Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

በሲዳማ ክልል ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ የሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት በይፋ ተጀምሯል ። ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠው የጉበት በሽታ መከላከያ ...
06/12/2025

በሲዳማ ክልል ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ የሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት በይፋ ተጀምሯል ።

ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠው የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት አገልግሎት በማስጀመሪያ መርሐ ግብር በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በይፋ ተጀምሯል።

በማስጀመሪያው መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ሀላፊ አቶ በላይነህ በቀለ እንደተናገሩት ፦ጥራቱን የጠበቀ የክትባት ተደራሽነትን ማረጋገጥ ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ሚናው የላቀ መሆኑን ገልፀዋል ።

እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ክልል የጉበት ቫይረስ በሽታን ስርጭትን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፋት እቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ በላይነህ ፤ ለዚህም ህፃናት እንደተወለዱ በ24 ሰአት ውስጥ ለሚሰጠው የጉበት በሽታ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ ክትባት ሁሉም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጉበት በሽታ ከሚተላለፍባቸው ዋነኛ መንገዶች መካከል ከእናት ወደ ልጅ መሆኑን የተናገሩት አቶ በላይነህ ሕፃናትን እንደ ተወለዱ ክትባቱን እንዲወስዱ ማድረግ ዋነኛ የመከላከያ መንገድ መሆኑን ተናግረዋል ።

የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባቱ ከዛሬ ጀምሮ በመደበኛ ክትባት መርሐ ግብር ተካትቶ መሰጠት እንደሚጀምርም ገልጸዋል።

በሁሉም ጤና ተቋማት ጥራቱን ጠበቀ መልኩ በመደበኛ የክትባት ፕሮግራም አስገብተው ክትባቱን እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን ፤ ወላጆች ልጆቻቸውን እንደ ወለዱ ህጻናት በ24 ሠአት ውስጥ እንዲያስከተቡ ለወላጆች ጥሪአቸውን አስተላልፈዋል ።

በፕሮራሙ ላይ ከሲዳማ ክልሉ ጤና ቢሮ ፣ከአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ ከጤና መምሪያ እንዲሁም ከጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል::

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር  ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ "እኔም የከተማዬ የፅዳት አምባሳደር ነኝ !” በሚል መሪ  ቃል በተዘጋጀው የፅ...
22/11/2025

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ "እኔም የከተማዬ የፅዳት አምባሳደር ነኝ !” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የፅዳት ንቅናቄ ዘመቻ ተሳታፊ ሆነዋል።
************************
በታቦር ክፍለ ከተማ በፋራ ቀበሌ የተጀመረው ፅዳት በንቅናቄ መልክ ለሚቀጥሉት 8 ሳምንታት በሁሉም ክፍለ ከተማ እንደሚካሄድ ታውቋል።

‎ከንቲባ ጥራቱ በየነ በፅዳት ዘመቻው የማስጀመሪያ መርሀግብር ላይ እንደተናገሩት የሀዋሳ ከተማን ውብ፣ ፅዱና አረንጓዴ የማድረጉ ሂደት እንደ ከተማ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

‎ይህ ጥረት በተቀናጀ መልኩ ከዳር በማድረስ ሀዋሳን ለነዋሪዎቿ፣ ለባለሀብቱ እና ለጎብኚው ምቹ ማረፊያና ጥሪት ማፍሪያ ለማድረግ የበኩሉን አስተዋፆኦ የሚያበረክት በመሆኑ ይበልጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።

‎ይህ የሚሆነው ሁሉም የሀዋሳ አካባቢዎች ብሎኮችና መንደሮች ውብና ፅዱ መሆን ሲችሉ ነውም ብለዋል።

‎ከተማችን ሀዋሳ ውብ ፅዱና አረንጓዴ የሚለውን ስሟን ጠብቃ እንድትጓዝ የሁላችንንም ጥረት እና የተቀናጀ ተሳትፎ ያስፈልጋታል ብለዋል ከንቲባ ጥራቱ በየነ።

‎ጽዳትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ማለት የሰለጠነ የከተማ ባለቤት እንደሆነ የተናገሩት አቶ ጥራቱ ለዚህም ሀዋሳን እንደ ሀገር በዚህ ዘርፍ ተመራጭ እንድትሆን እየተጉ ያሉ የፅዳት ሰራተኞች ሚናቸው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል።

‎የፅዳት ዘመቻው በ8ቱም ክፍለ ከተማ በተመሳሳይ ሰዓት ስለመከናወኑም ከንቲባ ጥራቱ በየነ ተናግረዋል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ ‎**************************************...
06/11/2025

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ገለጹ
‎******************************************

‎ይህ የተገለጸው የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ውይይት መድረክ ባደረገበት ወቅት ነው።

‎የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮስፍ ዮሄ በንግግራቸው ሆስፒታሉ በሚሰጠው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ከፍተኛ ቁጥር ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

‎በዚህ ረገድ በሆስፒታሉ ቀደም ሲል ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት በማስቀጠልና አዳዲስ አገልግሎቶችን በማስጀመር ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑንም አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል።

‎ሆስፒታሉ በየጊዜው ከሕብረተሰብ የሚነሱ ጥያቄዎችን በአግባቡ ምላሽ መስጠት የሚያስችለውን መድረክ መፍጠሩ ለአገልግሎቱ ውጤታማነት አመላካች እንደሆነም ነው ኃላፊው ያስረዱት።

‎ከሐዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ የህክምና አገልግሎቶች ዳይሬክተሬት ዳይሬክተር አቶ ወ/ሰንበት ዳንኤል የሆስፒታሉ ዕድገት እየጨመረ የመጣውን የህብረተሰብ ክፍል በማስረዳት እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ለቀጣይም በችግሮቹ ዙሪያ ጠንክሮ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

‎ሆስፒታሉ ቀደም ብሎ ከህብረተሰቡ ይነሱ የነበረውን ቅሬታዎችን በመፍታት የህክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በመሟላት የተሻለ አገልግሎት ለህብረተሰቡ እየሰጠ መሆኑን አቶ ወ/ሰንበት ተናግረዋል።

‎ተሳታፊዎቹ እንደገለጹት የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ እያሳየ እንደመጣና በተለይም የህክምና ባለሙያዎች ለህሙማን በሚያደርጉት እንክብካቤ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎በዚህ ረገድ በሆስፒታሉ የተጀመሩ የህንፃ ግንባታዎች ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ፣ የአልተራሳውንድን አገልግሎትን ጨምሮ በሌሎች ላይ ጥረት እንዲደረግ ጠቁመዋል።

04/11/2025
‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ገለፀ‎‎የሐ/ከ/የመ/ኮ/ መምሪያ‎ጥቅምት 13/2018 ዓ/ም‎ሐዋሳ ‎‎በከተማ የጤ...
24/10/2025

‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ገለፀ

‎የሐ/ከ/የመ/ኮ/ መምሪያ
‎ጥቅምት 13/2018 ዓ/ም
‎ሐዋሳ

‎በከተማ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል ያሉት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኋላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ የ2018 የማዐጤመ አገልግሎት ውል የሚታደስበት ወቅት መሆኑን አስመልክቶ ተናግረዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ዜጎች አስቀድመው በሚከፍሉት አነስተኛ መዋጮ ያልተገባ የጤና ወጪ ውስጥ እንዳይገቡ እና ወጪውን በመፍራት ልከሰት የምችለውን የጤና መታወክን የሚቀንስ መሆኑን ገልፀው በየዓመቱ አበረታች ለውጦች መመዝገባቸውን ሀላፊው ጠቁመዋል።

‎ባለፉት አምስት ዓመታት በጤና መዲን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥርና ተገልጋዮች ወደ ጤና ተቋማት የነበረው ፍሰት ጨምሯልም ነው ያሉት።

‎የተጠቃሚው ቁጥር መጨመርን አስመልክቶም የማህበረሰቡ የግንዛቤ ደረጃ ማደግ፣ የጤና ተቋማቶቻችን ዝግጅት እየተሻሻለ መምጣቱና ተገልጋይ ተኮር አገልግሎት እየሰጠ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል አቶ ይርዳቸው።

‎በጤና ተቋማቶቻችን ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ከህብረተሰቡ ዘንድ አልፎ አልፎ የሚነሱ የመድሃኒት አቅርቦት ችግር መኖሩንም ሀላፊው አስረድተዋል።

‎ችግሩንም ለመፍታትም ከተማ አስተዳደሩ ከወትሮ በተሻለ የመድኋኒት አቅርቦት እንድኖር ሀብት መመደቡን እንዲሁም ጤና ተቋማቶቻችን የ 'ማዐጤመ' ቅድመ-ክፊያ ወስዶ መድኋኒት እንድገዙ ተደርጓልም ነው ያሉት ኋላፊው።

‎በተጨማሪም የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቶችን በማጠናከርና መድኋኒት ቤቱንም የ 'ማዐጤመ' አባላት በመታወቂያቸው እንድገለገሉበት በሚያስችል ሁኔታ ውል በማሰር የመድኋኒት አቅርቦት ችግር ለመፍታት መታቀዱንም አቶ ይርዳቸው ተናግረዋል።

‎አቶ ይርዳቸው አያይዘውም በ '2018' በጀት አመትም 49 ሺህ 2 መቶ 60 አባወራዎችን በዚህም 241 ሺህ 3 መቶ 74 ዜጎችን በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን መርሃ-ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ግብ ተጥሎ የዕቅድ አካል በማድረግ እየተሰራ ስለመሆኑን ተናግረዋል።

‎የነባር አባላት እድሳት እና የአዲስ አባላት ምዝገባ ከጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ድረስ እንደሚያካሂድ አቶ ይርዳቸው ጠቁመዋል፡፡

‎በሁሉም ጤና ተቋማቶቻችን አገልግሎቱ ከሰኞ ጥቅምት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ2018 ዓ.ም በታደሰ መታወቂያ ስለሚሰጥ ማህበረሰቡም በመድህን መርህ መሠረት ቀበሌ በመድረስ በከፍተኛ የተፈረጁ 1ሺህ 9 መቶ 30 ብር፣ በመካከለኛ ደረጃ የተፈረጁ 1 ሺህ 3 መቶ 10 ብር በመክፈል የታደሰ መታወቂያ በመያዝ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሁኑ ላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ሰራተኞች የቡሹሎ እናቶችና ህጻናት ህክምና ማዕከል በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል። የጨቅላ ህጻናትና የህጻናት ህክምና...
14/10/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ሰራተኞች የቡሹሎ እናቶችና ህጻናት ህክምና ማዕከል በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።
የጨቅላ ህጻናትና የህጻናት ህክምና፣ የእናቶች የወሊድና የቀዶ ህክምና አገልግሎት እንዲሁም ተቋሙ በላቀበት በclinical engineering ዙሪያ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ጉብኝት የተደረገባቸው ሲሆን ከማእከሉም የስራ ሀላፊዎች ጋርም በጉብኝቱ ዙሪያ እንዲሁም ሁለቱ ጤና ተቋማት በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/02/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ፣ በሆስፒታል ...
11/10/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 01/02/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ፣ በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች እንዲሁም የቀበሌ አመራሮችን ባካተተ በተመረጡ በካችመንት ባሉ መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው የህዝብ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።*****...
23/09/2025

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀው የህዝብ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።
**************************************
‎ዛሬ በቀን 13/01/18 ዓም ግድቡ የኔ ነው ፣‎ የውጭ ተጽዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ! የህዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያ፣ ማንሰራራት ምልክት እና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ በተደረገው ሰልፍ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።

‎በሰልፉ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ የዘመናት የትውልድ መሻት የሆነውን የህዳሴ ግድባችን ተገንብቶ በድል መጠናቀቁ የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ ስኬታማነት ማሳያ ነው ብለዋል።

‎ህብረታችን የትልቅነታችን ምልክት ነው ያሉት ኘሬዚዳንቱ፣ ስንደመር እና በጋራ ስንቆም በትክክል የማንችለው ነገር እንዳሌለ ማሳየት የቻልንበትም ነው በማለት ተናግረዋል።

‎በቀጣይ ኢትዮጵያችን የባህር በር እቅድን ጨምሮ ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶችን ለማሳካት ጥረታችን በታላቅ ትግል የሚተገበር ይሆናል።

‎አባይን በደፈርንበት እጃችን ዛሬም በታሪክ እጥፋት ያጣነውን የባህር በር በሰላማዊ የሆነ ድርድር በማድረግ ኢትዮጵያን በቀይ ባህር በቅርቡ እንድትነግስ ያስችላታል ብለዋል።


የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን /World Patient Safety Day/ በሀዋሳ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል  ተከበረ።****************************************...
18/09/2025

የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን /World Patient Safety Day/ በሀዋሳ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።
********************************************
ዛሬ በቀን 8/01/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የአለም የህሙማን ቀን ስለ ህሙማን ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት፣ የፅዳት ዘመቻ በማድረግ እንዲሁም የጤና ትምህርት በመስጠት ተከብሯል።

“ደህንነቱን የጠበቀ ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናትና ህፃናት” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ክብረ በአል ላይ የሆስፒታል ማናጅመንት የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ስታፍ ተሳታፊ ሆነዋል።

ልንከላከላቸው የምንችላቸውን የህክምና ሞቶችን እንዲሁም ጉዳቶችን ማስቀረት ዋነኛ ትኩረታችን ሊሆን እንደሚገባ ያሳሰቡት የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ፣ ህሙማንን ከፍ ሲል ደህንነታቸውን ጠብቆ ማከም፣ ዝቅ ሲልም አለመጉዳት መርሀችን ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የበአሉ ተሳታፊዎችም በቀረበው የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ የተለያዩ ሀሳቦችን አንስተው ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ የህሙማንን ደህንነት ጠብቆ አገልግሎት ለመስጠት የገቡትንም ቃል-ኪዳን አድሰዋል።

ዛሬ በቀን 1/01/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የአዲስ አመት በአልን በጋራ አክብረዋል።
11/09/2025

ዛሬ በቀን 1/01/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የአዲስ አመት በአልን በጋራ አክብረዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ ማስተላለፍን ጨምሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ፣*****...
10/09/2025

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ ማስተላለፍን ጨምሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ፣
***************************************
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ የማስተላለፍን ጨምሮ እገዛ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የእህል፣ የምግብ ዘይት ና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በመልዕክታቸው፦÷ ሆስፒታሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ እንደሆነ ገልፀው በዚህም ጊዜ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸው የሚደነቅ በማለት ዛሬ የተደረገው ማዕድ ማጋራት ብቻ ሳይሆን በጤናው ዘርፍ በትጋት ፣በቁርጠኝነትና በመሰጠት የህይወት መስዋትነትን ጨምሮ ቤተሰባችሁን መስዋዕት በማድረግ ለበረከታችሁት ዓርአያነት ያለው ተግባር ለማበረታታትና እናመሰግናችኋለን ለማለት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

አዲስ ዓመት በዓል የሚከበርበት፣ ጥልቅ የሆነ ማህበራዊ ትስስሮች የሚጠናከሩበት፤ ከግለሰብ ጀምሮ በቤተሰብ፣ በማህበረሰብ፣ በመንግስትና በተለያዩ ተቋማት ጭምር አዳዲስ ክንውኖች የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው አውስተው፤ በመልካም ምኞት መግለጫቸው፥ "መጪው አዲስ ዓመት የሰላም፣ የጤና ፣የፍቅር፣ የመተሳሰብ እንዲሆን እመኛለሁ" ብለዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ በበኩላቸው 2017 ዓ/ም እንደሀገር ስኬት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን በማንሳት ሁሉም በተሰማራበት መስክ ለሀገር ብልጽና እሴትን በሚጨምሩ ተግባራትላ ጠንካራ የአብሮነት፣ የመደጋገፍ፣ የመከባበርና የመረዳዳት ዕሴቶቻችን ሊጎለብቱ እንደሚገበቸው ተናግረዋል፡

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ዩዌ የሆስፒቲሉ MCCቲም ባለሙያዎች በተቋሙ በርካታ የበጎነት ተግባር እንደሚያከናወኑ ገልጸው ፤ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ የማስተላለፍን ጨምሮ እገዛ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የእህልና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እጅግ አበረታች ብለውታል ፡፡

በፕሮግራሙ የጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች፣የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ፣ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ፣ የማጅመቶች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሠራተኞች ፎረምና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ*********************************************በመድረኩም በ2017 ...
05/09/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሠራተኞች ፎረምና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ
*********************************************
በመድረኩም በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ባለሙያዎች፣ የስራ ሂደት፣ የቀድሞ ማኔጅመንት አካላት፣ ድጋፍ ላደረጉ ድርጅቶች፣ የጤና ተቋማትና ለግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ ሆስፒታሉ በቅርብ ጊዜ ቢቋቋምም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ እንዳለው ገልፀው ከተማውን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ከዚህ በላይ መሠራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

ከህብረተሰቡ የተሠጠውን የሆስፒታሉ የአገልግሎት ምስክርነት ለማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት በምን አግባብ እሰራለን የሚለውን በመነጋገር ውጤቱን ማስቀጠል እንደሚገባም አቶ ማራዶና ተናግረዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጌቱ ማሞ በንግግራቸው በበጀት ዓመቱ ሆስፒታሉ ባጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ የሆስፒታሉን የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማዘመን ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊ ድጋፍ እያደረገ መቆየቱን ተናግረው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ የተቀናጀ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዮን ህብረተሰብ ፍላጎት ለማርካት በበጀት አመቱ መጀመሪያ የታቀዱ ስራዎች በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በአፈፃፀም ወቅት የተገኙ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና በጉድለት የተለዩ ችግሮችን ለቅሞ በ2018 መፍታትና የእርምት እርምጃዎችን በመውስድ የተሻ አፈፃፀም እንሚያስመዘግብ አቶ ዮሴፍ ተናግረዋል።

በጀት ዓመት በሆስፒታሉ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማበረታቻ ሽልማት እንደተደረገላቸው አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል።

የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም የሆስፒታሉ ሚዲካል ዳሬክተር ዶ/ር ሄኖክ ኢሳያስ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓበታል።

የመድረኩ ተሣታፊዎች በበኩላቸው በተቋሙ የተለያዩ አገልግሎት ዘርፎች ላይ በርካታ ቁጥር ላላቸው ማህብረሰብ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልፀው ከዚህ በተሻለ መልኩ መሰራት እንዳለበት ሀሳብ ሰጥተዋል።

በመድረኩም ተሸላሚዎች የሰረተፍኬት፣ የማዳልያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram