Benishangul Gumuz Health Bureau

Benishangul Gumuz Health Bureau ጤንነቱ የተጠበቀ ዜጋ እናፍራ
(1)

በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህጸን መንሸራተት ነጻ የህክምና አግልግሎት በዘመቻ እየተሰጠ መሆኑን የቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ። ‎‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች ...
21/11/2025

በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህጸን መንሸራተት ነጻ የህክምና አግልግሎት በዘመቻ እየተሰጠ መሆኑን የቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች እና ህጻናት ጤና ባለሙያ ወ/ሮ ወርቅነሽ አሰጌ በዘመቻ መርሃ ግብሩ እንዳሉት፥ የማህጸን መውጣት በአንዳንድ እናቶች ላይ የሚታይ የጤና ችግር ነው።

በሽታውን ለማከም ከፍተኛ የሙያተኛ አቅም እና ግብዓቶች የመጠይቅ እንደሆነ የጠቁሙት ባለሙያዋ
ቢሮው ከጎንደር ዩኒቨርሲቲና ከዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ዘመቻውን እያካሄደ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በመጀመሪያ ዙር 15 የዘመቻ ቀናት ከ60 በላይ እናቶችን በሆስፒታሉ ማከም መቻሉን የገለጹት ወ/ሮ ወርቅነሽ ድርጅቱ ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።

ከአከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ችግሩ አሳሳቢ ነው ያሉት ወ/ሮ ወርቅነሽ በቀጣይም በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገው እንቅስቃሴ ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማህጸንና ጽንስ ህክምና ስፔሻለስት ዶ/ር አለሙ ተሻለም፤ የማህጸን መውጣት በስፋት በወልድ ወቅት በእናቶች ላይ የሚከሰት መሆኑን አብራርተዋል።

ከፍተኛ ህመምን የሚያስከትል መሆኑንም ጠቅሰው ከግንዛቤ እጦት የተነሳ ለረጅም ጊዜ ብዙዎቹ በህመሙ እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል፡፡

የክልሉ ጤና ቢሮው ያቀረበላቸውን ጥሪ ተከትሎ በመርሀ ግብሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እናቶችን በጥንቃቄ በማከም ጤንነታቸውን መመለስ መቻላቸውንም አስረድተዋል፡፡

የዊንግ ኦፍ ሂሊንግ ግብረ ሰናይ ድርጅት አስተባባሪ ዶ/ር ቃልኪዳን ይታየው በበኩላቸው የማህጸን መንሸራተት የደረሰባቸው እናቶች ህክምና አግልግሎቱን አገኝተው ሙሉ ጤንነታቸው እንድመለስ ከመስራት ባለፈው በዘርፉ ብቁ ሙያተኞችን ለማፍራት የሚደረግ የዘመቻ መርሀ ግብር መሆኑን አንስተዋል፡፡

ያለአቻ ጋብቻ እና የተለያዩ የስራ ጫናዎች የማህጸን መንሸራተትን ሊያስከትሉ እንደሚችሉም የሚናገሩት ዶ/ር ቃልኪዳን ሽንት እና ሰገራን ያለመቆጣጠር፣ በዳሌ እና በወገብ አከባቢ ከፍተኛ የህመም ስሜት መኖር ከበሽታው ምልክቶች መካከል እንደሚጠቀሱም አሳውቀዋል፡፡

የህክምና አግልግሎቱን የሚያገኙ እናቶችም ህመሙ እስኪሻላቸው ድረስ አስፈላጊው ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውም ጠቁመው ሌሎችም ወደ ህክምና መስጫ ተቋማት በመምጣት የአግልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።

የበሽታው ህመም እጅግ ከባድ እና ቤተሰብን እስከመበተን የሚያደርስ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ህክምናውን ሲከታተሉ ያገኘናቸው ታካሚዎችና የታካሚ ቤተሰቦች ናቸው ፡፡

ታካሚዎቹ ለተመቻቸላቸው ነጻ የህክምና አግልግሎትም ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የቤንሻንጉል ሚድያ ዘገባ ያመላክታል።

በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች ከታህሳስ 3-6/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ እንዲሳካ የአጋር ድርጅቶች ድርሻ የጎላ መሆኑን ተገለጸ። የክልሉ ጤና ቢሮ የዘመቻው ...
21/11/2025

በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች ከታህሳስ 3-6/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ እንዲሳካ የአጋር ድርጅቶች ድርሻ የጎላ መሆኑን ተገለጸ።

የክልሉ ጤና ቢሮ የዘመቻው ቅድመ ዝግጅት ላይ ከተለያዩ ድርጅት ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ከታህሳስ ወር መግቢያ ጀምሮ ለሚካሄደው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የታለመውን ዕቅድ እንዲሳካ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ አስገንዝበዋል።

ሀላፊው አክለውም ከዚህ ቀደም አጋር አካላት የሚያደርጉትን እገዛ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው በዚህ ዘመቻ ይህንን አጠናክሮ እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።

በአራተኛ ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆኑ ህጻናት ተጠቃሚ የሚሆኑ ሲሆን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ከወዲሁ እየተሰራ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ባሻገር በመተከል ዞን የተከሰተው የኮሌራ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር በሚቻልበት ዙሪያ እንዲሁም እንደ ሀገር የተከሰተው የማርበርግ ቫይረስ ዙሪያ በክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ መብራቱ በጉኖ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የዕለቱ መልዕክት!!
21/11/2025

የዕለቱ መልዕክት!!

የክልሉ ጤና ቢሮ የአደጋ  ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ  በክልሉ እንዳይከሰት የቅድመ መከላከልና መቆጣጠር ስራ እየሰራ መሆኑን አሳወቀ። የክልሉ ጤና ቢሮ የኦፕሬሽን ...
20/11/2025

የክልሉ ጤና ቢሮ የአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በክልሉ እንዳይከሰት የቅድመ መከላከልና መቆጣጠር ስራ እየሰራ መሆኑን አሳወቀ።

የክልሉ ጤና ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ በወቅታዊ የጤና ጉዳይ ላይ በክልሉ ለተቋቋመው የአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በNovember 14/2025 መከሰቱ በላቦራቶሪ ማረጋገጡን ያስታወሱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው የክልሉ ጤና ቢሮ የተቀናጀ የአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ማእከላትና የህክምና ተቋማትን እንዴት ማቋቋምና ማጠናከር እንዳለበት በውይይቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

እንደ ም/ቢሮ ኃላፊው ገለጻ ክልሉ ከሱዳን ጋር ድንበር በመሆኑ በክልሉ ብዛት ያላቸዉ ስደተኞች መኖራቸው ብዛት ያላቸው የድንበር መሻገሪያ በሮች መኖራቸው በተጨማሪም በክልሉ በመአድን ቁፉሮ ምክንያት ከፍተኛ የሰዎች ፍሰት መኖሩ የስጋት ቀጠና ውስጥ በመሆናችን የክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫና የቅኝትና ቁጥጥር ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመግለፅ በሀገር ውስጥና በድንበር አከባቢ መግቢያ እና መውጫ ቦታዎች ላይ የጤና ምርመራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ኃለፊው አሳስበዋል።

ምልክቶቹ ከፍተኛ ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ እና ደም መፍሰስ ሲሆኑ የበሽታው ምልክት የታየበት ማንኛውም ሰው ወደ ጤና ተቋም መሄድ ወይም በነፃ የስልክ መስመር 6016 መደወል አለበት።

ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ማህበረሰባችንን ለመጠበቅ የቅድመ ስራዎች እየተሰራ ነው ያሉት የቤ/ጉ/ክ/መ/ ጤና ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ ህብረተሰባችን ቀደም ሲል የተጠቀሱትን የመከላከያ እርምጃዎችን መከተል እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

በበየነ መረብ በተካሄደው በዚህ ውይይት ላይ የክልሉ የሁሉም አከባቢዎች የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎችና የስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማዘመንና የተሻለ የጤና  አገልግሎት  ለማህበረሰብ እንዲሰጥ የተጀመረዉ የማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክት አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተገለጸ።**********...
16/11/2025

የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማዘመንና የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ እንዲሰጥ የተጀመረዉ የማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክት አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተገለጸ።
************
( የቡለን ህዳር 7/2018 ዓ/ም ) በአንደኛ ምዕራፍ በህብረተሰብ ተሳትፎ ፕሮጀክት የተሰራዉን የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አፈጻጸም በባለድርሻ አካላት በመገምገም የቀጣይ ሁለተኛ ምዕራፍ ስራ ለማስጀመር አቅጣጫዎች ተቀምጧል ።

የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ እና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ነመራ ማሩ የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ እንዲሰጥ በቦርድ አባላት ዉሳኔዎችን በማስተላለፍና ኮሚቴዎችን በማዋቀር ስራ ዉስጥ በመግባት ዉጤታማ ስራዎች መስራታቸዉ ገልጿል ።

አቶ ነመራ ማሩ አክለዉም በአንድነትና በትብብር መንፈስ የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማዘመንና ለህዝብ በሚመጥን መልኩ የተሰራዉን ስኬታማ ስራዎችን ለሁለተኛ ምዕራፍ ስራ አጠናክሮ በማስቀጠል ሆስፒታሉን ወደ የተሻለ ደረጃ ማሻገር እንዳለበት አቶ ነመራ ማሩ አሳስበዋል ።

የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራአስኪያጅ አቶ ንጋቱ ወየሳ ለማህበረሰብ የተሻለ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ምቹ ሁኔታዎች ወሳኝ በመሆናቸዉ ማህበረሰብ አቀፍ የልማት ድጋፍ ፕሮጀክት በመንደፍና የተለያዩ ኮሚቴዎችን በማዋቀር እንዲሁም ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ ስራዎችን በመስራት የተሻለ ተቋም ለመገንባታ የተቻለ መሆኑን ገልጿል ።

በማህበረሰብ ተሳትፎ ፕሮጀክት በአንድኛ ምዕራፍ ከከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ በመሰብሰብ የሆስፒታሉን ካርድ ክፍል ፣ የእናቶችና ህጻናት ክፍል ፣ የመዳሃኒት ክፍል ፣ የቲቪ ህመማን ክፍል ፣የአስተዳደር ክፍል እና ሌሎችን ዘርፎችን በተሻለ ደረጃ ለማህበረሰብ የጤና አገልግሎት እንዲሰጡ የተደረገ ሲሆን ይህ ዉጤታማ ስራ ተግባራ ለሰራተኞች ምቹ የስራ ሁኔታ ከመፍጠር በተጨማሪ ሆስፒታሉን ከሌሎች ሆስፒታሎች ጋር ተወዳደሪ እንዲሆን የተደረገ ስኬታማ ስራ መሆኑን የሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ አቶ ንጋቱ ወየሳ ገልጿል ።

የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማዘመንና የተሻለ የጤና አገልግሎት እንዲሰጥ የተሰራዉ ዉጤታማ የማህበረሰብ ተሳትፎ ድጋፍ ስራዎች በሁለተኛ ምዕራፍ አጠናክሮ በማስቀጠል ሆስፒታሉን ወደ የተሻ ደረጃ ለማሻገር የተለመደዉ ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቶ ንጋቱ ወየሳ አሳስበዋል ።

የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የማዘመን እና የተሻለ የጤና አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመ የገቢ አሰባሰቢ ኮሚቴ ሰብሳባ አቶ ገዛህኝ ሻንበል የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተሻለ አገልግሎት እንደሰጥ የማህበረሰብ ንቅናቄ ስራዎችን በመስራትና ከወረዳ ማዓከል እስከ ቀበሌ ማህበረሰብ ግንዛቤ በመፍጠር አንድ ሚሊዮን ሰማኒያ ሽህ ብር በመሰብሰብ ሆስፒታሉ የተሻለ የጤና አገልግሎት እንዲሰጥ በማህበረሰብ አቀፍ ተሳትፎ ፕሮጀክት የተሰራ ሲሆን የተመጀረዉ የማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጀክት ድጋፍ በሁለተኛ ምዕራፍ አጠናክሮ በማስቀጠል ሆስፒታሉን ወደ የተሻለ ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጠዉ መስራት እንደሚጠበቅ አቶ ገዛህኝ ሻንበል አሳስበዋል ።

በሪፖርት ግምገማዉ PUi ኢንተርናሽናል ድርጅት 550,ዐዐዐዐ ብር ወጪ የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የእናቶችና የህጻናት አንቡላንስ ጥገና በማድረጉ የምስጋና እና የዕዉቅና ሰርቲፊኬት በመስጠትና በአንደኛ ዙር በማህበረሰብ ተሳትፎ ፕሮጀክት የተሰራዉን የቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ክፍሎችን ጉብኝት በማድረግ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል መረጃው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ነው

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች እና መከላከያ ዘዴዎችአዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus Disease) በወረርሽኝ ...
16/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች እና መከላከያ ዘዴዎች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus Disease) በወረርሽኝ መልክ የሚከሰት የደም መፍሰስና ትኩሳት ህመም ሲሆን በሰዎችም ሆነ በሌሎች እንስሳት ላይ ይከሰታል።

የበሽታው ምልክቶች ለቫይረሱ በተጋለጥን ከ2 እስከ 9 ባሉት ቀናት ውስጥ የሚታዩ ሲሆን፤ ምልክቶቹ:-

👉 ከአፍ፣ ከአፍንጫ ወይም ከቆዳ ስር ደም መፍሰስ፣

👉 ከፍተኛ ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ ማለት እና ራስ ምታት፣

👉 የጡንቻ እና የጀርባ ህመም፣

👉 ማቅለሽለሽ፣ የሆድ ህመም እና ተቅማጥ፣

👉 ደረት፣ ጀርባ እና ሆድ ላይ በጣም ጎልቶ የሚታይ ሽፍታ ናቸው።

የበሽታው መተላለፊያ መንገዶች

👉 ከበሽተኛ ደም፣ ሽንት፣ እንባ እና ሌሎች ፈሳሾች ጋር የሚፈጠር ቀጥተኛ ንክኪ፣

👉 በታመመ ወይም በሞተ ሰው የሰውነት ፈሳሽ የተበከሉ ቁሶች (እንደ ልብስ፣ አልጋ ልብስ፣ መርፌ እና ሌሎች መገልገያዎች) ጋር በሚኖር ንክኪ፣

👉 በተጨማሪ በበሽታው ከተያዙ የሌሊት ወፎች ወደ ሰዎች ይተላለፋል።

የበሽታው መከላከያ መንገዶች

👉 የተዘረዘሩት ምልክቶች ሲኖሩ ወደ ህክምና ተቋም መሄድ፣

👉 ከታመመ ሰው ጋር ንክኪ ካለዎት እና ትኩሳት ካለ በአፋጣኝ ወደ ጤና ተቋም መሄድ፣

👉 ሞት በሚከሰትበት ጊዜ አስከሬኑን በባለሙያ ማዘጋጀት እና መቅበር፤ አላስፈላጊ የቀብር ሥነ ሥርዓቶችን ማስቀረት እና ንክኪ ያላቸውን ቁሶች ማስወገድ፣

👉 ከታመመ ሰው ደም እና ፈሳሽ ንክኪ ራስን መጠበቅ፣

👉 ለታመመ ሰው እንክብካቤ በምናደርግበት ጊዜ የመከላከያ ዘዴዎችን ማለትም የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ማስክ እና የእጅ ጓንት መጠቀም፣

👉 እጅን በሳኒታይዘር ወይም በሳሙናና በውሃ በአግባቡ መታጠብ እንደሚገባ የጤና ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል።

በ2030 ትኩረት  የሚሹ ሀሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል  የተያዘውን  ሀገራዊ ግብ ለማሳካት  መንግታዊ  ያልሆነ  ድርጅቶች  እያደረጉት  ያለዉ እገዛ  ተጠናክሮ  መቀጠል  እንደአለበት  የቤ...
15/11/2025

በ2030 ትኩረት የሚሹ ሀሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት መንግታዊ ያልሆነ ድርጅቶች እያደረጉት ያለዉ እገዛ ተጠናክሮ መቀጠል እንደአለበት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ገለፀ ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር ካርተር ሴንተ ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም በክልሉ የተከናወኑ ተግባራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ በመንግስት በ2030 ትኩረት የሚሹ ሀሩራማ በሽታዎችን ለማጥፋት እንደሀገር የተያዘውን ግብ ለማሳካት መንግስታዊ ያልሆነ ድርጀቶች እያበረከቱ ያሉት እገዛ አበረታች በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

በተለይም ካርተር ሴንተር ኢትዮጵያ በክልሉ በመተከል ዞን ሁሉም ወረዳዎች የፎኬትና ተላላፊ የሆነ የዝሆነ በሽታዎችን ለመከላከል ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር ተቀናጅቶ የሰራቸው ሥራዎች እና የተመዘገቡ ዉጤቶች አበረታች እንደነበረ ምክትል ሀላፊዉ ገልፀው ፕሮጀክቱ ወደሌሎች የክልሉ ወረዳዎች መስፋፋት እንደአለበት አስገንዝበዋል ።

የካርተር ሴንተር ኢትዮጵያ ምክትል ሀላፊ አቶ የማነ ቀጀላ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በክልሉ በባለፉት ወራት ላስመዘገባቸዉ ስኬቶች የክልሉ መንግስት ድጋፍና ክትትል ከፍተኛ ድርሻ እንደነበረዉ ተናግረው ይህ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

የካርተር ሴንተር ኢትዮጵያ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር አለማየሁ አሰፋ ፕሮጀክቱ በ2017 ዓ.ም በማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት ዕደላ፣በአቅም ግንባታ ሥራዎች፣የጤና ሥርዓትን በማጠናከር ፣በፋይናንስ ፣በግብዓትነት እና በቴክኒክ እገዛ እና በበሽታው ዳሰሳ ቅኝት ዘርፌ ብዙ ተግባራት የተከናወኑ ቢሆንም በመድሀኒት አቅርቦት ምክንያት አንዳንድ ወደኋላ የቀሩ ተግባራት በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰሩ አስረድተዋል ።

በመድረኩ ላይ የክልል ፋይናንስ ቢሮ ምክትል ሀላፊ፣የጤና ሚኒስቴር የትኩረት የሚሹ ፕሮግራሞች አስተባባሪ፣ከካርተር ሴንተር ኢትዮጵያዊ ፣ከክልልና ከዞን የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል ።

የማህበረሰብን ግንዛቤ በማሳደግ እጅ የመታጠብ ልምድ ማዳበር ተላላፊ የሆኑ  በሽታዎችን ለመከላከል መሰረት መሆኑ  የጤና ቢሮ ገለፀ  ። እጅን በሳሙና በመታጠብ ብቻ 50% የተቅማጥ በሽታዎችን...
14/11/2025

የማህበረሰብን ግንዛቤ በማሳደግ እጅ የመታጠብ ልምድ ማዳበር ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል መሰረት መሆኑ የጤና ቢሮ ገለፀ ።

እጅን በሳሙና በመታጠብ ብቻ 50% የተቅማጥ በሽታዎችን 30% የመተንፈሻ አካል በሽታዎች እንዲሁም የተለያዩ ትላትሎች ሰውነታችን ውስጥ እንዳይገቡ እንደሚከላከልም ገልጿል።

ቢሮው ከቢልዲግሉ ወረዳ ጤና ጸ/ቤት ጋር በመተባበር የእጅ መታጠብ ቀን በቢልዲጊሉ ወረዳ ባምፄ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እጃችንን ዘወትር በአግባቡ በመታጠብ ተምሳሌት እንሁን! በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል።

በክልሉ ጤና ቢሮ የዋን ዋሽ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ግርማ ከበደ እለቱን አስመልክቶ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን እጅን በሳሙና መታጠብ በርካታ የጤና ጥቅሞች እንደሚሰጥ ገልጸው በተለይ
የሆድ ህመሞችን፣የመንተንፈሻ አካል በሽታዎችን፣እንዲሁም የተለያዩ ትላትሎች ወደ ሰውነታችን ውስጥ እንዳይገቡ ይከላከላል ብልዋል።

አቶ ግርማ አክለውም 80 በመቶ የሚሆኑ ተላላፊ በሽታዎች በንክኪ የሚተላለፉ በመሆናቸውና ዋነኛ አስተላላፊ የእጆቻችን ጣቶች በመሆናቸው ተማሪዎች የእጅ ንጽህና ለመጠበቅ በጤና ባለሙያዎች የሚሰጠውን ትምህርት በመተግበር ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን በማስተማር ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የድርሻቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።

የቢልዲጊሉ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ አብዱዛሂር በበኩላቸው የተቅማጥ በሽታ 2ኛው ዋነኛ የህፃናት ሞት ምክንያት በመሆኑ ዛሬ የእጅ መታጠብ ቀንን በት/ቤት ስናከብር ተማሪዎች የእጅ መታጠብን ባህል በማድረግ የራሳቸውንና የማህበረሰባቸውን ጤና እንዲጠብቁ ለማስቻል ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የእጅ መታጠብ ባህል በየአመቱ በሚከበረው የእጅ መታጠብ ቀን ሳይሆን የዘወትር ተግባራችን በመሆኑ በወሳኝ የእጅ የመታጠብ ጊዜያት እጅ የመታጠብ ባህልን ማዳበር ይጠበቅብናል ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የእጅ መታጠብ ቀንን አስመልክቶ የተለያዩ አስተማሪ እና አዝናኝ ድራማዎችና ጭዉዉቶች ቀርበዋል።

በመተከል ዞን የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር መንግስት ከሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ባሻገር መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶች ድርሻ የጎላ ሊሆን እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ። ቢሮው በመተ...
14/11/2025

በመተከል ዞን የጤና ስርዓቱን ለማጠናከር መንግስት ከሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ባሻገር መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶች ድርሻ የጎላ ሊሆን እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።

ቢሮው በመተከል ዞን በሚገኙ የጤናው ዘርፍ የአጋር ድርጅቶች ስራዎች ሪፖርት በግ/በለስ ከተማ ግምግማ አካሂደዋል።

በመተከል የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ጨምሮ ለሎች የጤና አገልግሎቶች ላይ መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር አካላት የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ ናቸው።

በዞኑ PUI ጨምሮ MCMDO,FIDO's,NRC,ZOA እና ለሎች አጋር ድርጅቶች የጤናው ዘርፍ በተለይ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ላይ የተለያዩ ስራዎች እንደሚሰሩ ባቀረቡት ሪፖርት ለመገንዘብ ተችለዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ በዚህ ወቅት እንዳሉት መንግስት የጤናውን ዘርፍ ለማሻሻል ከሚያደርገው ዘርፈ ብዙ ጥረት ባሻገር መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶች ክፍተቶችን በመቅረፍ ረገድ ትልቅ ድርሻ አላቸው ብለዋል።

አጋር ድርጅቶች ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ዘርፉን ሊያግዙ እንደሚገባ ያስታወቁት አቶ አለም እርስ በእርስ በመናበብና በመቀናጀት እንዲሁም የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት በወቅቱ በማድረግ ድጋፋቸውን አጠናክሮ እንዲቀጥሉም አሳስበዋል ።

የመተከል ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ታረቀኝ አርጌታ በበኩላቸው በዞኑ የተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ ምላሽ ለመስጠት እየተደረገ ባለው ጥረት አጋር አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡም አስገንዝበዋል ።

በዞኑ የሚገኙ አጋር አካላት ትኩረታቸውን በተለይ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥርና ምላሽ አሰጣጥ ላይ፣የስነ ንጽህና አገልግሎት ስራዎች ላይ፣በስርዓተ ምግብ ላይ እንዲሁም የማህበረሰብ ተሳትፎ ስራዎችን ላይ አቅምን በመገንባት በግብአትም ሆነ ሙያዊ እገዛዎችን በማድረግ ረገድ የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ።

በመድረኩ ላይ በዞኑ የሚገኙ አጋር አካላት የስራ ሪፖርት ቀርቦ ውጤታማ ውይይት ተደርጓል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

Alert letter
14/11/2025

Alert letter

  ምንድን ነው?‎‎ይህ በሽታ በቫይረስ የሚከሰት ከባድ የበሽታ ቡድን ነው ። በሽታው በመሰረቱ የደም መፍሰስን ወይም የደም መርጋትን በሰውነት ውስጥ የሚያመጣ ነው ። በርካታ የሰውነት አካላት...
14/11/2025

ምንድን ነው?

‎ይህ በሽታ በቫይረስ የሚከሰት ከባድ የበሽታ ቡድን ነው ። በሽታው በመሰረቱ የደም መፍሰስን ወይም የደም መርጋትን በሰውነት ውስጥ የሚያመጣ ነው ። በርካታ የሰውነት አካላትን በማጥቃት እና በሰውነት ውስጥ ያሉ የደም ሥሮችን የሚጎዳ ፣ በተለያዩ ቫይረሶች የሚመጣ በሽታ ነው።

#‎የበሺታው_መንስኤ እና የቫይረስ ዓይነት

‎. Ebola and ,Rift Valley Fever (RVF) & Yellow Fever ተብሎ የሚከፈል ሲሆን እንደ #ኢቦላቫይረስ ፣ #ደንጉ እና #የለውፊቨር የተባሉ ቫይርሶች የበሺታው መንስኤ ሲሆኑ #በትንኝ ንክሻም የሚመጡ ናቸው ።

‎ በሽታው ስሙ እንደሚያመለክተው በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም እንዲፈስ በማድረግ ለሞት የሚዳርግ ህክምና አልባ አደገኛ በሺታ ነው።

‎በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም መድማት እና መፍስሥ ከተከሰተ የበሽታው ከባድ ደረጃ ምልክት ነው።

‎በሽታው እንዴት ይተላለፋል?

‎1· ከተያዙ እንስሳት ጋር በመነካካት፡ በእንስሳት (ለምሳሌ አይጥ) ፣ ሽንት፣ ምራቅ ፣ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች በሚነካኩበት ጊዜ።
‎2· በነፍሳት ንክሻ፡
‎3· ከሰው ወደ ሰው፡ ከተያዘ ሰው የሚገኘው ደም፣ ምራቅ፣ የሰውነት ፈሳሾች ወይም ሌሎች ክምችቶች በቀጥታ በሚነካኩበት ጊዜ። ይህ ለበሽታው ከባዱ እና ዋነኛው ዓይነት የመተላለፊያ መንገድ ነው።



‎ምልክቶቹ በድንገት ሊታዩ እና በፍጥነት ሊባባሱ ይችላሉ። አንድ ሰው በቫይረሱ በተጠቃ ከ 2-21 ቀናት ውስጥ ምልክቶቹ መታየት ይጀምራሉ

‎መጀመሪያ ላይ የሚታዩ ምልክቶች፣‎ምልክቶቹን በሁለት ከፍሎ ማየት የሚቻል ሲሆን ‎የመጀመሪው ቀለል ያሉ ምልክቶች እና የመጨረሻው አደገኛ //አስጊ ደረጃ ላይ ሲደርስ የሚታዩ ናቸው።


‎· ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት (ትኩሳት)
‎· ድካም እና የመዛል ስሜት
‎· የጡንቻ፣ የአጥንት ህመም እና ቁርጥማት
‎· ራስ ምታት
‎· የጉሮሮ ህመም

‎ (በሽታው እየተባባሰ ሲሄድ)፡

‎· በቆዳ ስር ደም መውጣት
‎. ከአፍ፣ አፍንጫ፣ ከዓይን ወይም ከጆሮ ደም መፍሰስ።
‎· የጭንቅላት አዕምሮ መናጋት ፣ መደንገጥ፣
‎. ራስን መሳት ኮማ ውስጥ መግባት)
‎· የኩላሊት እና የጉበት መጎዳት እና ስራ ማቆም
‎· ከፍተኛ ድካም እና ሾክ/Shock
‎· የበርካታ አካላት አለመሥራት

‎እንዴት መከላከል ይቻላል ?

‎በሽታው በትንኝ ንክሻ አማካኝነት የሚተላለፍ በመሆኑ ነፍሶን ከሞት መታደግ ስለሆነ በአግባቡ ይጠቀሙት ። ከታማሚ ሰው ጋር ያልዎትን ንክክ መከላከል እና ‎አፋጣኝ አስፈላጊ የህክምና እርዳታ ማግኘት አስፈላጉ ሆኖ ፣በሺታውን ሙሉበሙሉ ማዳን የሚችል ህክምና የለም ፣
‎መከላከል ብቸኛው ቁልፍ መንገድ ነው !

‎ የሚከተሉትን ማድረግ ያስፈልግዎታል !!

‎1. እጆችዎን በንፅህና ይታጠቡ፡ በሳሙና እና በንጹህ ውሃ ዘወትር ማጠብ አስፈላጊ ነው።
‎2. ከሌሎች ሰዎች (ክምችቶች) ራስዎን ይጠብቁ፡ ከሰዎች ደም፣ ምራቅ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች ንክኪዎች ራስዎን ይጠብቁ። ይህ ለቤተሰብ አባላት እና በተለይም ለህክምና ባለሙያዎች እጂግ አስፈላጊ ነው።
‎ብዙ የህክምና/ጤ ና ባለሙያዎች ህይወታቸውን የሚያጡበት ወረርሺኝ ነው።
‎3. ከእንስሳት ይራቁ፣ አይጦችን እና ሌሎች እንስሳት ከቤትዎ አርቀው ያቆዩ። የሚታወቁ የእንስሳት ክምችቶች ባሉበት ስፍራ ጥንቃቄ አይለይዎት
‎4. ከነፍሳት ይጠበቁ ፣ አጎበር መጠቀም፡

MOH

ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት  ጤና ቢሮ የስነ ምግባር  መከታተያ ክፍል ገለፀ።የመንግሥት ሀብት ለታለመለት ዓላማ  እንዳይዉል...
13/11/2025

ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ መሆኑን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የስነ ምግባር መከታተያ ክፍል ገለፀ።

የመንግሥት ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዳይዉል ከሚያደርጉት መካከል ሙስናና ብልሹ አሠራር አንዱ ነው ።

ይህንን ለመከላከል በሁሉም ሴክተር መ/ቤቶች የስነ ምግባር መከታተያ መኮንኖችን በመመደብ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ሥራ እየሰራ ይገኛል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የስነ ምግባር መኮነን አቶ ሃምሳ አለቃ ቶሌሳ በቢሮ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚፈፀመዉን ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ ዳይሬክቶሬቶችን የመለየት እና የሙስናና ብልሹ አሰራር ቅድመ የመከላከል ሥራዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ስራዎች በመሰራት ላይ ነው ብለዋል።

ቢሮው ካለዉ የሥራ ባህር አኳያ በርካታ የፕሮጀክት ሥራዎች የሚሰሩበት በመሆኑ ለሥራ የሚመደቡ በጀቶች ለታለመላቸዉ ዓላማ እንዲዉሉ የክትትልና የድጋፍ ሥራዎች በመሰራት ላይ መሆናቸውን አቶ ሃምሳአለቃ ገልጸዋል ።

በመንግሥትም ሆነ በባለድርሻ አካላት የሚገነቡ ግንባታዎች ጥራታቸዉን ጠብቀው እንዲገነቡ ከቢሮ መሀንድሶች ጋር በመሆን አስፈላጊው ሁሉ ክትትል እየተደረገ መሆኑን የስነ ምግባር መኮነኑ ተናግረዋል ።

ሙስናና ብልሹ አሰራርን መከላከል የሚቻለው በቢሮ የስነ ምግባር መከታተያ ክፍል ብቻ ባለመሆኑ ሁሉም የሥራ ክፍሎች መተባበር እንደአለባቸዉ ጠይቀዋል ።

ህዳር 4/2018 ዓ.ም

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Benishangul Gumuz Health Bureau:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram