01/03/2026
እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ፣ የነፃነት ተምሳሌት እና የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ማህተም ነው!
ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን በደማቸውና በአጥንታቸው የፃፉት ታሪክ ዛሬም ድረስ በፅናት እንድንቆም ብርታት ይሆነናል።
እኛም በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት፣ ይህንን የአባቶቻችንን የድል አድራጊነት መንፈስ በመውረስ፣ የሕዝባችንን ጤና ለመጠበቅና ጥራት ያለው መድኃኒት በየደረጃው ለሚገኝ የጤና ተቋም በተመጣጣኝ ዋጋ ለማድረስ የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን።
የአድዋ ድል የሁላችንም ኩራት ነው!