Debre Tabor Comprehensive Specialized Hospital

Debre Tabor Comprehensive Specialized Hospital Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Debre Tabor Comprehensive Specialized Hospital, Hospital, Debre Tabor.

በደብረታቦር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሊቋቋም የታሰበውን የጡት ካንሰር ህክምና መስጫ ማእከል እውን ለማድረግ ሁሉም አካል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ!ዓለም አቀፉን የጡት ካንሰር ቀን...
08/11/2024

በደብረታቦር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሊቋቋም የታሰበውን የጡት ካንሰር ህክምና መስጫ ማእከል እውን ለማድረግ ሁሉም አካል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ!

ዓለም አቀፉን የጡት ካንሰር ቀን አስመልክቶ በደብረታቦር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከበሽታው ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ እና በሆስፒታሉ የጡት ካንሰር ህክምና ማእከልን ማቋቋም በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡

የሆስፒታሉ፣ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ የደብረታቦር ከተማ አስተዳደርና የደቡብ ጎንደር ዞን የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት የፓናል ውይይቱ ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ላይ የደብረታቦር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ሰውመሆን ደሳለኝ እንደተናገሩት የጡት ካንሰር በሽታ በርካታ ወገኖችን ለህመምና ለሞት እየዳረገ የሚገኝ አስከፊ በሽታ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በበሽታው የሚያዙ ዜጎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ገልፀው የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ሁላችንም ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡

የጤና ባለሙያዎች ስለ በሽታው የጠራ ግንዛቤ በመያዝ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸውም አስገንዝበው በሆስፒታሉ የፊታችን ሰኞ ጀምሮ የጡት ካንሰር ልየታ ስራ የሚጀመር ስለሆነ እድሜያቸው ከ40 አመት በላይ የሆኑ ሴቶች ወደ ሆስፒታሉ በመሄድ የቅድመ ካንሰር ምርመራ እንዲያደርጉ መክረዋል፡፡

ዶክተር ሰውመሆን አያይዘውም በሆስፒታሉ የጡት ካንሰር ህክምና መስጫ ማእከል ለማቋቋም በእቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ማእከሉን ለማቋቋም የሚመለከተቸው የመንግስት አካላት እና መንግስታና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ድርጅቶች ድጋፍና እገዛ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል፡፡

በፓናል ውይይቱ ላይ ስለ ጡት ካንሰር ምንነት፣ አጋላጭ ምክንያቶች፣ የበሽታው ምልክቶች፣ የምርመራ መንገዶች፣ የበሽታው ደረጃዎች፣ የህክምና ዘዴዎችና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች በዘርፉ ባለሙያዎች ገለጻ ተደርጓል፡፡

በፓናል ውይይቱ ላይ የተሳተፉ አካላትም በሰጡት ሀሳብ የጡት ካንሰር በሽታ በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን መጠነ ሰፊ ችግር ለማስቀረት ለማህበረሰቡ ስለ በሽታው በተገቢው ሁኔታ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ሴቶች በሚፈለገው እድሜ ላይ የቅድመ ካንሰር ምርመራ እንዲያደርጉ አስፈላጊውን ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡

በሆስፒታሉ የጡት ካንሰር ህክምና ማእከልን በማቋቋም አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የተያዘው እቅድ ይበል የሚያሰኝ መሆኑንም ተናግረው ስራውን በቀላሉ በማሰጀመር ሊያግዙና ሊደግፉ የሚችሉ አካላትን ማስተባበር እንደሚያስፈልግም ጠቁመው ለህክምና ማእከሉ እውን መሆን ማህበረሰቡና ሌላውም አካል ሊሰራና ሊተባበር ይገባልም ብለዋል፡፡

የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ማህበረሰቡ የአካባቢ ቁጥጥር ስራን በተገቢው ሁኔታ ሊሰራ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡የወባ ወረርሽኝ በክልሉና በከተማ አስተዳደሩ በከፍተኛ ሁኔታ...
05/11/2024

የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ማህበረሰቡ የአካባቢ ቁጥጥር ስራን በተገቢው ሁኔታ ሊሰራ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡

የወባ ወረርሽኝ በክልሉና በከተማ አስተዳደሩ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ በመሆኑ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት የመከላከልና የመቆጣጠር ስራን ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግም ተመላክቷል፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ “የዓርብ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ” በሚል መሪ መልእክት ጤና ጣቢያ መር የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ቁጥጥር ስራን የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ ከወባ በሽታ ጋር ተያይዞ ሰነድ ያቀረቡት የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ በረከት ገደፋው እንዳሉት የወባ በሽታ በሀገራችን ብሎም በክልላችን ገዳይ ከሚባሉት አስከፊ በሽታዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ መሆኑን ጠቅሰው በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ እና በወረርሽኝ መልክ እየተስፋፋ መሆኑን ገልፀው የወባ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከጥቅምት 15 እስከ ታህሳስ 30 2017 ዓ/ም የሚቆይ ጤና ጣቢያ መር የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ቁጥጥር ስዎችራን ለመስራት ማህበረሰቡን ባሳተፈ አግባብ በንቅናቄ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡

በየሳምንቱ አርብ አርብ በሚካሄደው የአካባቢ ቁጥጥር ስራም ለወባ ትንኝ መራቢያ አመች የሚሆኑ ነገሮችን የማጽዳት፣ የማዳረቅ፣ የማፋሰስ፣ የማጣፈፍ እና ሌሎችም ስራዎች እንደሚሰሩ ጠቅሰው ህብረተሰቡ በየአካባቢው ውሀ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስ፤ ወንዞችን ኩሬዎችንና ሌሎችንም ውሀ ያላቸውን ነገሮች የመረበሽ፤ ሰባራ እቃወችን፣ የዛፍ ቅጠሎችንና ሌሎችንም ውሀ ሊይዙ የሚችሉ ነገሮችን ማስወገድ እንዳለበት አስገንዝበው የወባ በሽታ በከተማ አስተዳደሩ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ እየተስፋፋ በመሆኑ ሁላችንም ትኩረት ሰጥተን በመስራት በሽታውን መከላከልና መቆጣጠር አለብንም ብለዋል አቶ በረከት፡፡

የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደበበ አክሎግ እንደተናገሩት በክልሉ ብሎም በከተማ አስተዳደሩ የወባ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋና የማህበረሰቡ የጤና ችግር እየሆነ መምጣቱን ጠቁመው በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የአካባቢ ቁጥጥር ስራውን በሚፈለገው መንገድ መስራት አለብን ብለዋል፡፡

የወባ በሽታ በአብዛኛው ሰብል በሚሰበሰብበት ወቅት የሚከሰት በመሆኑ በምርትና ምርታማነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ መሆኑንና በዜጎች ላይም ሞትን እያስከተለ የሚገኝ አስከፊ በሽታ መሆኑን ገልፀው ማህበረሰቡን ባሳተፈ አግባብ የመከላከልና የቁጥጥር ስራዎችን መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ የተሳተፉ አካላትም በሰጡት ሀሳብ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የማህበረሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ የአካባቢ ቁጥጥር ስራዎችን በባለቤት ይዞ እንዲሰራ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረው ወረርሽኙን በሚፈለገው አግባብ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ሁላችንም ትኩረት ሰጥተን መስራት አለብን ብለዋል፡፡

በገጠር ቀበሌዎች ለሚኖረው የማህበረሰብ ክፍል ቀደም ሲል የወባ መከላከያ አጎበር ይሰጥ እንደነበርም አውስተው አሁን ካለው የወባ ወረርሽኝ አኳያ አጎበርን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

በተያያዘም በደብረታቦር ከተማ አስተዳደር “የዓርብ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ” በሚል መሪ ሀሳብ ጤና ጣቢያ መር የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ቁጥጥር ስራ ባሳለፍነው አርብ በንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን ተግባሩ በየሳምንቱ አርብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል፡፡

መረጃበደብረታቦር ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና ህዳር 9-13/2017 ዓ.ም ይሰጣል
03/11/2024

መረጃ

በደብረታቦር ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና ህዳር 9-13/2017 ዓ.ም ይሰጣል

Address

Debre Tabor

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Tabor Comprehensive Specialized Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category