Fanus Nega .ፋኑስ ነጋ

Fanus Nega .ፋኑስ ነጋ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fanus Nega .ፋኑስ ነጋ, Doctor, Gonder.

01/08/2023

ታላቅ አማራዊ ንቅናቄ ጥሪ፤ ለመላው አማራ ሕዝብ!

የአማራ ሕዝብ ላለፉት አመታት በከፍተኛ መሳደድ፣ መፈናቀል እና ጅምላ ግድያ ላይ ይገኛል። ነገር ግን ነብልባሉ የአማራ ፋኖ ባደረገው አስደናቂ ተጋድሎ የአማራ ሕዝብ አንገቱን ቀና አድርጎ መሄድ ጀምሯል፤ በልበ ሙሉነት እኔ አማራ ነኝ! እኔ ፋኖ ነኝ ማለት ጀምሯል። የአማራ ሕዝብ ተጋድሎም ተጠናክሮ ቀጥሏል። ይቀጥላል‼️

እየተዋደቀ ለሚገኘው የአማራ ሕዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ ፋኖ እኛ ምን አድርገናል ብላችሁ አስባችሁ ታውቃላችሁ?

የአማራ ወጣቶች ማሕበር ለመላው የአማራ ሕዝብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚከተለውን እንድናደርግ የከበረ ጥሪውን ያስተላልፋል፦

በመጪው ዕረቡ ዕለት በተመሳሳይ ሰዓት (ከቀኑ 10:00 ሰዓት ) በቤታችን፣ በስራ ቦታችን፣ በመዝናኛ ቦታዎች ፣ በመንገድ ላይ ወዘተ ሁላችን በአንድ ላይ በመነሳት "እኔ ፋኖ ነኝ!!" የሚል ታላቅ ህዝባዊ ንቅናቄ ተዘጋጅቷል።

አፈፃፃሙ ሁሉም በእያለበት በተናጠል ሆነ በጋራ በመሆን እጃችን ቸብ! ቸብ! በማድረግ በጭብጨባ እኔ ፋኖ ነኝ ማለት ይኼንን በተንቀሳቃሽ ምስል በማስቀረት በማህበራ ሚዲያ ማለትም በፌስቡክ፣ በቴሌግራም፣ ቲክቶክ፣ ዩቱዩብ ወዘተ በማጋራት እንዲሁም ለተለያዩ የአማራ የሚዲያ ተቋማት እና ባለሞያዎች ማጋራት ነው። በዚህ ታላቅ አማራዊ ንቅናቄ ሁሉም እንዲሳፍ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

ይህ ወሳኝ ተግባር የአማራ ፋኖ እየከፈለ ከሚገኘው የደም መስዕዋትነት አንፃር እጅግ ቀላሉ ነው። ስለሆነም ለዚህ ቀላል ነገር ግን ታላቅ አማራዊ ንቅናቄ ሁላችንም ከዛሬ ጀምሮ እንድንዘጋጅ የአማራ ወጣቶች ማህበር ለተከበረው የአማራ ህዝብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።

በመጨረሻም "ፋኖነት" ከተሰኘው የጌትነት ይርሳው ድንቅ መፅሃፍ የተገኘውን ስንኝ እየጋበዝን ሁሉም ለተደረገው ጥሪ ተግባራዊነት እንበርታ እንላለን።

ይቅርብሽ ነሐሴ በጭቃ እንዳትወደቂ
እንዳትመጭ ሰኔ ጥሩ ቀን ዕወቂ
ፋኖ ከጠራሽ ግን መስከረም ዝለቂ።

ፋኖ ገና ገና ፋኖ ገና ገና
የነሐሴው መብረቅ የሐምሌው ደመና።

ቋንቋ ይለመዳል ድሮም መግባቢያ ነው
ታሪክ ሚወረስ ግን ከአያት ቅድመ አያት ነው።

አንገት ደፍቶ መኖር ከመሰለው ሞኝ
እኔስ የጀግና ዘር የነፍጠኛ ነኝ።

እኔስ በውሻዎች ስፈራ ስፈራ
እኔስ በቀበሮ ስፈራ ስፈራ
ነብሩ ደረሰልኝ አቤት የአምላክ ሥራ።

ድል ለአማራ ፋኖ ‼️
ድል ለአማራ ህዝብ‼️

የአማራ ወጣቶች ማህበር

30/07/2023

“አፍሪካ አዲስ የሀይል ማዕከል እየሆነች ነው”- ፕሬዝዳንት ፑቲን

የሩሲያ ፕሬዝዳንት በሩሲያ አፍሪካ ጉባዔ መዝጊያ ላይ ባደረጉት ንግግር የአፍሪካ የኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ሚና እያደገ መጥቷል ማለታቸውን አርቲ ዘግቧል።

"የምዕራባዊያን ሀገራት ተጽዕኖ በተቃራኒው እየቀነሰ መጥታል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ "አፍሪካ አዲስ የሀይል ማዕከል እየሆነች ነው" ሲሉም አክለዋል።

ይሁንና በአፍሪካ አሁንም የቅኝ ግዛት አመለካከት አልተወገደም የሚሉት ፕሬዝዳንት ፑቲን ይህ አመለካከት በቀድሞ ቅኝ ገዢ ሀገራት በግልጽ ይንጸባረቃልም ብለዋል።

ተጨማሪ ዝርዝር በተከታዩ ሊንክ ያንብቡ፤ https://am.al-ain.com/article/putin-africa-new-center-of-power

13/07/2023

በዛሬዋ ኢትዮጵያ በ "ይሉኝታና መሽኮርመም" የሚከወን ፖለቲካ፤ የሚገኝ ወዳጅነት የለም። ሌላውን አጥፍቶ ኢምፓየር ለመመስረት የሚውተረተር ሰልፈኛ ከታች እና ከላይ ሰቅዞ ይዞህ "ሀገሪቷ እንዳትፈርስ" የሚል ነጠላ ዜማ የምታዜም ከሆነ በፍርስራሿ ለመቀበር ወስነሃል ማለት ነው።

በዚህ ስርዓት እያንዳንዱ "ክልል" ዲ'ፋክቶ ሪፐብሊክ ነው፤ እያንዳንዱ "ብሔር" በህግ ሉዓላዊ ነው። ከዚህ እውነታ አታፈንግጥ፤ ኢትዮጵያ ያንተ ብቻ አይደለችም፤ ቤተክርስቲያን ያንተ ብቻ አይደለችም። በሁለቱም ጉዳይ እንደሌላው ኢትዮጵያዊ ድርሻህን ጠይቅ፣ የድርሻህን ተወጣ ..... በመጀመሪያ እኔም የማልደፈር ሉዓላዊ ነኝ ከሚለው ጀምር።

26/12/2022

Address

Gonder

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fanus Nega .ፋኑስ ነጋ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category