Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

የተሻለ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት በሕፃናት ዙሪያ ከሚሰሩ አጋር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ተጠቆመ‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎በጋሞ ዞ...
15/11/2025

የተሻለ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት በሕፃናት ዙሪያ ከሚሰሩ አጋር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ተጠቆመ

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎በጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ አዘጋጅነት "ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የነጭ ሪቫን ቀንና የሕፃናት ቀን በድምቀት ተከብሯል።

‎የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሕሩት ማሞ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለፁት በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች በቅርብ ሰዎች ጭምር የሚፈፀሙ መሆናቸው ጉዳዩ ውስብስብ እና አሳሳቢ እንደሚያደርግ ገልፀው የአለም አቀፍ ትኩረት አግኝተው የወረዱ የንቅናቄ መድረኮችን በዓላማ ጽናት መፈጸም ይገባል ብለዋል።

‎በሴቶችና ሕፃናት ደህንነት የወጡ ደንቦች፣ ህጎችና ፖሊሲዎች በአግባቡ እንዳይተገበሩ የሚያደርጉ አካላት የግንዛቤ ችግር ለመቅረፍ እንደሚሰራ ጠቁመው በፍትህ ተቋማት የተያዙ የወንጀል ጉዳዮች በወቅቱ እንዲፈቱ ይደረጋል ብለዋል።

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርስ የስነልቦና፣ የአካል፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ጥቃት መከላከል የሁሉ ባለድርሻ አካላት መሆኑን ገልፀው በታችኛው መዋቅር የሚስተዋለውን የጉዳዩን አሳሳቢነት ማቃለልና ከመረጃ ማጥፋት ተግባር እንዲቆጠቡ አስገንዝበዋል።

‎በጤናው ዘርፍ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር፣ የጡት ካንሰር እና የስነ ተወልዶ ጤና ፓኬጆችን ለመተግበር የሴቶች ልማት ሕብረቶች ከጤና ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት እንዲሰሩ አሳስበዋል ።

‎የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ምሕረት ኩንታ በበኩላቸው በጋራ ከሚሰሩ ባለድርሻዎች ጋር በመተባበር የስተሪንግ ኮሚቴ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርግት አስወጋጅ ኮሚቴና የፍትህ ፎረም ማቀናጀት እንደሚገባ አውስተው የሕፃናት ጊዜያዊ መቆያ ማዕከላት ግንባታና የጥበቃ ስርዓት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

‎በሕፃናት ጥቃትና ሕገወጥ ዝውውር የመከላከል ተግባርና ሕፃናት በነፃነት ሐሳባቸውን የሚገልጹና የሚደመጡ እንዲሁኑ ስሰራ መቆየቱን የገለፁት ተሳታፊዎቹ ከተለያዩ አከባቢዎች ለስራ በሚል የሚመጡ አካላት ማንነታቸው እንዲጣራ በአጽንኦት ጠይቀዋል።

‎በመጨረሻም ጥያቄና መልስ ውድድር በማካሄድ እና በሰቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርስ ጥቃትን በማውገዝ መድረኩ ተጠናቋል።

ኢትዮጰያ የተከሰተውን  የሄሞራጅክ ፊቨር በሽታ ለመቆጣጠር የምታደርገው  ጥረት የሚደነቅ ነው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም‎‎ ‎የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊ...
15/11/2025

ኢትዮጰያ የተከሰተውን የሄሞራጅክ ፊቨር በሽታ ለመቆጣጠር የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም


‎የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral Hemorragic Fever) በሽታ መከሰቱን እና የበሽታዉን ምንነት በማረጋገጥ ላይ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

‎ሚኒስቴሩ በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት መቻሉን መግለፁ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ የአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም በደቡብ ኢትዮጰያ ክልል የተከሰተውን የሄሞራጅክ ፊቨር በሽታ ለመቆጣጠር የምታደርገው ጥረት የሚደነቅ ነው ሲሉ ገልፀውታል።

‎ዋና ዳይሬክተሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት ፣ ኢትዮጰያ በደቡብ የአገሪቱ ክፍል 8 ሰዎች ያጠቃውን በሽታ የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን ማረጋገጧን ገልፀዋል።

‎ በኢትዮጰያ የተከሰተውን በሽታ ፈጣንእና ግልፅ ምላሽ ለመስጠት የጤና ሚንስቴር፣የኢትዮጰያ ህብረተሰብ ጤና ኢንልቲትዮት እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጤና ቢሮ ያደረጉትን ጥረት ዋና ዳይሬክተሩ አድንቀዋል።

‎ይህ እርምጃ ኢትዮጰያ ወረርሽኑ በፍጥነት ለመቆጣጠር ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ አድናቆታቸውን ባሰፈሩት መልክት ገልፀዋል።

የማህጸን ጫፍ እና የጡት ካንሰር ምንነትን በማወቅ በሳቢያው የሚከሰተውን ሞት ለመቀነስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪ...
15/11/2025

የማህጸን ጫፍ እና የጡት ካንሰር ምንነትን በማወቅ በሳቢያው የሚከሰተውን ሞት ለመቀነስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የማህፀን ጫፍ እና የጡት ካንሰር ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።

‎በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይስማ ከተማ የማህጸን ጫፍ እና የጡት ካንሰር ምንነትን በማወቅ በሳቢያው የሚከሰተውን ሞት ለመቀነስ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎አብዛኛው ችግር በግንዛቤ እጥረት የሚመጣ ነው ያሉት አስተዳዳሪው ባለድርሻዎች የግንዛቤ ሥራዎችን በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎ባለፈው ዓመት ምርመራ ከተደረገባቸው ሴቶች መካከል 6 በመቶ በሚሆኑ ሴቶች ላይ የማህጸን ጫፍ ካንሰር መገኘቱን የገለጹት የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይኸነው ደሳለኝ በሽታው ቀላል ህክምና ያለ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በጊዜ ህክምና ካላገኙ በሽታው ገዳይ በመሆኑ ልክ ህብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ የሉም ያሉት የጽ/ቤት ኃላፊው ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የልየታ እና የምርመራ አገልግሎት እንደሚጀመርም አመላክተዋል።

‎በቀጣይ በሽታው ዙሪያ ለህብረተሰቡ ሙሉ የግንዛቤ ሥራ እንደሚሰራ እና በሳቢያው የሚመጣ ህመምና ሞት ለመቀነስ ቅድመ መከላከል ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተመላክቷል።

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች
15/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ (Hemorrhagic Fever) ለመከላከል ብሎም ለሞቆጣጠር ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተጠቆመ፤‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ...
14/11/2025

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ (Hemorrhagic Fever) ለመከላከል ብሎም ለሞቆጣጠር ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተጠቆመ፤

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

‎መምሪያው በጅንካ ከተማ በተከሰተው የሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ (Hemorrhagic Fever) ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር ስርጭቱን ለመግታት እንዲሁም ሰብዓዊና ማህበራዊ ቀውስ እንዳያስከተል ለመቆጣጠር የሚያስችል ዝግጅት እያደገ መሆኑ ታውቋል፡፡

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ ከሁሉም ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የውይይት መድረክ የተካሄደ ሲሆን በውይይቱ የመምሪያው ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ኃላፊው በንግግራቸው በሽታው በድንገት በክልላችን ጂንካ ከተማ በድንገት ተከስቶ በሰው ህይወት ላይ አደጋ አስከትሏል ብለዋል፡፡

‎አቶ ሴይፉ በሽታው በቀላሉ ከተያዙ እንስሳት ጋር በመነካካት፡ በሽንት፣ ምራቅ ፣ ወይም ሌሎች ከሰውነት በሚወጡ ፈሳሾች በሚነካኩበት ጊዜ፣ በነፍሳት ንክሻ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው የሚገኘው የደም ልገሳ፣ የሰውነት ፈሳሾች ጋር በሚኖር ንክኪ እንደሚተላለፍ በመግለፅ መላው ማህበረሰብ ብርቱ ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

‎በመጨርሻም በሁሉም መዋቅሮች የቀውስ አስተዳደር ስርአት /Incident Management system/ በማጠናከር የበሽታ ቅኝት ስራዎች እንዲሁም ትክክለኛ መረጃ ለማህበረሰቡ በማድረስ በሽታውን ለመከላከል ብሎም ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ከመቸውም በላይ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

ተቋማት የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር  ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ አለባቸው ‎++++++++++++++++++++++++++‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪ...
14/11/2025

ተቋማት የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ አለባቸው
‎++++++++++++++++++++++++++

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓለምፀሀይ ጳውሎስ በመደመር መንግሥት ዕሳቤ ሁሉም ተቋማት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን የመተግበር ግዴታ አለባቸው አሉ።

‎የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተሞክሮ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ነው።
‎ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ሪፎርሙ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደርን በሚፈለገው ልህቀት ያስቀጥላል።

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የመደመር መንግሥት ዕይታ ለዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው ስልጠና ወቅት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቅ እንዳለበት አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ገልጸዋል።
‎የመደመር መንግሥት ዕሳቤ ተቋማት ዘመናትን የሚሻገሩ ዘላቂና እኛን መምሰል አለባቸው በሚል በግልጽ መቀመጡን ገልጸዋል።

‎በመሆኑም ሪፎርሙ በሀገራዊ ዕሳቤ የተቃኘ፣ ከሀገራዊ እሴት የተቀዳ መሆኑን አመልክተው፤ በሁሉም ተቋማት ገቢራዊ የሚደረግ ነው ብለዋል።
‎ሪፎርሙ በሦስት ምዕራፎች ሲከፈል የተሻለ አፈፃፀም፣ መካከለኛና ወደኋላ የቀሩትን በመለየት መሆኑን አንስተው፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግቦ በግልጽ ተመርጧል ነው ያሉት።

‎የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ በሶስት ምዕራፍ የተለየበት ሌላው መንገድ ተቋማት ከመጀመሪያዎቹ ልምድ እየወሰዱ በተሻለ መፈፀም እንዲችሉ ለማድረግ ነው ብለዋል።

‎ሂደቱ በሰባቱ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ምሰሶዎች አኳያ የሚታይ በመሆኑ ተቋማት ተግባራዊ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
‎በዘመናት መካከል የፀና ተቋም የመገንባት ዓላማ የያዘውን ሪፎርም በሂደት ማሻሻልና ማሳለጥ ይገባል ብለዋል።

‎በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ ተቋማት ወደ ትግበራ፣ ሁለተኛ ምዕራፍ ላይ ያሉት ደግሞ ወደ ዝግጅት በፍጥነት መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

‎ለሪፎርሙ ስኬት ምቹ የሥራ ቦታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ የሰራተኛው ምዘና ከሥራው ዓይነትና ባህርይ ጋር የተጣጣመ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

‎ተቋማት የሰራተኞችን አቅም ለመለየት፣ ለመመዘንና ለማብቃት የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሚከተለው አሰራር ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

‎በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምዘና ወቅት ስራውን በአግባቡ ሳይረዳ የሚሰራ ባለሙያ እንዳለ ጠቅሰው፤ ምዘናው የሰራተኛውን ጉድለቶች ለይቶ መሙላት ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት ብለዋል።

‎ምንጭ፡-የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን :

የአርባምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጨንቻ ሆስፒታል ደረጃ ማሻሻያ ወቅት ሆስፒታሉን በመድሃኒት ድጋፍ ለማድረግ የገቡትን ቃል የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አዳነ አልቶ በተገኙበት በዛሬው ዕለት አስረከቡ።‎...
14/11/2025

የአርባምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጨንቻ ሆስፒታል ደረጃ ማሻሻያ ወቅት ሆስፒታሉን በመድሃኒት ድጋፍ ለማድረግ የገቡትን ቃል የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አዳነ አልቶ በተገኙበት በዛሬው ዕለት አስረከቡ።

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከ 64 ዓመታት በኋላ ሐምሌ 5/2017ዓ.ም ወደ አጠቃላይ ሆስፒታል ማደጉ የምታወስ ሲሆን በዝሁ የማብሰርያ ፕሮግራም ወቅት በተካሄደ የድጋፍ መርሃ ግብር ወቅት የአርባምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተቋሙን በመድሃኒት እንደምደግፉ የኮሌጁ ዲንና የጨንቻ አጠቃላይ ሆስፒታል የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር አዳነ አልቶ መግለፃቸው የምታወስ ነዉ።

‎በዛሬዉ ዕለት ዶ/ር አዳነ አልቶ ቃል የገቡትን የ 200,000 ብር መድሃኒት በአካል ተገኝተዉ ለሆስፒታሉ ማኔጅመንት አካላት አስረክበዋል።

‎በስተመጨረሻም ዶ/ር አዳነ እንደገለፁት የገባነዉን ቃል ተግባራዊ አድርገናል ሌሎችም በወቅቱ ቃል የገቡ ተግባራዊ እንድያደርጉ ገልፀው በቀጣይ ኮሌጃቸዉ ከሆስፒታሉ ጎን በመሆን አስፈላጊዉን ድጋፍ እንደምያደርጉ ገልፀዋል ።

‎የጨንቻ አጠቃላይ ሆስፒታል የማኔጅመንት አካላት ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በገባዉ ቃል መሰረት ድጋፍ በማድረጋቸዉ አመስግነዉ ሌሎች ተቋማትና ግለሰቦችም የገቡትን ቃል ተግባራዊ እንድያደርጉ ጥሪያቸዉን አስተላልፈዋል ።

በጋሞ ዞን የሠላም በር ከተማ አስተዳደር የወባ በሽታ ፣ የማህፀን ጫፍ እና የጡት ካንሰር መከላከልና መቆጣጠር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 4/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ...
14/11/2025

በጋሞ ዞን የሠላም በር ከተማ አስተዳደር የወባ በሽታ ፣ የማህፀን ጫፍ እና የጡት ካንሰር መከላከልና መቆጣጠር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 4/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ወባ በሽታን ጨምሮ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን የአከባቢያችንን ንጽሕና በመጠበቅና አልጋ አጎበርን በመጠቀም በቀላሉ መከላከል እንደሚቻል የገለፁት የሠላምበር ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ባራና በዘመቻ በሚካደው የወባ በሽታ መከላከል ሥራ ሀለሉም ባለድርሻ አካላት በንቃት ልሳተፋ ይገባል ብለዋል።

‎አከባቢያችን ቆላማ እንደመሆኑ መጠንና በዞን ደረጃም ትኩረት ከሚሹ አከባቢዎች አንዱ ሆኖ መለየቱን ያነሱት አቶ ታምራት ባራና ንቅናቄ ሥራው በኮማንድፖስት እንደሚመራና ያለበት ደረጃ እየተገመገመ የበሽታው ስርጭት ያለበት ደረጃ ያለበት መሻሻል ሪፖርት የሚደረግ ይሆናል ብለዋል።

‎በቅርቡ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ለሁሉም ነዋሪዎች አልጋ አጎበር ስርጭት ያደረገ ቢሆንም የአጠቃቀም ጉድለት እንዳለ መለየታቸውን አቶ ገትነት ጋንታ የሠላምበር ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ በንግግራቸው ያነሱት።

‎ወባን፣ የማህፀን በር ካንሰርንና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በህክምናና አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ መከላከል እንደሚቻል ያነሱት የጽ/ቤቱ ኃላፊ ገዳይ የሆኑ እነኚን በሽታዎች ቀድሞ በመከላከልና ህክምና በመከታተል ልንከላከላቸው ይገባናል ብለዋል።

‎በሠላምበር መጀመሪያ ደረጃና ጤና ጣቢያ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ከሰኞ እስከ አርብ ነፃ ምርመራና ህክምና እንዳለ የጠቆሙት የሠላምበር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራአስኪያጅ ዶ/ር አሻ ደረሰ በየሰፈሩ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን መስጠት እንዲሁም ክትትልና ቁጥጥር ሥራ በደምብ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

‎ወባንና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ቀድመው ከመከላከል አንጻር ጉድለቶች እንዳሉ አስተያየታቸውን የሰጡት የመድረኩ ተሳታፊዎች በንቅናቄ በሚሰራው የወባና ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከያ ሥራ በንቃት በመሥራት በአጭር ጊዜ ለውጥ ልናመጣ ይገባናል ብለዋል።

‎በመድረኩ የወባ በሽታንና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከልን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተሰርቷል።

‎በሌላ በኩል ምንነቱ ያልታወቀና በንኪኪ በቀላሉ በመተላለፍ የሰውን ህይወት እያጠፋ ያለው ቫይራል ሄመሬጅክ ፌቨር(VHF) በሽታ በሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ በመከሰቱ ሁሉም የከተማው ነዋሪ ጥንቃቄ እንድያደርግ ጽ/ቤቱ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል።

የክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት በአርባ ምንጭ ማዕከል ባካሄደው 2...
13/11/2025

የክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት በአርባ ምንጭ ማዕከል ባካሄደው 25ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎቸ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው በወቅታዊ አስቸኳይ የጤና ጉዳይ በተመለከተ አጀንዳው ላይ ሲሆን፤ በዚህም በክልሉ በጅንካ ከተማ በተከሰተው ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ባለው የሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ (Hemorrhagic Fever) ዙሪያ በመምከር ስርጭቱን ለመግታት እንዲሁም ሰብዓዊና ማህበራዊ ቀውስ እንዳያስከተል ለመቆጣጠር የሚያስችል ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

የክልሉ መንግስት በጤናው ዘርፍ ከፌዴራል መንግስት እና ከአጋር አካላት ጋር ጥራት ያለው ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽትን ለማስፋት በማድረግ ላይ ካለው ጥረት ባለፈ፤ የጤና አደጋዎች እንዳይከሰቱ የመከላከልና ከተከሰተም በአፋጣኝ ምላሽ የመስጠት ስራዎች እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በጅንካ የበሽታውን መከሰት ያመላከቱ የቅኝት መረጃዎች መገኘት ተከትሎ ከፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ጋር አፋጣኝ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ ወደ ተግባር መገባቱም የተገለጸ ሲሆን፤ በሽታው ሰብዓዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ በማስከተል የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል ፈጣን ምላሽ ሰጪ ግብረ ሀይል ተቋቁሞ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ላይ መሆኑ ተመልክቷል።

አሁን ላይ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ንኪኪ የነበራቸውን ግለሰቦች በመለየት በጊዜያዊ ለይቶ ማቆያ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ከመሆኑም ባለፈ፤ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠርና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያስከትል ለመከላከል የክልሉ መንግስት የፈጣን ምላሽ መስጫ ማዕከል ጅንካ ላይ ተቋቁሞ ከፌደራል ድንገተኛ በሽታ የመከላከል ቡድን ጋር የተቀናጀ ተግባራት በማከናውን ላይ መሆኑ ተገልጿል።

ምክር ቤቱ ህብረተሰቡ በሽታው በቀላሉ በንኪኪ የሚተላለፍ መሆኑን በመገንዘብ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ያሳሰበ ሲሆን፤ በየጊዜው በሽታውን የተመለከተ አስፈላጊ መረጃ በፌደራል ጤና ሚንስቴር በኩል ብቻ የሚሰጥ መሆኑን አስታውቋል፡፡

መስተዳደር ምክር ቤቱ በተጨማሪም በክልሉ በበጀት አመቱ በየዘርፉ የተጣሉ የሰላም፤ የልማትና የመልካም አስተዳደር ግቦችን በህዝቡ ግንባር ቀደም ተሳትፎ የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ ለላቀ ውጤት ለማብቃት በሁሉም ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጿል፡፡

በዚህ ረገድ በተለይ የሰላምና ፀጥታ ተግባራትን በማጠናከር የክልሉ መለያና መገለጫ የሆነው የሰላም ተምሳሌትነትን የማስቀጠል፥ የገቢ መሰረቶችን በማስፋት የውስጥ ገቢን የማሳደግ፤ አላስፈላጊ የወጪ ቅነሳና የበጀት አጠቃቀም፤ መሶብ የአንድ መስኮት አገልግሎት አሰጣጥን የማስፋት እንዲሁም በንቅናቄ የሚከናወኑ ተግባራትን የማጠናከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

መስተዳድር ምክር ቤቱ በተጨማሪም ሌሎች የካቢኒ ውሳኔ የሚሹ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ስብሰባውን አጠናቋል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

የጡት ካንሰር - ይወቁ፣ ይቅደሙ!1.  የጡት ካንሰር ምንድን ነው?የጡት ካንሰር በጡት ውስጥ ያሉ ሕዋሶች ባልተለመደ መልኩ ሲራቡና ሲያድጉ የሚከሰት በሽታ ነው። የጡት ካንሰር በኢትዮጵያ የተ...
13/11/2025

የጡት ካንሰር - ይወቁ፣ ይቅደሙ!

1. የጡት ካንሰር ምንድን ነው?

የጡት ካንሰር በጡት ውስጥ ያሉ ሕዋሶች ባልተለመደ መልኩ ሲራቡና ሲያድጉ የሚከሰት በሽታ ነው። የጡት ካንሰር በኢትዮጵያ የተስፋፋ ያለ የካንሰር ዓይነት ሲሆን፣ ከሁሉም የካንሰር አይነቶች የጡት ካንሰር ታማሚዊች 32% ይዞ ይገኛል።

መረጃዎች እንደሚያሣዩት በየዓመቱ 16,000 በላይ አዲስ የጡት ካንሰር ታማሚዎች በኢትዮጲያ ይመዘገባሉ። ከ70% በላይ ሴቶችም በሽታው የመጨረሻ ደረጃ ወይም ስር ከሰደደ በሁዋላ ወደ ጤና ተቋም ስለሚመጡ የህክምናው ዉጤት ዉስብስብ እና ዝቅተኛ ያደርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ አብዛኛው ሴቶች የጡት ካንሰር ግንዛቤ ስለሌላቸዉ የምርመራ እና የሕክምና አገልግሎቶች ለማግኘት የተገደቡ ናቸው።

2. የጡት ካንሰር በምን ይከሰታል?

የጡት ካንሰር አንድ የተለየ መንስኤ ባይኖረዉም ፤ መከላከል የምንችላቸዉ እና የማንችላቸዉ ነገሮች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ።

3. መነሻ ምክንያቶች

• በቤተሰብ የነበረ ታሪክ ወይም የተወረሰ ዘረመል
• የመጀመሪያ የወር አበባ ቀደም ብሎ መጀመር ወይም ለማረጥ መዘግየት እና እድሜ መጨመር
• የመጀመሪያ እርግዝናን ከ30 ዓመት በኋላ ሲሆን እና አለማጥባት
• ወፍረት፣ በተለይ የወር አበባ ከተቋረጠ በኋላ
• አልኮል መጠጣት ወይም ማጨስ
• ቀደም ብሎ በደረት ላይ የተደረገ የጨረር ሕክምና ጋር ተያይዞ መኖር መንስኤዎች ሊሆኑ ይችላሉ።

4. ምልክቶች — ከሚከተሉት አንዱን ካዩ ወደ ጤና ባለሙያ ይሂዱ!

• በጡት ወይም በእጅ ትከሻ ስር የተለየ እብጠት ወይም መጠጠር
• የጡት መጠን ወይም ቅርፅ መቀየር
• የቆዳ መቅላት ወይም መንቀጥቀጥ
• የጡት ጫፍ ወደ ውስጥ መግባት ወይም ደም የያዘ ፈሳሽ መውጣት
• በጡት ውስጥ በአንድ ቦታ የማያቆም ህመም መሰማት ምልክቶች ናቸው።

5. በቀላሉ ራስዎን መፈተሻ መንገድ

1. በመስታወት ፊት ቆሞ ትከሻዎን ቀጥ በማድረግ እና እጆችዎን በወገብ ላይ አድርገው ጡቶችዎን ይመልከቱ። የቆዳ መቆጣት እና የጡት መጠን ለውጦች ይመልከቱ። እጆችዎን ወደ ላይ ቀጥ አድርገው ያንሱ እና ለውጦችን ይመልከቱ።
2. በተጨማሪ አንድ እጅዎን በማንሳት በሌላኛው እጅዎ በመካከለኛው 3 ጣቶች ክብ እንቅስቃሴ በማደረግ ከጡትዎ የውጨኛ ክፍል ጀምረው እስከ ጫፉ ድረስ ይመርምሩ። እጅዎን በመቀያየር ሁለቱንም ጡቶች ተኝተው አልያም ቆመው መመርመር ይችላሉ።

6. ምርመራ

• ከላይ የተጠቀሱ ምልክቶችን ካስተዋሉ እና የተለየ ለውጥ ካገኙ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ምርመራ ያድርጉ።
• የጡት ካንሰር ምርመራ በሰለጠነ የጤና ባለሙያ በተመረጡ ጤና ተቋማት ይሰጣል።
• የጡት ካንሰር ምርመራ እንደ አስፈላጊነቱ አልትራሳውንድ ወይም ማሞግራፊ ጨምሮ ፓቶሎጂ ምርመራዎችን ያጠቃልላል።

7. ሕክምና

የጡት ካንሰር ህክምና የተለያዩ አማራጮች አሉት
• ቀዶ ጥገና፣ ኬሞቴራፒ፣ የሆርሞን እና የጨረር ሕክምና

8. ተጋላጭነትን ለመቀነስ መደረግ ያለባቸው ነገሮች

• ክብደት መቆጠጠርና አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ
• አልኮልን መቀነስ እና አለማጨስ
• በተቻለ መጠን በወሊድ ወቅት ማጥባት
• በቤተሰብ ውስጥ የበሽታው ታሪክ ካለ ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ምርመራ ማድረግ
• ማንኛውም ለውጥ በሚኖርበት ጊዜ ቀደም ብለው ህክምና ምርመራ ያድርጉ — ቀድሞ ከተገኘ የመዳን እድሉ ከፍተኛ ስለሆነ

9. መቼ ወደ ህክምና ተቋም መሄድ አለብዎት

ያልተመደ እብጠት ወይም መጠጠር፣ የቆዳ ለውጥ፣ የጡት ጫፍ ለውጥ ወይም የጡት ህመም ሲያጋጥምና ምልክቶቹ ከጥቂት ሳምንታት በላይ ከቆዩ በአፋጥኝ ወደ ጤና ተቋም መሄድ ይገባል፡፡

13/11/2025
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የህፃናት የጉበት ቫይረስ መከላከያ ክትባት (Hepatitis B Birth Dose) ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡‎‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 4/2018 ዓ....
13/11/2025

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የህፃናት የጉበት ቫይረስ መከላከያ ክትባት (Hepatitis B Birth Dose) ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

‎አርባ ምንጭ፡- ህዳር 4/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ አዲስ ለሚወለዱ ህጻናት የጉበት ቫይረስ መከላከያ ክትባት (Hepatitis Birth Dose) እና (Measles 5 dose) ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት መጀመሩ ታውቋል፡፡

‎የስልጠና መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ አጥናፉ አበራ በመልዕክታቸው እንደ ሀገር ብሎም እንደ ዞን የጉበት በሽታን ለመቀነስ እና አስቀድሞ ለመከላከል ህጻናት እንደተወለዱ ክትባቱ እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል፡፡

‎አክለውም Hepatitis B የተባለው የጉበት ቫይረስ ከሰው ወደ ሰው ተላላፊና ለጉበት ካንሰር ተጋላጭ በማድረግ ገዳይ የሆነ በሽታ በመሆኑ ይህንን ቫይረስ አስቀድሞ መከላከል እንዲቻል በአጭር ጊዜ ክትባቱን ለህጻናት ለማስጀመር ስልጠናው አጋዥ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎የኩፍኝ ክትባትን ከ10 ዶዝ ወደ 5 ዶዝ መቀየርን አስመልክቶ አቶ አጥናፉ እንደተናገሩት፤የመድሀኒት ብክነትን በመፍራት በቀጠሮ ቀናቸዉ ክትባት ሳይወስዱ የሚቀሩ ህፃናት ወቅቱን ጠብቀዉ እንዲወስዱ በማድረግ ሊከሰት የሚችለውን የኩፍኝ ወረርሽኝን ለመከላከል እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡

‎ስለሆነም የተገኘውን ግብዓት በአግባቡ በመውሰድ እና የክትባት ጥራትን በማረጋገጥ አስፈላጊውን ምላሽ በመስጠት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ የህፃናት የጉበት ቫይረስ ምንነት መከላከያ መንገዶች፣የክትባቱ አጀማመርን፣የኩፋኝ ክትባት ከዚህ ቀደም ከነበረዉ 10 ዶዝ ወደ 5 ዶዝ መቀየር ፣ የክትባት መረጃ ጥራት ማሻሻያ ተግባራት ዙሪያ በዘርፉ ከፍተኛ ባለሙያዎች አማካይነት ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።

‎በስልጠናው ላይ ከሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር የጤና ጽ/ቤቶች ኃላፊዎች፣ የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪዎች፣ ከሁሉም ሆስፒታሎች የሆስፒታል አመራር አካላት እና የእናቶችና ሕፃናት ኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram