ አቶ ሰለሞን ገልፀዋል ።

በዚህ ጥናት የሚሰራው አዲስ ነገር ምን ምን እንደሆነ ፣ ጥናቱ የሚዘጋጅበትን ዝርዝር ፣ መረጃ ለሚሰበስቡ አካላት ስልጠና መሰጠቱን እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን የስራ ሂደት አማካሪ እና ጥናት አስተባባሪ አቶ ወንድወሰን በዝርዝር አቅርበው ፤ ጥናቱ የቅርብ ጊዜ መረጃ እንዲኖር እንደሚያደርግና WHO በሚጠይቀው መሰረት ሪፖርተር ማዘጋጀት እንደሚያስችል አስረድተዋል ።

# ማገልገል ክብር ነዉ!
ዘጋቢ ማኅሌት አበራ

"የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የኦዲት ግኝቶችን በማረም ረገድ እንደ ምሳሌ የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነ ነው" ---- ቋሚ ኮሚቴው--------------‎‎(ዜና ፓርላማ) ...
02/01/2026

"የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የኦዲት ግኝቶችን በማረም ረገድ እንደ ምሳሌ የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነ ነው" ---- ቋሚ ኮሚቴው
--------------
‎‎(ዜና ፓርላማ) ታኅሣሥ 23፣ 2018 ዓ.ም፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የኦዲት ግኝቶችን መነሻ በማድረግ የጀመራቸው የሪፎርም ስራዎችና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለሌሎች ተቋማት እንደ ምሳሌ የሚጠቀስ መሆኑን ገለጸ።

‎ቋሚ ኮሚቴው በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ባደረገው የመስክ ምልከታ፣ ተቋሙ ቀደም ሲል የነበሩ የኦዲት ግኝቶችን መሰረት በማድረግ የወሰዳቸው የማስተካከያ እርምጃዎች ውጤታማ መሆናቸውን አረጋግጧል።
በተለይም የመድኃኒት አቅርቦትና ስርጭት ስርዓቱን በዘመናዊ ሶፍትዌር (ERP) መደገፉ ስራውን ከማቀላጠፍ ባለፈ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን እንዲሰፍን ማድረጉን ቋሚ ኮሚቴው አድንቋል።

‎የመድኃኒት መጋዝኑ ደረጃውን የጠበቀ መውጫና መግቢያ ያለው መሆኑ፣ መድኃኒቶች እንደየባህሪያቸው ተለይተው በዘመናዊ መደርደሪያዎች መቀመጣቸው እና የተደራጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋቱ ለሌሎች ቅርንጫፎችም እንደ ተሞክሮ ሊወሰድ የሚችል መሆኑ ተጠቁሟል።

‎የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ የሽመቤት ደምሴ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከጤና ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየሰራበት ያለው "የፍላጎት ትንበያ ስርዓት" የመድኃኒት እጥረትን ለመቅረፍ የሚኖረው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም "ERP Skill Matrix" የተሰኘው የሰራተኞችን ክህሎት መለኪያ ዘዴ እና መድኃኒቶችን እስከ ጤና ተቋማት ድረስ በራሱ ትራንስፖርት የማድረስ አሰራሩ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል።

‎ሰብሳቢዋ አክለውም፣ በመጋዘን ውስጥ መድኃኒቶችን ለማንቀሳቀስ የሚያገለግሉ የእጅ ትራኮች (Manual Trucks) እንደ መድኃኒቶቹ ዓይነት ተለይተው ጥቅም ላይ መዋላቸው ለደህንነታቸው የሚሰጠውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከመድኃኒት ሽያጭ ክፍያ አሰባሰብ ጋር የተያያዙ አፈጻጸሞች ይበልጥ ሊሻሻሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አስናቀች ደቺሳ በበኩላቸው፣ ቅርንጫፉ በአራት ክልሎች ለሚገኙ 9.6 ሚሊዮን ለሚሆኑ ህዝቦች አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸዋል። ቀደም ሲል በአቅርቦት ሂደት ላይ የነበሩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ አሁን ላይ ከጤና ተቋማት ጋር በበጀት ላይ የተመሰረተ ውል ተገብቶ ወደ ስራ መገባቱን አስረድተዋል።

‎የ"ERP" ሲስተም ተግባራዊ መደረጉ እያንዳንዱን የመድኃኒት ሽያጭና የክምችት ቁጥጥር (Inventory Analysis) የተቀናጀ እንዳደረገው የገለጹት ስራ አስኪያጇ

‎የተጀመረው የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት በጤና ተቋማት ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ፣ ቋሚ ኮሚቴው የሰጣቸውን አስተያየቶች በመውሰድ ክፍተቶችን ለማረም እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

‎(በ አምላኩ ነጋ)
Copied from House of Peoples Representatives of FDRE

02/01/2026
መድኃኒቶችን ያጎደለዉ ግለሰብ ተቀጣ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከሀምሌ 1/2014 -ሰኔ30/2015 ዓ.ም  ድረስ የዋና መጋዘን 3 ኃላፊ የነበረዉ ...
01/01/2026

መድኃኒቶችን ያጎደለዉ ግለሰብ ተቀጣ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከሀምሌ 1/2014 -ሰኔ30/2015 ዓ.ም ድረስ የዋና መጋዘን 3 ኃላፊ የነበረዉ አቶ ጭምዴሳ ቡርቃ የተገላባጭ ፈንድ እና የፕሮግራም መድኃኒቶችን ከ385ሺ ብር በላይ በማጉደል የወንጀል ክስ ተመስርቶበት ዉሳኔ ተሰጥቷል፡፡

ጉድለቱ በኦዲት ሪፖርት የተረጋገጠ በመሆኑ የክስ ሂደቱን ሲከታተል ቆይቶ ታህሳስ 08/2018 በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት አዲስ ከተማ ምድብ 3 በዋለዉ ችሎት ተከሳሽ አቶ ጭምዴሳ ከ385 ሺብር በላይ እንዲከፍል እና ዉሳኔ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ከፍሎ እስኪያጠናቅቁ 9% ወለድ ጋር እንዲከፍል ፍርድቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ
ሰላም ይደግ

Happy New Year 2026! 🌍✨The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service (EPSS) extends its warmest New Year greetings to our ...
31/12/2025

Happy New Year 2026! 🌍✨

The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service (EPSS) extends its warmest New Year greetings to our international suppliers, supply chain stakeholders, donors, and strategic partners.

We are grateful for your continued collaboration and commitment to strengthening the healthcare supply chain in Ethiopia.

May 2026 be a year of greater impact, innovation, and shared success as we work together to ensure health security for all.Happy New Year!

28/12/2025

ይህ መድሃኒትን በድሮን የማድረስ ፕሮግራም በጤና ሚኒስቴር፣ ኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ፣የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) እና በFreight in Time በትብብር እየተተገበረ ነው።,,

ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በዳሰነች ወረዳ  #በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በይፋ ጀመረ____________የጤና ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽ...
28/12/2025

ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በዳሰነች ወረዳ #በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በይፋ ጀመረ
____________

የጤና ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ጋር በመተባበር፣ የማርበርግ ቫይረስ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የህይወት አድን #መድኃኒቶችንና ክትባቶችን በድሮን የማድረስ ስራ ዛሬ በይፋ ጀምሯል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታትና ራቅ ያሉ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ በወሰደው የፈጣን ምላሽ እርምጃ፣ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #በዳሰነች ወረዳ በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በስኬት ተከናውኗል።

የዳሰነች ወረዳ ካለው ራቅ ያለ መልክዓ ምድር አኳያ በመኪና ለማጓጓዝ ረጅም ሰዓታት ይወስድ የነበረውን ጉዞ፣ በድሮን በመታገዝ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ክትባቱን በ –80°C ቅዝቃዜ ጠበቆ በማድረስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ክትባቱን መስጠት ጀምሯል።

ይህም ተግባር የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ወረርሽኞችን ቀድሞ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገሩን በተግባር ያሳየበት ነው።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ለመመከት የራሷን የውስጥ አቅም እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም መጀመሯን የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ሲሆን፣ በቀጣይም ይህ በድሮን መድኃኒት የማድረስ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ለአገልግሎቱ አሶሳ ቅርንጫፍ የምስጋና ሠርተፊኬት አበረከተ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አሶሳ ቅርንጫፍ  #በታላቁ  #ህዳሴ  #ግድ...
27/12/2025

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ለአገልግሎቱ አሶሳ ቅርንጫፍ የምስጋና ሠርተፊኬት አበረከተ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አሶሳ ቅርንጫፍ #በታላቁ #ህዳሴ #ግድብ በጥበቃ ስራ ለሚገኙ እንዲሁም ለኮስታል ጋርድ አባላት እና አመራሮች የተለያዩ መድኃኒቶችን በመለገስ ላበረከተዉ አስተዋፅኦ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የምስጋና ሠርተፊኬት ተበርክቷል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ!

የሀገር ውስጥ ምርት ለጤናው ዘርፍ፡ አገልግሎቱ ከአምራቾች ጋር የነበረውን አፈጻጸም ገመገመ ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እ.ኤ.አ በ2030 በአፍሪካ ፈጣን...
25/12/2025

የሀገር ውስጥ ምርት ለጤናው ዘርፍ፡ አገልግሎቱ ከአምራቾች ጋር የነበረውን አፈጻጸም ገመገመ ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እ.ኤ.አ በ2030 በአፍሪካ ፈጣንና ቀልጣፋ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ያለው ተቋም ለመሆን የያዘውን ራዕይ ለማሳካት እየሰራ ይገኛል።

ይህንኑ ግብ ለማሳካት የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ማሳደግና ተሳትፏቸውን ማጠናከር አንዱ ቁልፍ ስትራቴጂ ነው።

በዚሁ መሰረት፣ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ከሀገር ውስጥ አምራቾች ጋር የአፈጻጸም ግምገማ አካሂደዋል።

በውይይቱ ላይ አምራቾች የህክምና ግብዓቶችን በተሰጣቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ማቅረባቸውና ያልቀረቡ ግብዓቶች በሚጠናቀቁበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በግምገማው ወቅት ዋና ዳይሬክተሩ የሚከተሉትን ዋና ዋና የአሰራር አቅጣጫዎች ሰጥተዋል፦

✅ብክነትን መቀነስ፦ በመጋዘን በቂ ክምችት ያላቸው የህክምና ግብዓቶች የመጠቀሚያ ጊዜያቸው (Expiry date) እንዳያልፍ ለማድረግ፣ አምራቾች የማምረቻ ጊዜያቸውን እንዲያዘገዩ ተደርጓል።

✅አቅርቦትን ማፋጠን፦ በክምችት እጥረት ያለባቸው ግብዓቶች በአጭር ጊዜ ተመርተው ለአገልግሎቱ እንዲቀርቡ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ይህ እርምጃ በመድኃኒት አቅርቦት ላይ የሚታየውን መቆራረጥ ከመቅረፉ ባለፈ፣ ያለአግባብ የሚባክኑ የህክምና ግብዓቶችን ምጣኔ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ይጠበቃል።

!
ዘጋቢ፦ ማኅሌት አበራ

የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ የአዋጅ ቁጥር 1354/2017 ትግበራ ያለበት ደረጃ ገመገመ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ...
25/12/2025

የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ የአዋጅ ቁጥር 1354/2017 ትግበራ ያለበት ደረጃ ገመገመ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አዲሱን የማቋቋሚያ አዋጅ ተከትሎ እያከናወናቸው ያሉ የሪፎርም ስራዎችንና ያስመዘገባቸውን ውጤቶች በዝርዝር ገመገመ።

ቁልፍ የለውጥ ነጥቦች እና የሪፎርም ስራዎች የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ወርቀሰሞ ማሞ እና ምክትል ሰብሳቢው ዶ/ር ታደለ ቦርቃ በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ግምገማ፤ ተቋሙ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የመድኃኒት እጥረትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የጀመራቸው ስራዎች ውጤታማ መሆናቸው ተመልክቷል።

በግምገማው ወቅት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት፤ አዋጁን መሠረት በማድረግ የሚከተሉት ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል፦

✅ዲጂታላይዜሽን (Smart Digital Health Supply Chain) የተቋሙን አሰራር ዘመናዊና ግልጽ ለማድረግ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ በጥሩ ደረጃ እየተከናወነ ይገኛል።

✅የመሠረተ ልማት ዝመና፡ የመድኃኒት መጋዘኖችን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ (Standardized) ለማድረግ ሰፊ የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።

አዲሱ አዋጅ ተቋሙ ተወዳዳሪና ቀልጣፋ እንዲሆን ትልቅ ዕድል ፈጥሯል፤ ከፍተኛ አመራሩ እያደረገ ያለው ክትትልና ድጋፍ ለተመዘገበው ስኬት መሰረት ነው — ወ/ሮ ወርቀሰሞ ማሞ (የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ)

የመስክ ምልከታ እና ቀጣይ አቅጣጫ
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በተቋሙ መጋዘኖች ተገኝተው የተከናወኑ የዲጂታላይዜሽን እና የንብረት አያያዝ ስራዎችን በአካል ተመልክተዋል።

አባላቱ በሰጡት አስተያየት፤ ተቋሙ የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙን በማሳደግ የፈጠረው ለውጥ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው፣ የህዝብን የጤና ዋስትና ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ኮሚቴው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

ማገልገል ክብር ነው!
ሠላም ይደግ

UK Government Donates Critical Medical Supplies to Ethiopia to Combat Marburg Virus፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ADDIS ABABA – The Gove...
25/12/2025

UK Government Donates Critical Medical Supplies to Ethiopia to Combat Marburg Virus
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ADDIS ABABA – The Government of the United Kingdom has delivered a significant batch of medical supplies and equipment to Ethiopia to bolster the country’s preparedness and response to the Marburg virus.

During the handover ceremony, Ethiopia’s Minister of Health, Dr. Mekdes Daba, expressed her gratitude to the UK government for the timely assistance.

She emphasized that the donation is vital for combating cross-border pathogens and enhancing the capacity of healthcare facilities to manage public health emergencies.

"These supplies will play a pivotal role in protecting our frontline healthcare workers who are at the heart of our pandemic response efforts," Dr. Mekdes stated.

The UK Ambassador to Ethiopia, Darren Welch, reaffirmed the United Kingdom's commitment to supporting Ethiopia's journey toward self-reliance in medical equipment manufacturing.

He noted that a robust health system is essential for preventing and containing outbreaks that pose transboundary risks.

The support package includes Personal Protective Equipment (PPE) and essential diagnostic kits, designed to improve Ethiopia’s overall epidemic readiness and national health security.

የእንግሊዝ መንግስት  የማርበርግ የቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያግዝ የቁሳቁስ  ድጋፍ አደረገ።።።።።።።።።።።።።።።።።በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የእንግ...
25/12/2025

የእንግሊዝ መንግስት የማርበርግ የቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያግዝ የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
።።።።።።።።።።።።።።።።።

በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የእንግሊዝ መንግሥት ላደረጋቸው ወቅታዊ ድጋፎች አመስግነዋል።

ልገሳው ድንበር አቋርጠው የሚመጡ በሽታ አምጪ ተህዋሲያንን ለመዋጋት እና የጤና ተቋማት ለሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ የመስጠት አቅምን ለማጠናከር እንደሚረዳ ተናግረዋል።

ዶ/ር መቅደስ አክለውም የተለገሱት መሣሪያዎች በወረርሽኝ ምላሽ ጥረቶች ውስጥ የተሳተፉ ግንባር ቀደም የጤና ባለሙያዎችን ለመጠበቅ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወቱ ተናግረዋል።

የዩኬ አምባሳደር ዳረን ዌልች እንዳሉት ዩናይትድ ኪንግደም ኢትዮጵያ የሕክምና መሳሪያዎችን በማምረት ረገድ ራሷን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት ትደግፋለች።

የሁለቱ ሃገራት ትብብር ከኢትዮጵያ አልፎ ለአህጉራዊ እና ለዓለም አቀፍ የጤና ደህንነት አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል።

አምባሳደሩ ጠንካራ የጤና ሥርዓቶች ድንበር ተሻጋሪ አደጋዎችን የሚፈጥሩ ወረርሽኞችን ለመከላከል እና ለመቋቋም አስፈላጊ መሆናቸውን አፅንዖት ሰጥተዋል።

ድጋፉ የግል መከላከያ መሳሪያዎችን (PPE) እና ወሳኝ የምርመራ ኪቶችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም የኢትዮጵያን የወረርሽኝ መከላከል ዝግጁነት እና ምላሽ ለማሻሻል እንደሚያግዝ ተገልጿል።

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram