31/03/2026
ከባለድርሻ አካላት ጋር ያሉ ስራዎች በዲጅታል ስርአት ለማስተሳሰር እየተሰራ ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አገልግሎቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ስራ በዲጅታል ስርአት ለማስተሳሰር እየተሰራ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ በባለድርሻ አካላት ማጠቃለያ መድረክ ተናግረዋል።
በተለይም የፋይናንስ አሰራሮችን ወደ ዲጅታል በመቀየር ጊዜን በመቆጠብ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል።
አያይዘውም በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተው ጦርነት የአቅርቦት ሰንሰለቱን እንዳያስተጓጉል ከመቼውም በላይ የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚጠይቅ ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል።
የባለድርሻ አካላት ውጤታማነት ከአመት አመት በእጅጉ እየተሻሻለ ነው ያሉት ዶ/ር አብዱልቃድር ይህም ጠንካራ የአቅርቦት ሰንሰለት ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
መድረኩ ተወያይተን ብቻ የምንሄድበት ሳይሆን በፍጥነት ወደ ትግበራ ገብተን የክትትል ስራዎችን የምናጠናክርበት ነው ሲሉ የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው ተናግረዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለአገልግሎቱ ያላቸውን አጋርነት አረጋግጠዋል።
ለ3ቀናት ሲካሄድ የቆየው 8ተኛው የባለድርሻ አካላት የመክክር መድረክ የተለያዩ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።
ሰላም ይደግ