14/03/2016
ሀገሬ ኮሚዩኒቲ ደቨሎፕመንት አሶሴሽን አፋር ላይ እየሰራ ያለውን ፕሮጀከት ለማስቀጠል እና በክልሉ በኢሊኖ ምክንያት ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ ለመስጠት ህዝባዊ መዋጮ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል ላይ ቴሌቶን ማካሄዱን ተከትሎ የተለያዩ ባለ ሀብቶች እና ድርጅቶችን ባናገረበት ጥሩ ምላሽ እያገኘ ነው ፡፡ ለዚህም አብይ ምሳሌ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሚለርስ አሶሴሽን በስሩ የሚገኙትን ዱቄት እና የዱቄት ውጤት አምራቾችን በማስተባበር ከ 2000(ሁለት ሺ ) ኩንታል ዱቄት በላይ በማሰባሰብ ለመለገስ ቃል ገብቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ፡፡ለማሰባሰብ ሂደቱም አመቺ እና ቀልጣፋ ይሆን ዘንድ ስልት ወጠኖ እየሰራ ነው ፡፡ ያሰባሰብ ሂደቱም በአሁኑ ጊዜ በ6(ስድስት ) ክላስተር በመከፋፈል ፡
ምድቡም
1. በቃልቲ አከባቢ ዙሪያ ላሉት የዱቄት ፋብሪካዎች Echa food complex
2. በቡራዮ እና አዲስ አበባ አከባቢ ላሉት የዱቄት ፋብሪካ Afia food complex
3. በአለምገና ዙሪያ ላሉት ዱቄት ፋብሪካዎች Haymen flour factory
4. በደቡብ ካልል ከባቢ ላሉት የዱቄት ፋብሪካዎች አዋሳ ከተማ Metafray flour factory
5. ናዝሪት አከባቢ ላሉ የዱቄት ፋብሪካዎች Mohmed abubekr flour factory
6. በአሳላ ከተማ ከባቢ ላሉ የዱቄት ፋብሪካዎች አሰላ chilalo flour factory የተመደቡ ሲሆን አባላቶች በተመደቡበት ክላስተር ማበርከት የሚፈልጉትን በተመደቡበት ክላስተር እንዲያስረክቡ በኢትዮጵያ ሚለርስ አሶሴሽን በኩል ለሁሉም አባላት መልእክቱን በማድረስ ወደስራ ተገብቷ ፡፡ ለአሰራርም ይመች ዘንድ ሀገሬ ኮሚዩኒቲ ደቨሎፐምንት አሶሴሽን በአይነት ለሚለግሱ የዕቃ መረከቢያ ሰነድ አዘጋጅቶ ከላይ በተዘረዘሩት የዱቄት ፋብሪካዎች አስቀምጧል ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ላስረከቡት እቃ ህጋዊ የድርጅቱን ደረሰኝ መውሰዶን እንዳይዘነጉ ሀገሬ ያስገነዝባል ፡፡
Helping HCDA is assisting the needy!!!