04/03/2026
በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር አፈፃፀምና የሁለተኛ ኳርተር የስታፍ ፎረም ተካሄደ።
***********************************
ዛሬ በቀን 25/06/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እና የሁለተኛ ኳርተር ስታፍ ፎረም ተካሄዷል። በዕለቱ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት፣ Hospital accreditation baseline assessment እና ፅዱ Initiative baseline assessment ሪፖርት ቀርቧል። በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሰብሳቢው ለተነሳው አስተያየትና ጥያቄዎች ከመድረኩ መልስ ተሰጥቶባቸዋል። በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተጠቆሙ የስታፍ ተወካይ እጬዎች ለምርጫ የቀረቡ ሲሆን አብላጫውን ድምፅ ያገኘው ግለሰብ የስታፍ ተወካይ ሆኖ ተመርጧል።