Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውና የ100 ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተውን ወርሀዊ የፅዳት ዘመቻ በቀን 25/04/...
03/01/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውና የ100 ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተውን ወርሀዊ የፅዳት ዘመቻ በቀን 25/04/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እና በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ አካሂደዋል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመጀመሪያ ግማሽ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና ተሰጠ።********************************...
29/12/2025

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመጀመሪያ ግማሽ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና ተሰጠ።
********************************
በነርሲንግና ሚድዋይፈሪ ዳይሬክቶሬት አማካኝነት የመጀመሪያ መንፈቅ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ ተሰጥቷል።
ይህ አይነቱ ፈተና ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ለሶስተኛ ጊዜ የተሰጠ ሲሆን በዚኛው ዙር 52 ነርሶችና 19 ሚድዋይፈሪ ነርሶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ተፈታኝ ባለሙያዎች ፈተናው ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ የረዳቸው መሆኑን ገልፀው፤ ክፍተት በሚታይበት ቦታ ላይ ዳይሬክቶሬቱ ባዘጋጀው የእውቀትና ክህሎት ማሳደጊያ ስርአት ውስጥ ተካተው ቀጣይነት ያለው ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውን ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል  በቀጣይ በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ  ላይ ውይይት አደረገ ።****************************************በቀን 20/04...
29/12/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀጣይ በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ ።
****************************************

በቀን 20/04/18 ዓም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ልማት እቅድ እና ኢኮኖሚ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ዮሀንስ፣ በጤና ሴክተር ለማሳካት የተያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ ተግባራትን በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በመመዝለል መርህ መቃኘት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቅሰው የ 100 ቀን ዕቅዱ በዋናነትም የትራንስፎርሜሽን ግብ ስራዎችን ማጠናከር፣ የቤተሰብ ብልፅግና ፓኬጆችን እና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤን ማጠናከር፣ ለበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ተግባራት ትኩረት በመስጠት ፣የእናቶችና ህጻናት ጤናን ማሻሻልና የስርዓተ ምግብ አገልግሎትን ማጠናከር፣ የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን፣ የጤናና ጤና ነክ ቁጥጥር ዘርፉን ማሻሻል፣በሴክተሩ የዘመነ መረጃን በተገቢው መሰነድና መጠቀምን እንደ ምሰሶ የሚቀመጡ መሆናቸውን አክለው ገልፀዋል።

የሆስፒታሉ የ100 ቀን እቅድ በሆስፒታሉ ልማት ዕቅድ የቀረበ ሲሆን የእለቱ የክብር እንግዳ አቶ አክሊሉ ዮሀንስና የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ በቀረበ ሪፖርት ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት መድረክ በጋራ መርተውታል። ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽ ተሰቶባቸዋል።

እንኳን ደስ አለን/አላችሁ!🎉🎉🎉አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለሰልጣን በተደረገ ምዘና ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ!🎉***************...
27/12/2025

እንኳን ደስ አለን/አላችሁ!🎉🎉🎉
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለሰልጣን በተደረገ ምዘና ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ!🎉
*********************************
በESA/FDA checklist መሰረት በአራቱ Pዎች (Practice፣ Premise፣ Product እና Professional ) በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የምዘና ቡድን በተደረገ አሰሳ 86% በማምጣት በክልል ደረጃ ከፍተኛ የተባለ ውጤትን አስመዝግቧል። በሆስፒታል ደረጃ ከተደራጀ አጭር ጊዜ የሆነው ተቋሙ፣ በጠንካራ አደረጃጀት እየተመራ በፍጥነት ሪፎርሞችን በመተግበርና የታለመለትን ግብ ለመድረስ ፈጠራን በማከል እጅግ አስደናቂ ለውጥን አሳይቷል። ይህ ውጤት እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዋፆ ያበረከታችሁ የሆስፒታላችን ማናጅመንት፣ የክፍልና ስራ ሂደት አስተባባሪዎች ፣የጥራት ቁጥጥር ክፍል፣ የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለስልጣን እንዲሁም መላው ሰራተኞቻችን ይህ አፈፃፀም በጋራ የመተባበር ውጤት ነውና ላቅ ያለ ምስጋና ይገባችኋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሁለተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡*****************ከቀን 13-14/04/18 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በ...
23/12/2025

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሁለተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡
*****************
ከቀን 13-14/04/18 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደ የደም ልገሳ መርሀግብር ለተቋሙ ሪከርድ የሆነ 112 ዩኒት ደም መሰብሰብ ተችሏል። በMCC ኮሚቴ አስተባባሪነት በተካሄደው የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ የሆስፒታሉ ማናጅመንት እንዲሁም ሰራተኞች በስፋት ተሳትፈዋል።
በዚህ በጎ አድራጎት ተግባር በማስተባበር የተሳተፋችሁ የሆስፒታሉ ማናጅመንት፣ MCC committee እና QIT team እንዲሁም ውድ የሆነውን ስጦታ ላበረከታችሁ የሆስፒታላችን ሰራተኞችና ተገልጋዮች ምስጋና ይገባችኋል።
ደም እንለግስ ህይወትን እንታደግ!

በሲዳማ ክልል ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ የሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት በይፋ ተጀምሯል ። ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠው የጉበት በሽታ መከላከያ ...
06/12/2025

በሲዳማ ክልል ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ የሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት በይፋ ተጀምሯል ።

ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠው የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት አገልግሎት በማስጀመሪያ መርሐ ግብር በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በይፋ ተጀምሯል።

በማስጀመሪያው መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ሀላፊ አቶ በላይነህ በቀለ እንደተናገሩት ፦ጥራቱን የጠበቀ የክትባት ተደራሽነትን ማረጋገጥ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ሚናው የላቀ መሆኑን ገልፀዋል ።

እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ክልል የጉበት ቫይረስ በሽታን ስርጭትን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፋት እቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ በላይነህ ፤ ለዚህም ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ ለሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት ሁሉም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጉበት በሽታ ከሚተላለፍባቸው ዋነኛ መንገዶች መካከል ከእናት ወደ ልጅ መሆኑን የተናገሩት አቶ በላይነህ ሕፃናትን እንደ ተወለዱ ክትባቱን እንዲወስዱ ማድረግ ዋነኛ የመከላከያ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል ።

የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባቱ ከዛሬ ጀምሮ በመደበኛ ክትባት መርሐ ግብር ተካትቶ መሰጠት እንደሚጀምርም ገልጸዋል።

በሁሉም ጤና ተቋማት ጥራቱን ጠበቀ መልኩ በመደበኛ የክትባት ፕሮግራም አስገብተው ክትባቱን እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን ፤ ወላጆች ልጆቻቸውን እንደ ወለዱ ህጻናት በ24 ሠአት ውስጥ እንዲያስከተቡ ለወላጆች ጥሪአቸውን አስተላልፈዋል ።

በፕሮራሙ ላይ ከሲዳማ ክልሉ ጤና ቢሮ ፣ከአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ ከጤና መምሪያ እንዲሁም ከጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል::

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር  ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ "እኔም የከተማዬ የፅዳት አምባሳደር ነኝ !” በሚል መሪ  ቃል በተዘጋጀው የፅ...
22/11/2025

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ "እኔም የከተማዬ የፅዳት አምባሳደር ነኝ !” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የፅዳት ንቅናቄ ዘመቻ ተሳታፊ ሆነዋል።
************************
በታቦር ክፍለ ከተማ በፋራ ቀበሌ የተጀመረው ፅዳት በንቅናቄ መልክ ለሚቀጥሉት 8 ሳምንታት በሁሉም ክፍለ ከተማ እንደሚካሄድ ታውቋል።

‎ከንቲባ ጥራቱ በየነ በፅዳት ዘመቻው የማስጀመሪያ መርሀግብር ላይ እንደተናገሩት የሀዋሳ ከተማን ውብ፣ ፅዱና አረንጓዴ የማድረጉ ሂደት እንደ ከተማ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

‎ይህ ጥረት በተቀናጀ መልኩ ከዳር በማድረስ ሀዋሳን ለነዋሪዎቿ፣ ለባለሀብቱ እና ለጎብኚው ምቹ ማረፊያና ጥሪት ማፍሪያ ለማድረግ የበኩሉን አስተዋፆኦ የሚያበረክት በመሆኑ ይበልጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።

‎ይህ የሚሆነው ሁሉም የሀዋሳ አካባቢዎች ብሎኮችና መንደሮች ውብና ፅዱ መሆን ሲችሉ ነውም ብለዋል።

‎ከተማችን ሀዋሳ ውብ ፅዱና አረንጓዴ የሚለውን ስሟን ጠብቃ እንድትጓዝ የሁላችንንም ጥረት እና የተቀናጀ ተሳትፎ ያስፈልጋታል ብለዋል ከንቲባ ጥራቱ በየነ።

‎ጽዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ማለት የሰለጠነ የከተማ ባለቤት እንደሆነ የተናገሩት አቶ ጥራቱ ለዚህም ሀዋሳን እንደ ሀገር በዚህ ዘርፍ ተመራጭ እንድትሆን እየተጉ ያሉ የፅዳት ሰራተኞች ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል።

‎የፅዳት ዘመቻው በ8ቱም ክፍለ ከተማ በተመሳሳይ ሰዓት ስለመከናወኑም ከንቲባ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ ‎**************************************...
06/11/2025

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ
‎******************************************

‎ይህ የተገለጸው የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ውይይት መድረክ ባደረገበት ወቅት ነው።

‎የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮስፍ ዮሄ በንግግራቸው ሆስፒታሉ በሚሰጠው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ከፍተኛ ቁጥር ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

‎በዚህ ረገድ በሆስፒታሉ ቀደም ሲል ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት በማስቀጠልና አዳዲስ አገልግሎቶችን በማስጀመር ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑንም አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል።

‎ሆስፒታሉ በየጊዜው ከሕብረተሰብ የሚነሱ ጥያቄዎችን በአግባቡ ምላሽ መስጠት የሚያስችለውን መድረክ መፍጠሩ ለአገልግሎቱ ውጤታማነት አመላካች እንደሆነም ነው ኃላፊው ያስረዱት።

‎ከሐዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ የህክምና አገልግሎቶች ዳይሬክተሬት ዳይሬክተር አቶ ወ/ሰንበት ዳንኤል የሆስፒታሉ ዕድገት እየጨመረ የመጣውን የህብረተሰብ ክፍል በማስረዳት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ለቀጣይም በችግሮቹ ዙሪያ ጠንክሮ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

‎ሆስፒታሉ ቀደም ብሎ ከህብረተሰቡ ይነሱ የነበረውን ቅሬታዎችን በመፍታት የህክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በመሟላት የተሻለ አገልግሎት ለህብረተሰቡ እየሰጠ መሆኑን አቶ ወ/ሰንበት ተናግረዋል።

‎ተሳታፊዎቹ እንደገለጹት የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ እያሳየ እንደመጣና በተለይም የህክምና ባለሙያዎች ለህሙማን በሚያደርጉት እንክብካቤ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎በዚህ ረገድ በሆስፒታሉ የተጀመሩ የህንፃ ግንባታዎች ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ፣ የአልተራሳውንድን አገልግሎትን ጨምሮ በሌሎች ላይ ጥረት እንዲደረግ ጠቁመዋል።

04/11/2025
‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ገለፀ‎‎የሐ/ከ/የመ/ኮ/ መምሪያ‎ጥቅምት 13/2018 ዓ/ም‎ሐዋሳ ‎‎በከተማ የጤ...
24/10/2025

‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ገለፀ

‎የሐ/ከ/የመ/ኮ/ መምሪያ
‎ጥቅምት 13/2018 ዓ/ም
‎ሐዋሳ

‎በከተማ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል ያሉት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኋላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ የ2018 የማዐጤመ አገልግሎት ውል የሚታደስበት ወቅት መሆኑን አስመልክቶ ተናግረዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ዜጎች አስቀድመው በሚከፍሉት አነስተኛ መዋጮ ያልተገባ የጤና ወጪ ውስጥ እንዳይገቡ እና ወጪውን በመፍራት ልከሰት የምችለውን የጤና መታወክን የሚቀንስ መሆኑን ገልፀው በየዓመቱ አበረታች ለውጦች መመዝገባቸውን ሀላፊው ጠቁመዋል።

‎ባለፉት አምስት ዓመታት በጤና መዲን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥርና ተገልጋዮች ወደ ጤና ተቋማት የነበረው ፍሰት ጨምሯልም ነው ያሉት።

‎የተጠቃሚው ቁጥር መጨመርን አስመልክቶም የማህበረሰቡ የግንዛቤ ደረጃ ማደግ፣ የጤና ተቋማቶቻችን ዝግጅት እየተሻሻለ መምጣቱና ተገልጋይ ተኮር አገልግሎት እየሰጠ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል አቶ ይርዳቸው።

‎በጤና ተቋማቶቻችን ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ከህብረተሰቡ ዘንድ አልፎ አልፎ የሚነሱ የመድሃኒት አቅርቦት ችግር መኖሩንም ሀላፊው አስረድተዋል።

‎ችግሩንም ለመፍታትም ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮ በተሻለ የመድኋኒት አቅርቦት እንድኖር ሀብት መመደቡን እንዲሁም ጤና ተቋማቶቻችን የ 'ማዐጤመ' ቅድመ-ክፊያ ወስዶ መድኋኒት እንድገዙ ተደርጓልም ነው ያሉት ኋላፊው።

‎በተጨማሪም የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቶችን በማጠናከርና መድኋኒት ቤቱንም የ 'ማዐጤመ' አባላት በመታወቂያቸው እንድገለገሉበት በሚያስችል ሁኔታ ውል በማሰር የመድኋኒት አቅርቦት ችግር ለመፍታት መታቀዱንም አቶ ይርዳቸው ተናግረዋል።

‎አቶ ይርዳቸው አያይዘውም በ '2018' በጀት አመትም 49 ሺህ 2 መቶ 60 አባወራዎችን በዚህም 241 ሺህ 3 መቶ 74 ዜጎችን በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን መርሃ-ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ግብ ተጥሎ የዕቅድ አካል በማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑን ተናግረዋል።

‎የነባር አባላት እድሳት እና የአዲስ አባላት ምዝገባ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ድረስ እንደሚያካሂድ አቶ ይርዳቸው ጠቁመዋል፡፡

‎በሁሉም ጤና ተቋማቶቻችን አገልግሎቱ ከሰኞ ጥቅምት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ2018 ዓ.ም በታደሰ መታወቂያ ስለሚሰጥ ማህበረሰቡም በመድህን መርህ መሠረት ቀበሌ በመድረስ በከፍተኛ የተፈረጁ 1ሺህ 9 መቶ 30 ብር፣ በመካከለኛ ደረጃ የተፈረጁ 1 ሺህ 3 መቶ 10 ብር በመክፈል የታደሰ መታወቂያ በመያዝ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሁኑ ላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ሰራተኞች የቡሹሎ እናቶችና ህጻናት ህክምና ማዕከል በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል። የጨቅላ ህጻናትና የህጻናት ህክምና...
14/10/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ሰራተኞች የቡሹሎ እናቶችና ህጻናት ህክምና ማዕከል በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።
የጨቅላ ህጻናትና የህጻናት ህክምና፣ የእናቶች የወሊድና የቀዶ ህክምና አገልግሎት እንዲሁም ተቋሙ በላቀበት በclinical engineering ዙሪያ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ጉብኝት የተደረገባቸው ሲሆን ከማእከሉም የስራ ሀላፊዎች ጋርም በጉብኝቱ ዙሪያ እንዲሁም ሁለቱ ጤና ተቋማት በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/02/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ፣ በሆስፒታል ...
11/10/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/02/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ፣ በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች እንዲሁም የቀበሌ አመራሮችን ባካተተ በተመረጡ በካችመንት ባሉ መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram