16/03/2026
የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።
*****************************************
ዛሬ በቀን 07/07/18 ዓም የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጫምባላላ በዓል በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ጊቢ ከአካባቢ ማህበረሰብ፣ ከሀገር ሽማግሌ እንዲሁም ከሆስፒታሉ ማናጅመንትና ሰራተኞች ጋር በጋራ በድምቀት ተከብሯል።
በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት በጀመረው ዝግጅት ፣የሲዳማ ብሄር ባህል ፣ ወግ እንዲሁም ትውፊትን የሚያወሱ ዝግጅቶች የተሰናዱ ሲሆን የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞችም ለታዳሚያን ቀርበዋል።
በዕለቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ፣ ፍቼ ጫምባላላ የሰላምና የእርቅ በአል መሆኑን አውስተው፣ ያለፈ ቂምና ጥላቻን አስወግደን ወደአዲሱ አመት መሻገር እንደሚገባ በንግግራቸው አፀንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የሲዳማ ብሄር ባህላዊ ምግብ ቀርቦ በጋራ ማዕድ ተቋድሰዋል።
Hawalle Sidaamu Daga Diru sooro Fichee Cambalaallate ayyanira keeruni iillishinke!
እንኳን ለሲዳማ ብሔር የዘመን መለዋጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ !