Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

የአገልግሎቱ ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ የቀጥታ ስርጭት አድማሱን 96% ማድረሱን አስታወቀ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ በ5ዞኖች ውስጥ የሚ...
10/11/2025

የአገልግሎቱ ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ የቀጥታ ስርጭት አድማሱን 96% ማድረሱን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቀብሪደሃር ቅርንጫፍ በ5ዞኖች ውስጥ የሚገኙ 79ጤና ተቋማት እና 5ሆስፒታሎች የጤና ፕሮግራም መድኃኒቶችን በቀጥታ ስርጭት ማድረሱን የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱል ወሌ ሀሰን ተናግረዋል።

ቅርንጫፉ በ2016ዓ.ም የቀጥታ ስርጭት አደማሱን 48% ብቻ እንደነበር አስታውሰው በ2017 በጀት አመት የስርጭት ተሽከርካሪዎችን በመጨመር እና በአጋር አካሉ Fright ln Time(FIT) እገዛ ወደ 96% በማድረስ የደንበኞች እርካታ መጨመር እንደተቻለ ገልፀዋል።

አክለውም የስርጭት ወጭንከ4% ወደ 0.7% መቀንስ እንደተቻለ አንስተዋል።

# ማገልገል ክብር ነው!
ሰላም ይደግ

10/11/2025

ጎብኝዎች ስለ አገልግሎቱ ለውጥ የመሠከሩት

በእቅድ ላይ የተመሰረተ ግዥን ለመፈፀም ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት ወሳኝ ነዉ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በ2023ዓ.ም በአፍሪካ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ እና ብቁ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ያለዉ...
07/11/2025

በእቅድ ላይ የተመሰረተ ግዥን ለመፈፀም ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት ወሳኝ ነዉ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በ2023ዓ.ም በአፍሪካ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ እና ብቁ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ያለዉ ተቋም የመሆን ራዕይን ለማሳካት ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት (Committed Demand and Supply System; CDSS) ወሳኝ እንደሆነ የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ንጉሴ ገልፀዋል።

ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓትን ለማሳካት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትና የመድኃኒት ፈንድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1354/2017ዓ.ም በመፅደቁ በአዋጁ አንቀጽ 23 እና24 መሰረት እንዲሁም በ1066/2017 የግዥ መመሪያ ተግባራዊ መሆኑ አዎንታዊ ሚና ያላቸዉ ሲሆን ፤ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም መተግበር ፤ ቁርጠኛ የአመራር ብቃትና ፍላጎትን መሰረት ያደረገ አቅርቦት CDSS እንዲሳካ አይነተኛ ድርሻ እንዳላቸዉ ም/ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

በተያያዘም CDSS ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለዉ ያስታወሱት አቶ ሰሎሞን ለአብነትም ቀጣይነት ያለዉና ፍትሃዊ የሆነ አቅርቦትን እንደሚፈጥር ፤ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን እንደሚመልስ ፤ የህክምና ግብዓት የግዥ ጊዜን እንደሚያሳጥር እንዲሁም የመዲኃኒቶችን ብክነትን እንደሚቀንስ አመላክተዋል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

ባለድርሻ አካላት ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት (CDSS) ዉጤት እንዲያመጣ ከፍተኛ ሚና አላቸዉ፨፨፨፨፨፨፨፨የጤና ሚኒስቴር ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት እንዲሳካ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮ...
07/11/2025

ባለድርሻ አካላት ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት (CDSS) ዉጤት እንዲያመጣ ከፍተኛ ሚና አላቸዉ
፨፨፨፨፨፨፨፨

የጤና ሚኒስቴር ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት እንዲሳካ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን ከመምራት ባለፈ የጤና ተቋማትን አቅም ማጎልበት ፣ ማቀናጀት እና በየጊዜዉ መገምገም እንደሚገባው የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ንጉሴ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትም የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ሲሆን የግብዓት ፍላጎት አስተዳደርና የአቅርቦት እቅድን ማስተካከል ፤ የመድኃኒቶችን ዋጋ መተመን ፤ ጥራታቸዉ የተረጋገጡ መድኃኒቶችን ግዥ መፈፀም ፤ ቴክኒካዊ ድጋፍ ማድረግና መረጃዎችን ለጤና ተቋማቱ የሚሰጥ ይሆናል።

በተጨማሪም የመስተዳደርና የክልል የአስተዳደር አካላትም ለCDSS ስኬት ጉልህ ሚና እንዳላቸዉ አቶ ሰሎሞን ጠቁመዉ የግዥ በጀት ከመያዝ አንስቶ ጤና ተቋማቱን እንደሚያቀናጁና እንደሚደግፉ ተናግረዋል።

አገልግሎቱ ከ5ሺ31 የሀገሪቱ ጤና ተቋማት 100% በሚባል ደረጃ ዉል በተገባለት የአቅርቦት ስርዓት መሰረት ግብዓቶችን ለማቅረብ በመዋዋል ወደ ስራ ገብቷል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

ዉል በተገባለት የአቅርቦት ስርአት  4991  ጤና ተቋማት  መድኃኒት ለመግዛት ዉል ገብተዋል ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የህክምና ግብአቶችን አቅርቦት ...
07/11/2025

ዉል በተገባለት የአቅርቦት ስርአት 4991 ጤና ተቋማት መድኃኒት ለመግዛት ዉል ገብተዋል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የህክምና ግብአቶችን አቅርቦት ለማሻሻል እና የማህበረሰቡን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችለውን ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት የደረሰበትን ደረጃ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ገምግሟል።

የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ እንደተናገሩት በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የመንግስት ጤና 4991 የጤና ተቋማት በጀት ይዘው፡ራሳቸው መጥነው የህክምና ግብአቶችን ከአገልግሎቱ ለመግዛት ውል መግባታቸውን ተናግረው ፤ በአገልግሎቱ በኩል አጠቃላይ 42 ቢሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብአቶችን ለማቅረብ ውል ገብተናል ሲሉ አንስተዋል።

ስርአቱ አገልግሎቱ የያዘውን ራዕይ እና ተልዕኮ ለማሳካት ቁልፍ ሚና የሚጫዎት በመሆኑ ሁሉም ሰራተኛ በንቃት እና በትብብር ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል።

አሁን ላይ ከእቅዳችን አኳያ እየተሰሩ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ሲራዎች ተጠናቀው የስርጭት ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ስርአቱን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማራመድ ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት(CDSS) ኢንሸቲቭ ሳይሆን ህጋዊ መሰረት ያለው የስርዓት ለውጥ ነው፤በተዘጋጅው መመሪያ እና ዳሽ ቦርድ በመታገዝ በእያንዳዱ የስራ ክፍል እና ቅርንጫፎች የሚተገበር የአገልግሎቱ የዚህ አመት ቁልፍ ተግባር ነው ብለዋል፡፡

ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርአት ከሚጠቀሙ ሌሎች ሀገራት ያላቸውን ተሞክሮ በመቀመር ስራዎችን ለመከወን እንደሚያስችል እና ለዚህም ችግሮች ሲፈጠሩ አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጡ ለማድረግ ኮማንድ ሴንተር መቋቋሙን ተናግረዋል።

የአገልግሎቱ ሰራተኞች የተሰጠውን ግንዛቤ መሰራት በማድረግ በዊንግ እና በዳይሬከረቶሬት ደረጃ ውይይቱን የሚያስቀጥሉ ሲሆን በጤና ተቋማት እና በአገልግሎቱ መካከል እኩል ተጠያቂነት ለሚያሰፈነው ህጋዊ አሰራር ለተግባራዊነቱ ቁርጠኞች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነው!!
ሰላም ይደግ

የስኳር መድኃኒቶች የስርጭት መጠን እያደገ ይገኛል፨፨፨ከሀምሌ 1 2017ዓ.ም እስከ ጥቅምት 26 2018ዓ.ም ድረስ ለስኳር በሽታ ህክምና የሚዉሉ መድኃኒቶች በሁሉም ቅርንጫፎች መሰራጨታቸዉን ...
06/11/2025

የስኳር መድኃኒቶች የስርጭት መጠን እያደገ ይገኛል
፨፨፨
ከሀምሌ 1 2017ዓ.ም እስከ ጥቅምት 26 2018ዓ.ም ድረስ ለስኳር በሽታ ህክምና የሚዉሉ መድኃኒቶች በሁሉም ቅርንጫፎች መሰራጨታቸዉን የአገልግሎቱ የኢንቬንቶሪ ማኔጅመንት ባለሞያ አቶ ክብርአለም ሃይማኖት ገልፀዋል።

በቁጥር 1.2 ሚሊየን የሚጠጉ እንደ ኢንሱሊን ፣ ሚትፎርሚንና ግሊቤንክላሚድ አይነት መድኃኒቶች የተሰራጩ ሲሆን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ተቋማት ጋር በመቀናጀት የስኳር ህመምተኞች አገልግሎት እንዲያገኙ እየሰራ ይገኛል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

የአገልግሎቱ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ከአጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ከአጋር አካላት ጋር የምክ...
05/11/2025

የአገልግሎቱ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ከአጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ከአጋር አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡

በምክክሩ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ በ2017 ዓ.ም ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለተሳታፊዎች ገለጻ የተደረገ ሲሆን ፤ የመጋዘን አያያዙን እና አጠቃላይ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ለተሳታፊዎች በማስጎብኘት በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

ከፍትህ ቢሮ የተሳተፉ የህግ ባለሙያዎች መስሪያ ቤቱ እየሰራ ያለው ስራ ያደነቁ ሲሆን ፤አገልግሎቱ ለማህበረሰቡ ጤና መሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ በቀጣይ የተጠናከረ እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡

የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ አቶ አምሳሉ ጫኔ እንደተናገሩት ጤና ተቋማት በዱቤ የወሰዱትን ገንዘብ በወቅቱ ባለመክፈላቸው መድኃኒት ገዝቶ በወቅቱ ለማቅረብ የሚያስቸግር በመሆኑ ተቋማት ያለባቸውን እዳ በወቅቱ መክፈሉ ጥቅሙ ለጋራ ነዉ ብለዋል፡፡

አክለዉም ፈለገ ህይዎት ሆስፒታል በፍትህ አካላት እገዛ እና የማግባባት ስራ ከነበረበት ከሀያ አራት ሚሊዮን ብር በላይ እዳ ውስጥ ከሀያ ሚሊዮን ብር በላይ እንዲከፍሉ መደረጉን አንስተዉ ፤ ከአጋር አካላት የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ!
ሰላም ይደግ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች መስፈርቱን የሚያሟሉ አ...
05/11/2025

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
ተ.ቁ የሥራ መደቡ መጠሪያ ተፈላጊ ችሎታዎች የሥራ ልምድ
/በዓመት/ ደረጃ
የደመወዝ መጠን የቤት አበል ብዛት
የስራ ቦታ
የትምህርት
ደረጃ የትምህርት ዓይነት
1 ባዮሜዲካል ኢንጂነር የመጀመሪያ ዲግሪ ባዮሜዲካል ኢንጂነሪንግ 0 ዓመት XI 14,983 6,000 1 ዋና መስሪያ ቤት
2 የGPS ሲስተም አስተዳደር ባለሙያ የመጀመሪያ ዲግሪ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ ኢንፎርሜሽን ሲስተም /ሳይንስ/ ቴክኖሎጂ፣ማናጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም 2 ዓመት በኔትወርክ እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎች የሰራ/ች IX 12,566 6,000 1

ማሳሳቢያ፡-
በምዝገባ ወቅት አመልካቾች የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና የማይመለስ አንድ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ፆታ አይለይም፤ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡
በተራ ቁጥር 1 ላይ በተጠቀሰው የሥራ መደብ ላይ የሚያመለክቱ አመልካቾች የታደሰ የሙያ ፈቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
መንግስታዊ ካልሆኑ መ/ቤቶች የሚቀርቡ የሥራ ልምድ ማስረጃዎች በደንቡ መሠረት የገቢ ግብር የተከፈለባቸው መሆኑን የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
መመዝገቢያ ቀንና ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ባሉት 7/ሰባት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ሆኖ ከሰኞ እስከ ሐሙስ ጠዋት ከ2፡30-6፡30 ሰዓትና ከሰዓት ከ7፡30-11፡30 ሰዓት እንዲሁም ዓርብ ጠዋት ከ2፡30-5፡30 ከሰዓት ከ7፡30-11፡30 ሰዓት ድረስ ይሆናል፡፡
የምዝገባ ቦታ በዋናው መ/ቤት

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት
ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ፊትለፊት

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ክፍት የሥራ መደቦች መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

ተ.ቁ የሥራ መደቡ መጠሪያ ተፈላጊ ችሎታዎች የሥራ ልምድ
/በዓመት/ ደረጃ የደመወዝ መጠን የቤት አበል ብዛት
የስራ ቦታ
የትምህርት ደረጃ የትምህርት ዓይነት
1 የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎችንመጋዘን ኃላፊ የመጀመሪያ ዲግሪ ፋርማሲ 0 ዓመት XII 16,348 6,000

01 ዋና መስሪያ ቤት ሳሪስ
01 ዋና መስሪያ ቤት ሞጆ
01 ዋና መስሪያ ቤት አዳማ

ማሳሳቢያ፡-
ፆታ አይለይም፤ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡ በምዝገባ ወቅት አመልካቾች የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና የማይመለስ አንድ ኮፒ እንዲሁም የሙያ ፍቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

አመልካቾች የትምህርት ማስረጃ ሲያቀርቡ ስቱደንት ኮፒ ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡

የመመዝገቢያ ቀንና ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ባሉት 7/ሰባት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ሆኖ ከሰኞ እስከ ሐሙስ ጠዋት ከ2፡30-6፡30 ሰዓትና ከሰዓት ከ7፡30-11፡30 ሰዓት እንዲሁም ዓርብ ጠዋት ከ2፡30-5፡30 ከሰዓት ከ7፡30-11፡30 ሰዓት ድረስ ይሆናል፡፡

የምዝገባ ቦታ በዋናው መ/ቤት የሰው ኃብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት
ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ፊትለፊት

ለሐሩራማ በሽታዎች መከላከያ የሚውሉ መድኃኒቶች አቅርቦት ሁኔታ በአርባምንጭ ቅርንጫፍ የመስክ ምልከታ ተካሄደ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጤና ሚኒስቴር ከኦርቭስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ እ...
03/11/2025

ለሐሩራማ በሽታዎች መከላከያ የሚውሉ መድኃኒቶች አቅርቦት ሁኔታ በአርባምንጭ ቅርንጫፍ የመስክ ምልከታ ተካሄደ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጤና ሚኒስቴር ከኦርቭስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ እና ከሌሎች የተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያከናውነውን ተግባር አለም አቀፍ ጎብኝዎች ምልከታ ያደረጉ ሲሆን ፤ በዚህም በአገልግሎቱ አርባምንጭ ቅርንጫፍ በመገኘት የመስክ ጉብኝት አድርገዋል።

በመስክ ጉብኝቱ የጤና ሚንስተር ተወካይ ፣ የኦርቭስ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

በቅርንጫፉ በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ብሎም ለማጥፋት የሚያስችሉ የተለያዩ መድኃኒቶችን የክምችት ሁኔታ እና ወደ ተጠቃሚው የማድረስ አሰራር ስርአት በሰፊው ምልከታ ማድረጋቸውን የቅርንጫፋ ስራ አስኪያጅ አቶ አንድነት አሰፋ ተናግረዋል።

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ባዩት የአቅርቦት አሰራር ስርአት መደሰታቸውን ገልፀው ፤ ቅርንጫፍ መ/ቤቱ ላደረገላቸው አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል፡፡

# ማገልገል ክብር ነው!
ሰላም ይደግ

31/10/2025
29/10/2025

ይህን ዶክመንተሪ ፊልም በማህበራዊ ሚድያዎቻችን በቅርብ ቀን ይጠብቁን፡፡

"መንግስት ጤና አገልግሎቱ ላይ የተለያዩ ድጋፎችን ያደርጋል፡፡"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሰጡት ማብራሪያ
28/10/2025

"መንግስት ጤና አገልግሎቱ ላይ የተለያዩ ድጋፎችን ያደርጋል፡፡"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሰጡት ማብራሪያ

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram