Haramaya University Hiwot Fana Comprehensive Specialized Hospital

  • Home
  • Ethiopia
  • Harar
  • Haramaya University Hiwot Fana Comprehensive Specialized Hospital

Haramaya University Hiwot Fana Comprehensive Specialized Hospital Hiwot Fana Comprehensive University Hospital (HFCSUH) is a central teaching and referral hospital under Haramaya University.

It serves an estimated 20-30 million population in Eastern Ethiopia.

07/01/2026
 !  !ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት (ገና) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!Hordoftoonni amantaa kiristaanaa hundi baga guyyaa...
07/01/2026

!
!

ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት (ገና) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
Hordoftoonni amantaa kiristaanaa hundi baga guyyaa dhaloota Iyeesuus kiristoos (ayyaana qillee) nagayaan geessan !

በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የደስታና የበረከት በዓል ይሁንላችሁ!
Ayyaannichi kan nagayaa, jaalalaa, gammachuu fi milkii isiniif haa tahu !

መልካም የገና በዓል
Ayyaana gaarii

ታህሣስ 29/2018 ዓ.ም
Mudde 29,2018

ኑሮዋቸውን በውጭ አገር ያደረጉ የባቢሌ ከተማ እና አካባቢው ተወላጆች ለባቢሌ ጤና ጣቢያ የህክምና መስጫ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረጉ።በድጋፋ ለቀዶ ህክምና ፣ ለማዋወለጃ ፣ የህፃናት ማሞቂያ የሚ...
07/01/2026

ኑሮዋቸውን በውጭ አገር ያደረጉ የባቢሌ ከተማ እና አካባቢው ተወላጆች ለባቢሌ ጤና ጣቢያ የህክምና መስጫ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረጉ።

በድጋፋ ለቀዶ ህክምና ፣ ለማዋወለጃ ፣ የህፃናት ማሞቂያ የሚሆኑ መሳሪያዎች እና የተለያዩ መድሀኒቶች ያካተተ ድጋፍ መሆኑ ተገልጿል።

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከ C.U.R.E project እና ከተለያዩ የዳያስፖራ ማህበራት ጋር በመተባበር በኦሮሚያ ክልል ባሉ 11 ዞኖች እና አንድ ከተማ አሰተዳደር ስር ለሚገኙ 28 ጠቅላላ ሆስፒታሎች እና 9 ጤና ጣቢያዎች ድጋፍ ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ መሆኑን የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ መሀመድ ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ግምቱ 1.7 (አንድ ነጥብ ሰባት) ቢሊየን ብር የሚሆን 30 የህክምና ቁሳቁሶችን የጫኑ ኮንቴነሮችን የመርከብ እና አጠቃላይ የጉሙሩክ ቀረጥና ትራንስፖርት ወጪ እስከ 20 ሚሊየን ብር በመሸፈን ለየጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ማስረከቡን ዶ/ር አህመድ መሀመድ አስታውቀዋል ።

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ሚስኪ መሀመድ በጤናው ዘርፍ በርካታ ማነቆዎች ቢኖሩም ችግሮቹን ለመፍታት በሚደረገው ርብርብ ሁሉም ተሳታፊ ሊሆን እንደሚገባ እና እንደ ሁንዴ አለማቀፍ ልማት ተቋም እና ሌሎች የዳያስፖራው ማህበራት ከሐረማያ ዩኒቨርስቲ እና C.U.R.E project በመተባበር እያደረጉ ላለው ድጋፍ አመስግነዋል ።

ጤና የልማት መሰረት በመሆኑ እየተመዘገቡ ያሉ የልማት ውጤቶች የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ጤናው የተጠበቀ እና ምርታማነትን ለመሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል ።

በድጋፍ የተገኘውን ህክምና መስጫ ቁሳቁሶች የባቢሌ ጤና ዘርፍ አመራሮችና ባለሞያዎች በአግባቡ ጥቅም እንዲሰጡ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይጠበቅባችኋል ሲሉ ወ/ሮ ሚስኪ መሀመድ አስገንዝበዋል ።

ቀደምሲል በጤና ጣቢያው ለቀዶ ህክምና አገልግሎት የሚሆን ክፍል መገንባቱን እና በህክምና ቁሳቁሶች እጥረት ስራ ያልጀመረ በመሆኑ አብዛኛውን ታካሚዎችን ለእንግልት ይዳርግ ነበረ አሁን በተገኘው ድጋፍ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጤና ቢሮ ኃላፊ አት አብዱላዚዝ አብዱራህማን ገልፀዋል ።

በድጋፍ ርክክቡ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፣ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፣ የባቢሌ ከተማ አመራሮች ፣ አባ ገዳዎች ፣ አደ ሲንቄ ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ የባቢሌ ከተማ ነዋሪዎች እና ጤና ባለሞያዎች ተገኝተዋል ።

ዘጋቢ : ታደለ ጥላሁን
ፎቶ ግራፈር : በሐይሉ ግርማ
ታህሳስ 28/2018ዓ.ም
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Hospitaalota fi Buufataalee fayyaa Godina Harargee Bahaa fi lixaatti argamanif Deeggarsa Meeshaalee wal'aansa taasifame....
07/01/2026

Hospitaalota fi Buufataalee fayyaa Godina Harargee Bahaa fi lixaatti argamanif Deeggarsa Meeshaalee wal'aansa taasifame.

Deeggarsa Birri Billiyona 1.7 tilmaamamu karaa dhaabbata Pirojekti C.U.R.E,dhaabbata gargaarsaa fi misooma (Lammiif Relief and Development organization) fi Islamic Reliefin deeggarsa meeshaalee yaala fayyaa gara garaa Hospitaaloota 28 fi Buufataalee fayyaa 9 godina Harargee Bahaa fi lixaatti argamanif taasifamaa jira.deeggarsichi gara biyya keessa akka galuu taasisuf Hawaasa Diyaaspooraa Jaarsoo (Jarso Diaspora Community) deeggarsa baasii geejjibaa taasisaniru.

Yuunivarsiitiin Haramaayaa konteenaroota gara biyya keessa galan adeemsa seeraa barbaachisuu akka guutan taasisuu fi taaksii irraa bilisaan dhaabilee fayyaaf akka gahuu taasisuu irratti gumaacha olanaa taasisu isaa ibsamera.

Daayreektara olaanaa Yuunivarsiitii Haramaayaa kolleejji saayinsii fayyaa fi wal'aansa kan ta'an Dr.Ahmad Mahammad yaada kennanin yuunivarsiitiin Haramaayaa Hawaasni diyaaspooraa dhaabilee fayyaaf deeggarsa akka taasisan karaa garsisuuf marii gara garaa taasisa akka ture eerani,deeggarsichi hawaasni bakkuma jirutti tajaajila fayyaa fooyya'a akka argatu kan deeggaru ta'u dubbataniru.

Sirna walharkaa fuudhinsa meeshaalee wal'aansa fayyaa kanarratti I/Gaafatamaan waajjira fayyaa Godina Harargee Bahaa Obbo Abdulaziz Abdurahman,kantibaa Bulchinsa Magaalaa Baabbilee obbo Ahmadnajaash Abduraman,I/Gaafatamaa waajjira fayyaa Bulchinsa Magaalaa Baabbilee obbo Dachaasaa Damee argamaniru.

I/Gaafatamaan waajjira fayyaa Godina Harargee Bahaa Obbo Abdulaziz Abdurahman yaada kennanin wal gargaarun waliin jireenya ilma namaa keessatti hojii gaarii akka ta'e eerani,deeggarsi taasifame tajaajila fayyaa si'ataa fi dhaqabamaa ta'e hawaasa Aanichaaf akka kennu kan deeggaruu ta'uu dubbataniru.

Gabaasaan: Bahaayiluu Mokonin
Suuraa: Bahaayiluu Girmaa
Mudde 28/4 /2018
kutaa sab-qunnamti Yuunivarsiitii Haramaayaa koolleejjii saayinsii fayyaa fi wal'aansa

Duub deebii to'anno Field Epidemiology fi  Kallattilee itti aanuf karoora waloo qopheessuf waltajjii marii qooda fudhatt...
01/01/2026

Duub deebii to'anno Field Epidemiology fi Kallattilee itti aanuf karoora waloo qopheessuf waltajjii marii qooda fudhattoota waliin gaggeeffame.

Yuunivarsiitii Haramaayaa sagantaa Field Epidemiology suuparviishinii deeggarsaa fiildii beezii afur qabu irratti taasisee ilaalchisun duub deebii dhageeffachuf akkasumas hudhaalee fi milkaa'inoota qunnaman irratti mari'achun hojii itti aanuf kallatti fula duraa kaa'u fi karoora waloo qopheessuf waltajjii marii gaggeessera.

Ministeera fayyaatti Qindeessaa sagantaa Field Epidemiology kan ta'an Obbo Tasfaayee Digaafee ergaa dabarsanin sagantaa Field Epidemiology Yuunivarsiitii Haramaayaa sadarkaa biyyooleessaa fi idi-adunyaati beekkamti (accreditation) akka argatu gochuuf karoora qindaawaan hogganamu akka barbaachisu eerani, hojii Field Epidemiology keessatti huudhaalee qunnaman furuuf qooda fudhattoonni karaa ijaaramen fi qindominaan hojjechu akka qaban dhaamaniru.

Yuunivarsiitii Haramaayaa kollejjii saayinsi fayyaa wal'aansa Mana barumsa fayyaa hawaasatti Qindeessaa hojii Field Epidemiology kan ta'an Abdi Birhanu yaada kennanin kallatti ministeera fayyarra kaa'ame buu'ura gochuun hanqinoota adda bahan akka galtee karoora hojii itti aanutti fudhatame karoora waloo kan qophaa'e ta'u isaa ibsaniru.

Waltajjichaarratti sagantaa Field Epidemiology keessatti rakkoolee qunnaman fi muxxannowwan gaggaarii ( Best practices) adda baasuuf marii gadi fageenya gaggeessudhaan karoora hojii qindaa'a kan waloo (joint action plan) qophaa'e gamaaggamame akka mirkanaa'u taasisun hojiiraa akka ooluu kallattin kaa'mera.

Gabaasaan: Bahaayiluu Mokonin
Suuraa: Bahaayiluu Girmaa
Mudde 22/4 /2018
kutaa sab-qunnamti Yuunivarsiitii Haramaayaa koolleejjii saayinsii fayyaa fi wal'aansa

የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ትምህርት መርሀግብር ትግበራ ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለይቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ማቀድ  ውጤታማ እንደሚያደርግ ተገለፀ ። የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከጤና ሚኒስቴር ጋ...
01/01/2026

የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ትምህርት መርሀግብር ትግበራ ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለይቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ማቀድ ውጤታማ እንደሚያደርግ ተገለፀ ።

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚተገብረው የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና መርሀግብር ቀጣይነት እና የስልጠና አሰጣጥ ጥራቱን ለማሻሻል ያለመ ከጤና ሚኒስቴር ፣ የመስክ ልምምድ ሜድረጊያ ማዕከላት ተወካዮችና ሜንተሮች ፣ ከመምህራንና ሰልጣኞች ጋር ከድጋፋዊ ክትትል የተነኙ ክፍተቶችንና ተግዳሮቶችን መሰረት ያደረገና ወደፊት በጋራ የሚሰሩ የመፍትሄ ስራዎች ላይ ያተኮረ የጋራ እቅድ ዝግጅት ምክክር ተካሄደ ።

በጤና ሚኒስቴር የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ፕሮግራም አማካሪ እና አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ድጋፌ እንደገለፁት የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አመራሮች ለፕሮግራሙ የሰጡት ከፍተኛ ትኩረት በምስራቁ የአገሪቱ ክፍል የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና መርሀግብር በተሻለ ደረጃ ተግባራዊ እንዲሆን አስችሎታል ብለዋል ።

ከተለያዮ ባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ የመወያየትና የመስራት ባህልና አሁን እየታየ ያለው መነሳሳት መጠናከር እንዳለበትና ቋሚ የሆኑ የውይይት መድረኮች መበረታታት እንዳለባቸውና የበለጠ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

እቅድ ዝግጅቱ ቀደም ብሎ ከዮኒቨርሲቲውና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በመስክ ልምምድ ማድረጊያ ጣቢያዎች ማለትም በድሬደዋ አስተዳደር፣ በሶማሌ ክልልና ሀረሪ ጤና ቢሮዎች ፤ እንዲሁም በኦሮምያ ክልል በምስራቅ እና ምእራብ ሐረርጌ ዞን ጤና ፅ/ቤት የተደረገውን የድጋፋዊ ክትትል አካል የሆነውን የአፈፃፀም ግምገማ ተከትሎ የተገኙ ልምዶችን ፣ መልካም አጋጣሚዎች እና ክፍተቶችን መሠረት ያደረገ መሆኑን በሐረማያ ዩኒቨርስቲ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ትምህርት መርሀግብር አስተባባሪ አቶ አብዲ ብርሀኑ ጠቁመዋል ።

በዚህ የምምክክር መድረክም በተለዩ ክፍተቶችና ተግዳሮቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል የጋራ እቅድ ዝግጅት ተከናውኗል ።

ይህን ተግባራዊ ለማድረግም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሀላፊነት መወጣትና ፕሮግራሙ በላቀ ደረጃ ውጤታማ እንዲሆን ርብርብ እንዲያደርጉ አቶ አብዲ ጥሪ አቅርበዋል ።

የፕሮግራሙ ሰልጣኞች በበኩላቸው በመስክ ላይ ያገኘናቸውን እውቀት እና ክህሎቶችን በመጠቀም በመስክ ላይ ያከናወኗቸውን ተግባራት በተመደቡበት የመስክ ልምምድ ሜድረጊያ ጣቢያዎች ላይ ማቅረባቸውና በቦታው ላይ በተገኝተው ከፍተኛ መምህራን መገምገማቸው እንዳስደሰታቸው የገለፁ ሲሆን፤ የዚህ አይነት ተሞክሮም በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ላይ የጋራ መረዳት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል። ሁሉም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የጋራ የመፍትሄ እቅድ ማቀድ መቻሉ ለቀጣይ ትግበራ አቅም የፈጠረ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል ።

የሰልጠና ፕሮግራሙ በተለይ በድህረ ምረቃ ደረጃ የሚሰጠው የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና በ2022 እኤአ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና (accreditation) የተሰጠው ሲሆን፤ ይህ እውቅና ለአምስት አመት የሚቆይ በመሆኑ በሚቀሩት ግዚያት እውቅናውን ለማደስ የመረጃ አያያዝ ሂደትና በአግባቡ ሰንዶ የማስቀመጥ ሁኔታ ዋነኛው መስፈርት በመሆኑ በመስክ ምልከታችን ወቅት ከሰነድ አያያዝ ጋር የታዘብናቸው ክፍተቶችን በጋራ ለመቅረፍ የድጋፍ ክትትል ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል በማለት በሐረማያ ዩኒቨርስቲ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ፕሮግራም ሬዚደንት አማካሪ አቶ ለማ ቦጋለ ተናግረዋል ።

የምእራብ ሐረርጌ ዞን የፊልድ ሜንተር የሆኑት አቶ ዘመድኩን አስታጥቄ እንዳሉት በተለዩ ክፍተቶች ላይ ማሻሻያ ለማድረግ እና የትምህርት ጥራትንና ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሚረዳ የእርስበርስ ልምድ ልውውጥና ምክክር መደረጉን ገልፀው በጋራ እቅድ ማውጣታችን በቀጣይ ሰልጣኞች ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዲችሉ ከኛ የሚጠበቅብንን ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለናል ብለዋል ።

የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ትምህርት መርሀግብር በባህሪው 75 በመቶ የሚሆነው በመስክ ላይ የሚደረግ ትግበራ በመሆኑ ባሉ ክፍተቶች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር አቅዶ መስራት ችግሮችን መፍታት እና ብቁ ባለሞያችን ማፍራት ያስችላል ተብሏል ።

ዘጋቢ ታደለ ጥላሁን
ታህሳስ 21/2018 ዓ.ም
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Miseensota koree Gamaaggama Naamusa Qorannoo fayyaa Yuunivarsiitii Haramaayaa koollejjii Saayinsii fayyaa fi wal'aansati...
31/12/2025

Miseensota koree Gamaaggama Naamusa Qorannoo fayyaa Yuunivarsiitii Haramaayaa koollejjii Saayinsii fayyaa fi wal'aansatif Leenjii Ijaarsa Dandeetti kennamu ture xumurame

Leenjicha kan qopheesse Daayreektooreeti dhimma korniyaa fi HIV/AIDS Yuunivarsiitii Haramaayaa koollejjii Saayinsii fayyaa fi wal'aansa Institiyuuti Qorannoo Armaur Hasen ( AHRI) waliin ta'un yammu ta'u leenjicgii guyyaa Afurif Miseensota koree Gamaaggama Naamusa Qorannoo fayyaatif kennamera

Yuunivarsiitii Haramaayaa koollejjii Saayinsii fayyaa fi wal'aansatti Daayreektara Daayreektooreeti dhimma korniyaa fi HIV/AIDS kan ta'an Dr.Fatiyaa Mahammad yaada kennani qorannowwan fayyaa gaggeeffamu qajeeltoowwan naamusa qorannoo eegani akka gaggeeffaman ijaarsa dandeetti Miseensota koree Gamaaggama Naamusa dhaabbatummaa Qorannoo fayyaa cimsuuf fi hubannoo walfakkata akka qabaatan taasiisuf leenjiichii faayidaa gudda akka qabu eerani, koree Gamaaggama Naamusa Qorannoo fayyaa keessatti hirmaannaa dubartoota akka cimuu taasisuuf yaadame leenjii qophaa'e akka ta'e ibsaniru.

Koollejichaatti waliitti qabaan koree Gamaaggama Naamusa Qorannoo fayyaa kan Dr.Naggaa Baaraakii yaada kennanin qorannoowwan fayyaa gaggeeffamu duudhaa,Aadaa, naamusaan fi karaa saayinsawaa eeggaten gaggeeffamu akka qabu eerani, leenjichi hubanno fi dandeetti Miseensota koree kan cimsee fi miseensota haaraaf wal qooddannaa muxxannoo kan itti taasifame ta'u ibsaniru.

Hirmaattonni leenjichaa yaada kennanin leenjichi Miseensota koree dhimma naamusa qorannoo fayyaa irratti hubannoo walfakkata akka qabaatan kan taasisee akka ta'e eerani, leenjiin ijaarsa dandeetti kun itti fufiinsan kennamu akka qabu ibsaniru.

Gabaasaan: Bahaayiluu Mokonin
Suuraa: Bahaayiluu Girmaa
Mudde 19/4 /2018
kutaa sab-qunnamti Yuunivarsiitii Haramaayaa koolleejjii saayinsii fayyaa fi wal'aansa

31/12/2025
30/12/2025
በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ የድህረ ምረቃ መርሀግብር ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ (theory) ያገኙትን እውቀት በመስክ ልምምድ (field activitie...
29/12/2025

በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ የድህረ ምረቃ መርሀግብር ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ (theory) ያገኙትን እውቀት በመስክ ልምምድ (field activities/ residency) ክህሎት በማዳበር ከሚጠበቅባቸው የመስክ ልምምድ ውጤቶች (outputs) ጋር በማዛመድ የተግበሯቸውን ስራዎች በግብረ መልስ (report) መልክ በኮሌጁ ከፍተኛ መምህራኖች፣ ሜንተሮችና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጤና ፅ/ቤት በሚገኘው ፊልድ ቤዝ አቅርበዋል ።

ሰልጣኞቹ እውቀት እና ክህሎታቸውን ተጠቅመው መረጃን የማሰባሰብ የመተንተንና ሳይንሳዊ ይዘት ያለው አቀራረብን መከተላቸውንና የተገኙ ውጤቶችን በዩኒቨርስቲው ከፍተኛ መምህራንና በሌሎች ባለሙያዎች ተገምግሟል ።

በተጨማሪም የፕሮግራሙ አሰጣጥ ሂደትን አተገባበር እና የመረጃ አደረጃጀት በተቀመጠው የመመዘኛ መስፈርቶች ልክ መዝኖ እውቅና ማግኘት የሚያስችል ደረጃ ላይ መሆኑን በድጋፋዊ ክትትሉና በመስክ ጉብኝት ልኡካኑ ግምገማ ተደርጓል ።

ከታህሳስ 14-16/ 2018 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ፣ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ፣ በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ ጅግጅጋ እና በሐረሪ ክልል ጤና ቢሮ ሀረር ከተማ ላይ የሚገኙ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ የመስክ ልምምድ ማድረጊያዎች (field bases) ውስጥ ያሉ የሰነድ ዝግጅቶች እና የሰልጣኞች የስራ ውጤቶች ግምገማ በማድረግ የድጋፋዊ ክትትሉና በመስክ ጉብኝቱ ተጠናቋል።

የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ሰልጣኞች በዩኒቨርስቲ ውስጥ የሚሰጣቸውን የንድፈ ሀሳብ እውቀት በመስክ ላይ መተግበራቸው ለማረጋገጥ በጋራ ክትትልና ድጋፍ መደረጉ ብቁ ሙያተኞችን ማፍራት ያስችላል ተብሏል ።

ዘጋቢ:- ታደለ ጥላሁን
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ህዝብ ግንኘነት ክፍል

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ለምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።የጤና ምርምሮችን ለማከናወን አለማቀፍ እና አገር አቀፍ የስነ-ምግባር መርሆዎች እና...
29/12/2025

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ለምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

የጤና ምርምሮችን ለማከናወን አለማቀፍ እና አገር አቀፍ የስነ-ምግባር መርሆዎች እና ድንጋጌዎችን ምንድናቸው እንዲሁም ማህበረሰቡ በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ተሳትፎ እንዲያደርግ መሟላት ባሉባቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል ።

በማህበረሰብ ውስጥ ተጋላጭ ለሆኑ ነብሰጡር እናቶች ፣ ህፃናት እና የአእምሮ ህሙማን ተሳታፊ ሲሆኑ ጠቀሜታው እና ጉዳቱን በተጨማሪም የሰውሰራሽ አስተውሎት እና የዘረመል ምርምር ጉዳዮችን በተመለከተ ያሉ መስፈርቶችና የስነ-ምግባር መርሆዎች ላይ ግንዛቤን የሚፈጥር ስልጠና መሆኑን በ(AHRI) አርማውር ሐንሰን ምርምር ማዕከል ፓን አፍሪካን ኢኒሺዬቲቭ አስተባባሪ ዶ/ር ሐይለሚካኤል ጌታቸው ገልጸዋል ።

በኮሌጅ የስርዓት ፆታ እና ኤችአይቪ ኤድስ ቢሮ አስተባባሪነት ወደ ምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ ውስጥ የተካተቱ አዲስ ሴት አባሎች እና ለነባሮችም አቅም ለመገንባት ያለመ ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመው ይህም ኮሚቴው አለማቀፍ እውቅናን ለማገኘት ከተሰጡት ግብረ መልሶች የፅዖታ ተዋፅኦ በተመለከተ ከፍተኛ ማሻሻያ ማድረጉን ዶ/ር ፈቲሐ መሀመድ ገልፀዋል ።

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ነጋ ባራኪ በበኩላቸው የምርምር ስራዎች በምንም አይነት ከሰዎች መብት እና ደህንነት ጋር ግጭት የሚፈጥሩ የማህበረሰቡን ባህል እና እሴት የሚጎዱ መሆን የለባቸውም ለዚህም የጤና ምርምር ስነ-ምግባር ለችግሩ መፍትሔ ሰጪ መሆኑን አስረድተዋል ።

ቀደም ሲል ከታይላንድ በመጡ አለማቀፍ ገምጋሚ ቡድን የምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ አለማቀፍ እውቅና ለማግኘት በተደረገው ግምገማ የታዩ ውስን ክፍተቶች ላይ ማስተካከያ መረጉንና በተለይ በፅዖታ ተዋፅዖ ከፍተኛ ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል ።

እንደ ማህበረሰብ የሚሰሩ ምርምሮች በዋናነት ያሉ የጤና ችግሮችን ለመፍታ ከመሆኑ አንፃር የማህበረሰቡን ፍላጎት መረዳትና ማወቅ ይገባል ለዚህም የምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴው ያደረጋቸው ማሻሻያዎች እና የተሰጠው ስልጠና የጋራ መረዳት እንዲኖረን አስችሎናል ያሉት በኮሚቴው የማህበረሰብ ተወካይ ወ/ት የምስራች ጌታቸው ናቸው።

የማህበረሰቡን ደህንነት ፣ባህል እና እሴት የጠበቀና ያከበረ የጥናትና ምርምር ስራዎች የበለጠ እንዲስፋፋ መሰል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባም ተገልጿል።

ዘጋቢ ታደለ ጥላሁን
ፎቶ ግራፈር በሐይሉ ግርማ
ታህሳስ 19/2018 ዓ.ም
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haramaya University Hiwot Fana Comprehensive Specialized Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram