ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department

ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department This is the official page of Hadiya Zone Health Department. ይህ የሃድያ ዞን ጤና መም

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር  ጤና ጥ/ጽ/ቤት በወባ ወረርሽኝ መከላከልና አጎበር አጠቃቀም እንዲሁም የተፋጠነ ታላሚ ተኮር የህጻናት ክትባት ዘመቻ አፈፃፀም ሁሉም ባለድሻ አካላት በተገ...
07/11/2025

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት በወባ ወረርሽኝ መከላከልና አጎበር አጠቃቀም እንዲሁም የተፋጠነ ታላሚ ተኮር የህጻናት ክትባት ዘመቻ አፈፃፀም ሁሉም ባለድሻ አካላት በተገኙበት ገመገመ ።

*******ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ****

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት በወባ ወረርሽኝን መከላከልና አጎበር አጠቃቀም እንዲሁም የተፋጠነ ታላሚ ተኮር የህጻናት ክትባት ዘመቻ ማጠቃለያ አፈፃፀም ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በመገምገም በቀጣይ አቅጣጫ ላይ ውይይት አደረገ ።

በውይይት መድረኩ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬን ጨምሮ የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ እና ማኔጅመንት ፥ ከሆስፒታልና ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ፣ ከእናቶችና ህፃናት ፣ ከመረጃ ኦፊሰር እና ከጤና ኤክስቴንሽኖች ተሳትፈዋል።

የተፋጠነ ታላሚ ተኮር የህጻናት ክትባት ዘመቻ ሪፖርት በእናቶችና ህፃናት አገልግሎት ክፍል ኃላፊ በአቶ አማረ ማርቆስና የወባ መከላከልና መቆጣጠር ስራ ሪፖርት በጽ/ቤቱ ኃላፊ በአቶ ኤልያስ ዳዊት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል

በውይይት መድረኩ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ በክትባት ዘመቻው ይበል የሚያሰኝ ጠንካራ ስራ መሰራቱን አውስተው በቀጣይም በመደበኛው የክትባት ስራ ላይ አጠናክሮ በመስራት ባለመከተብ የሚመጡ ወረርሽኞችን መከላከል እንደሚገባ አሳስበው ከወባ መከላከልና መቆጣጠር ስራዎችም ጋር ተያይዞ የሚታይ ስራ መሰራቱን ገልፀው አጎበር ያለው በአግባቡ እንዲጠቀም ማስተማር እንደሚገባ በመግለጽ የታመሙትንም መመርመርና ማከም እንደሚገባ ገልፀዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት በበኩላቸው የተፋጠነ ታላሚ ተኮር የህጻናት ክትባት ዘመቻ ዋናው አላማ ክትባት ያልጀመሩትን ፈልጎ በማግኘት እንዲጀምሩ ማድረግ ፣ ክትባት ያቋረጡትን ማስቀጠል እና የሚዝል ክትባት በወቅቱ እዲወስዱ ማድረግና ሌሎችም በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎችን አቀናጅቶ መስራት ሲሆን በዚህም አመርቂ ውጤት መምጣቱንና ለዚህም ስኬት በትጋትና በቁርጠኝነት የሰሩ ባለድርሻ አካላትን ያመሰገኑ ሲሆን በመልሶ ማረጋገጥም የተሻለ መሆኑን በመግለጽ ነገር ግን በዘመቻው የተገኙ ህፃናትን ተከታትሎ ክትባት ማስጨረስ እንደሚገባ አሳስበዋል ከወባ ጋር በተያያዘም ብቸኛው አማራጭ በተጀመረው መንገድ የአካባቢ ቁጥጥር ስራውን አጠናክሮ መስራት ነው ያሉ ሲሆን ከአልጋ አጎበር አጠቃቀም ጋርም ተያይዞ ከ5 ዓመት ወዲህ ምንም አይነት የልጋ አጎበር ስርጭት እንዳልተደረገ አንስተው ህዝቡ በእጁ ያለውን እንዲጠቀም ማድረግ ይገባል በማለት በቀጣይም በቅንጅት ሁሉንም አይነት አደረጃጀት በመጠቀም የህዝባችንን ጤና መጠበቅ እንዲሁም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወባ ስጋት እንዳይሆን ማድረግ ይገባል በማለት የተለያዩ የስራ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎቹ ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ ምላሽና ማብራሪያ ከመድረክ ተሰጥቷል የእለቱ ፕሮግራም ተጠቃሏል።

ምንጭ:-የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥ/ጽ/ቤት) ሾኔ
ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ

በጊምቢቹ ከተማ የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ደሳለኝ ሽጉጤ በተገኙበት አጠቃላይ የክላስተሩ የጤና ስራዎች ያለበት ደረጃ እየተገመገመ ይገኛል። ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ጊምቢቹ:-በ...
05/11/2025

በጊምቢቹ ከተማ የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ደሳለኝ ሽጉጤ በተገኙበት አጠቃላይ የክላስተሩ የጤና ስራዎች ያለበት ደረጃ እየተገመገመ ይገኛል።

ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ጊምቢቹ:-

በጊምቢቹ ከተማ አጠቃላይ የክላስተሩ የጤና ስራዎች ያለበት ደረጃ እየተገመገመ ይገኛል።

የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ደሳለኝ ሽጉጤ በዚህ ወቅት እንደገለፁት ወቅቱን ጠብቆ የሚነሳ የወባ ወረርሽኝ መከላከልን የመቆጣጠር ተግባራትን መጠናከር የሚቻልበትን ሁኔታ በተመለከተ ፣የትራንስፎርሜሽን አጀንዳ በሁሉም ጤና ተቋማትና ጤና ጽ/ቤቶች እየተገመገመ ተግባራዊ መሆን እንዳበለት፣ሣምንታዊ የሪፖርትና የግምገማ ስርዓት በጽ/ቤት፣በጤና ተቋማት ፣በጤና ኬላ፣በቀበሌ ጭምር እየተገመገመ መሰራት እንዳለበት ፣በቋሚነትና በጊዜያዊነት ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን ማፋሰስ በሚቻልበት ሁኔታ፣የአጎበር አጠቃቀም በተመለከተ ክትትል መደረግ እንዳለበት ፣የእናቶች ማቆያ በሁሉም ጤና ተቋማት ማጠናከር መገንባትና አገልግሎት መስጠት እንዲችል መደረግ እንዳለበት ፣የጤና አገልግሎቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት መረጋገጥ እንዳለበትና መደበኛ ስራዎች በተጠናከረ መንገድ እንዲሰራ ድጋፋው ክትትልና እየተገመገመ መመራት እንዳለበት ትኩረት ያደረገ ግምገማ መሆኑን አብራርተዋል።

በተጨማሪ ሁሉም ጤና ተቋማት 7/24 ሰዓት ክፍት ሆነው አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸውና የቤት ለቤት ድጋፋው ክትትል መደረግ እንዳለበት እንዲሁም ሁሉም የጤና ባለሙያዎችና የጤና ተቋማት አስተዳደር ሠራተኞች የፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ ትኩረት ተደርጎ መሠራት እንዳለበት ዶክተር ደሳለኝ አጽንኦት ሰጥተው በመድረኩ አሳስበዋል።

በግምገማው የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ደሳለኝ ሽጉጤ፣የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ልማት ዕቅድ አቶ ተስፋዬ ሐንዴ፣የጊምቢቹና የጃጁራ ከተማ አስተዳደሮች ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ማኔጅመንት አካላት እንዲሁም የሶሮ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ማኔጅመንት አካላት ፣የሶስቱም መዋቅሮች የጤና ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ምንጭ:-ጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር
ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ!!

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ በዶ/ር ደሳለኝ ሹጉጤ የተመራው የመምሪያው ቡዱን ዛሬም ከትላንቱ በቀጠለዉ ድጋፋዊ ክትትል በዞኑ በተወሰኑ ክላስተር በመዘዋወር ወቅታዊ የወባ መከላከልና መቆጣጠ...
04/11/2025

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ በዶ/ር ደሳለኝ ሹጉጤ የተመራው የመምሪያው ቡዱን ዛሬም ከትላንቱ በቀጠለዉ ድጋፋዊ ክትትል በዞኑ በተወሰኑ ክላስተር በመዘዋወር ወቅታዊ የወባ መከላከልና መቆጣጠር ተግባራት ያለበትን ደረጃ እና ሌሎች መደበኛ ተግባራትን እየገመገመ ይገኛል፦
‎ ********25/2/2018********
‎በዛሬው ዕለት በጎምቦራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤትና በሰጌ ጤና ጣቢያ ተገኝተው በወረደውና ከተማ አስተዳደር በተመረጡ ጎጦች ቤት ለቤት በመግባት የአከባቢ ቁጥጥር፤የአልጋ አጎበር አጠቃቀም፤የግልና አከባቢ ቁጥጥር፣ የፀረ ወባ መድኃኒት ሪጭት በሌሎችም በዞኑ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ተመልክቷል።

‎በሚልከታቸው ወቅት የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ እንደገለፁት በዞኑ የወባ በሽታ ስጋት ወደ መይሆንበት ደረጃ ለማድረስ ዘርፉብዙ ተግባራት እየተከናወነ እንደሆነ በመግለፅ ወባን ጨምሮ በወረርሽኝ መልክ ልከሰቱ የሚችሉ ተግባራትን ለመከላከል በሚደረገው እርብርብ ውስጥ በየደረጃው ያለው ሁሉም አካለት ተቀናጅተው መሠረት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

‎የመምሪያው ኃላፊ አያይዘው በዞኑ ሥራ ከሉት መዋቅሮች ውስጥ በምሥራቅ ባዳዋቾ፤በምዕራብ ባዳዋችና ጊቤ ወረደ የኬሚካል ሥርጭት ሥራ እየተሰራ እንደሆነና አፈፃፀሙ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ እንዲጠነቀቅ በዘርፉ ከፈተኛ ልምድ በላቸው ኤክስፐርቶች ክትትል እተየተደረገ መሆኑ ገልፀው ኬምከሉን በሁሉም አከባቢ ተደራሽ ለማድረግ እጥረት ማጋጠሙን በመግለፅ በሌሎች የመከለከሉና የመቆጣጠሩ ተግባራት ትኩረት መደረጉን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

‎በተጨማሪም የወባ በሽታን ለመከላከል ከዞኑ መንግስት ጀምሮ በልዩ ትኩረትና በቅርብ ክትትል እየተደረገ እንዳለ በመግለፅ በየደረጃው ያለው የጤና መዋቅር በተለይም የአከባቢ ቁጥጥር፤የአልጋ አጎበር አጠቃቀምና በሌሎችም ተግባራት በየደረጃው የመንግስትና የህዝብ ኃላፊነት ከለው አካለት በተጨማሪም ከህዝብ ጋር በመቀናጀት ተግባራትን በብቃት መምራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።

‎ከዚህም በተጨማሪ መደበኛ ተግባራትንም ጎን ለጎን እየተካሄደ ሲሆን የሆስፒታል ድጋፉ ቀጥሎ በዛሬው ዕለትም የሆስፒታል ሪፎርምን መሰረት ባደረገ መልኩ ሰፋ ያለ ጊዜ በሆመች የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሆኖ በጊቤ ወረዳ በሜጋቾ ጤና ጣቢያ በአጠቃላይ ተግባራት ላይ ገንብ ውይይት ማድረግተችሏል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ በሻሾጎ ወረዳና ቦኖሻ ከተማ አስተዳደር የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር  ሥራዎች እና ሌሎች መደበኛ ሥራዎች ላይ ድጋፍና ክትትል  ተደረገ።‎ ...
04/11/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ በሻሾጎ ወረዳና ቦኖሻ ከተማ አስተዳደር የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራዎች እና ሌሎች መደበኛ ሥራዎች ላይ ድጋፍና ክትትል ተደረገ።
‎ ********24/2/2018********
‎የመምሪያ ሀላፊን ዶ/ር ደሣለኝ ሹጉጤን ጨምሮ ሌሎች የማኔጅመንት አካላትና ባለሙያዎች በድጋፉ የተሣተፉ ሲሆን በሻሾጎ ወረዳ የወባ በሽታን ሥርጭት ለመግታት እየተሠሩ ያሉ ተግባራትን ቤት ለቤት በመግባት ለማየት ተችሏል።

‎በዞኑ በ2018 ዓ.ም በሻሾጎና በጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር የአጎበር ሥርጭት የተካሄደ በመሆኑና በቤተሰብ ቁጥር ልክም እንድደርስ የተደረገ በመሆኑ በቡድኑ ተግባሩን ቤት ለቤት ጉብኝት በማድረግና ትምህርት በመስጠት ብሎም የሥርጭቱንም ሂደት በተለያዩ ቀበሌያት(ጤናኬላዎች) በመገኘት መዝገባቸውን ለመፈተሽ ተችሏል። አጎበሮችን በአግባቡ መጠቀም የወባን ሥርጭት ለመከላከል አንዱና ዋነኛው ዘዴ(intervention) በመሆኑ ማህበረሰቡ የተሰጠውን አጎበር በተሰጠው ልክ በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ከድጋፍ ቡድኑ ለወረዳው ጤና ጽ/ቤት ግብረ መልስ የተሰጠ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የመከላከል ዘዴዎች የሆኑትን የአከባቢ ቁጥጥር ሥራ ፣ የታመሙትን ቶሎ ማከምና ሌሎችንም በሠራዊት መልክ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ማጠናከርና የወባ በሽታን ቁጥር ትርጉም ባለው መልኩ መቀነሥ እንድምገባ ከወረዳው ብሎም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር መግባባት ተችሏል።

‎ከመደበኛ ተግባራትም አንፃር በቦኖሻ ሆስፒታልና በዶዕሻ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም አጠቃላይ ተግባራት ላይ ክትትል የተደረገ ሆኖ በቀጣይ መሠራት ባለባቸው ነጥቦች ላይ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል። የቦኖሻ ሆስፒታል ከቅርብ ጊዜ ወድህ የተለያዩ ለውጦችን እየጨመረ አገልግሎቱን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እያደረገ መሆኑን በግልፅ ማየት የተቻለ ሲሆን በተለይም በቦርድ የተወሰኑትን በከተማ አስተዳደሩ መሠራት ያለባቸው ነጥቦች በአብዛኛው መተግበራቸውን ለማየት ተችሏል። በድጋፉ ወቅትም ከሆስፒታሉ ሲንየር ማናጅመንት ጋር ከሥምምነት ጋር የተደረሰው ነገር ተግባራቱ ከዚህም በበለጠ መሻሻልና የተጀመሩ ጅምር ተግባራትም የበለጠ መጠናከር እንዳለባቸው ሲሆን ለዝህም የተለያዩ በሆስፒታሉ መተግበር ያለባቸው የርፎርም ተግባራት ባላቤት ተሰጥቷቸው መመራት እንዳለባቸውና የሆስፒታል ጥራት ሥራ ላይ የበለጠ ትኩረት በሚደረግባቸው ሁኔታ ላይ በሥፋት መደጋገፍ ተችሏል።

‎በዶዕሻ ጤና ጣቢያም ድጋፍ የተደረገ ሆኖ ጤና ጣቢያው በጥሩ እንቅስቃሴ ያለ ቢሆንም የፈውስም ሆነ የመከላከሉን (curative and prevention) ተግባራትን የበለጠ አቀናጅቶ መምራት እንዳለባቸው መነጋገር ትችሏል። በተለይ ወቅታዊ በሆነ የወባን ሥርጭት የመከላከሉና የመቆጣጠሩ ሂደት ላይ በካችሜኑቱ ትርጉም ያለው ለውጥ ሊያመጣና ተግባሩንም በየጊዜው በRRT መገምገም እንዳለባቸው በሥፋት ተነሥቷል። ከዚህም በተጨማሪ በወረዳው መሪ ጤና ጣቢያ በመሆኑ የEPAQ ሥራዎችን ማጠናከር እንደምገባና የተጀመሩ ጅምር ሥራዎችን በማስፋት ሌሎች ጤና ጣቢያዎች ልምድ መውሰድ በምችሉት ልክ ማድረስ እንደምገባ መስማማት ተችሏል። ከዝህም በተጨማሪ በሆሳዕና ከተማ ልች አምባና ቦብቾ ጤና ጣቢያ ላይም የተለያዩ ድጋፍ ሥራዎች መሥራት ተችሏል።

ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም።የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስታፍ ፎረም እያካሄደ ይገኛል።በስታፍ ፎረም ላይ የ2017 ዓም እቅድ ክንውን በሆስፒታሉ የልማት እቅድ ክፍል አስተባባሪበአቶ አበበ...
31/10/2025

ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም።

የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስታፍ ፎረም እያካሄደ ይገኛል።

በስታፍ ፎረም ላይ የ2017 ዓም እቅድ ክንውን በሆስፒታሉ የልማት እቅድ ክፍል አስተባባሪበአቶ አበበ ሄሎሬ ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይት መድረኩ ላይ የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራአስክያጅ/CEO/ አቶ አብርሃም ሎምቤ እንዲሁም የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይረክተር /CCO/ ዶ/ር አሸናፊ ኤርሚያስን ጨምሮ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት የጤና ባላሙያዎች እና የጋራ አገልግሎት ሠራተኞች ተገኝተዋል።
ምንጭ:- ሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

በሀዲያ ዞን በጊምቢቹ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አጠቃላይ ድጋፍ እና በአመካ ወረዳ በፉገጃ ጤና ጣቢያ  የማህበረሰብ ወይይት መድረክ ተካሄደ                     **** 18...
29/10/2025

በሀዲያ ዞን በጊምቢቹ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አጠቃላይ ድጋፍ እና በአመካ ወረዳ በፉገጃ ጤና ጣቢያ የማህበረሰብ ወይይት መድረክ ተካሄደ
**** 18/2/2018ዓ/ም*******
ከዞን ጤና መምሪያ በተወጣጡ የባለሙያዎች ቡድን በጊምቢቹ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና በሶሮ ወረዳ አቡና ጤና ጣቢያ በመገኘት አጠቃላይ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ሆስፒታሉም ከዚህ በፊት ከምታወቅበት ከፍተኛ ችግር በመውጣት ሂደት ውስጥ እንዳለ ማየት ተችሏል የምመለከታቸው ክፍሎች ሆስፒታሉን ማገዝ ከቻለ ከዚህም የተሻለ ለውጥ ልመጣ እንደምችል ማሳያዎች አሉ። ከጤና ጣቢያ አንፃርም በአንፃራዊነት የተሻለ ነገር ማየት የተቻለ ሆኖ መስተካከል በሚያስፈልጉ ጉዳዮች በሥፋት ውይይት ተደርጓል። በሌላው መልኩ በአመካ ወረዳ በፉገጃ ጤና ጣቢያ በቀን 18/2/2018ዓ/ም የማህበረሰብ ወይይት መድረክ ተካሄደ
በዕለቱም ከወረዳ የተገኙ ባለድርሻ አካለት :-
የወረዳ ምክትል አስተዳደር
የጤና ጽቤት ኃላፊ
የፉይናንስ ኃላፊ
የፓብልክ ሰረቭስ ኃለፊ
የሴቶችና ህፃናት ኃላፊ
አጠቃላይ ጤና ጣቢያ ባለሙያዎች
የከችሜንቱ ተጠቃም ህብረተሰብ በሙሉ በተገኙበት አጠቀላይ በጤና ጣቢያ አገልግሎት ምክክር መድረክ ተካሄደዋል.
የጤና ጣቢያው ኃለፊ አጠቃላይ በአንደኛ ሩብ አመት የተሰሩ ስራዎችን አቅርቦ በመጨረሻም መድረኩን ከወረዳ ም/አስተዳደርና የጤና ጽ/ቤት ኃላፊው ተመርቶ ጤና ጣቢያ ለይ የለውን አጠቀላይ ለአገልግሎት ችግር የሆኑ ነገሮችን ለህብረተሰቡ በመቅረብ ለምሳሌ 👉
✍የጤና ጣቢያ ግንባታ መፈራረስ ችግርና ጣሪያ በሁሉም ክፊል ክረምት ስራ እንዳይሰራ በማፍሰሱ ለስራ ችግር መሆን
✍በግብ ውበት ለይ ሰፊ ችግር መኖር
✍በማዐጤመ አጠቃቀም ለይ ችግሮች መኖሩን
✍በአንቡላንስ አጠቃቀም ዙርያ ለይ
✍የመድኃኒት ችግር እንድፋታ
ከለይ የተዘረዘሩትን ችግሮች የምመለከተው አካል ግዜ ሰይሰጥ ማስተካከል እንደለበትና ህብረተሰቡ ለጤና ጣቢያ ግንባታ እድሳትና አጠቃላይ ለጤና ጣቢያ ስራ ችግር የሚሆነውን የወረዳ አስተዳደርና ቀበሌ ተነጋግረው በአስቸኳይ ለህብረተሰቡ እንዲያሳውቅና ከተጠቃም ህብረተሰብ ከመንግሥት ስራተኞች ከሀገር ወጭ የሉት የአከባቢው ተወላጅ ማህብረሰብ ከባለሀብቶች ሌሎችም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለመስራት በሙሉ ህብረተሰብ ስምምነት ለይ ድርሳን የዛሬውን ስብሳባ በስኬት ጨርሰናል ። ምንጭ የአመካ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት።
ጤና መምሪያ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን የተለያዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት"በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ ዕውቅናና ተጠያቂነት ለጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል አመታዊ የጤና ጉባኤ አካሄዱ።        ...
24/10/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሀዲያ ዞን የተለያዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት"በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ ዕውቅናና ተጠያቂነት ለጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል አመታዊ የጤና ጉባኤ አካሄዱ።

**********13/02/2018 *********

የየመዋቅሩ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥና ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ መዋቅራዊ አሰራሮችን በመከተል በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ በጉባኤው ተነስቷል .

ህብረተሰብ ጤናና ብልፅግና ዕውን ለማድረግ ህብረተሰቡ የራሱንና የአከባቢውን ንፅህና መጠበቅ አለበት በቀጣይ አከባቢው ላይ የወባ ሥርጭት እንዳይስፋፋ ለመከላከል በትኩረት ሊሠራ እንደምገባም ተነሥቷል።

በእለቱም የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ 2818ዓ/ም በዞን ደረጃ ህብረተሰቡን ተጠቀሚ በማድረግ ተሸላሚ ለመሆን በጥብቅ እንደምሰሰራ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በየመድረኩም የየመዋቅሩ የፊት አመራሮች፣ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ማኔጅሜንት፣የጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎችና ከሁሉም ጤና ተቋማት የምመለከተው አባለት ተገኝተዋል። በመጨረሻም ከጤና ጽ/ቤት ደይሬክቶሬትና ከጤና ጣቢያ ኃላፊዎች ጋር የጋራ የግብ ስምምነት ውል በመፈራረም ስብሰባዎቹ ተጠናቀዋል።

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም ጉባኤ እያካሄዱ ነው።     **********13/02/2018 ዓ/ም *****
23/10/2025

በሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የ2017 ዓ.ም ጉባኤ እያካሄዱ ነው።

**********13/02/2018 ዓ/ም *****

ከራስ ጥቅም ባሻገር ለሰው ህይወት ቅድሚያ ሊሰጥ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ አሳሰቡ            ********12/02/2018 ********የሀድያ ዞን ጤ...
22/10/2025

ከራስ ጥቅም ባሻገር ለሰው ህይወት ቅድሚያ ሊሰጥ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ አሳሰቡ

********12/02/2018 ********

የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ "በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ ዕውቅናና ተጠያቂነት ለጠንካራ የጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ግምገማ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አነዮ በዞኑ በርካታ የሰው ኃይል ያለበት መሆኑን አንስተው ጤና ሴክተር በሰው ህይወት የሚሠራበት እንደመሆኑ መጠን ከራስ ጥቅም ባሻገር ለሰው ህይወት ሊሠራ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በዘርፉ አገልግሎት ከመስጠት አንፃር ክፍተት እንዳለ ያነሱት አስተዳዳሪው ከመረጃ አንፃርም ትክክለኛ መረጃ መቅረብ እንደሚገባ ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።

የሀድያ ዞን ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው በኩላቸው ጤና ለሁሉም ነገር መሠረት ስለሆነ ጤናን ማልማት የሁሉም የጋራ ሥራና አገራዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።

ጤና ላይ ካልተሠራ ጤናማ ዜጋን አፍርቶ ጤናማና ተወዳደሪ አገር መሥራት አይቻልም ያሉት አቶ ታምራት ይህን ጤና መገንባት የሚቻለው በተቀናጀ ኃይል በየደረጃው ሲሰራ ነው ብለው፤ ለዚህም የአመራር፣ የባለሙያና የህብረተሰቡ ሚና የጎላ ነው ብለዋል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ በበኩላቸው የጤና ሥርዓትን ከማጠናከር አንፃር በርካታ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቅሰው ለረጅም ዓመታት በማህበረሰቡ ዘንድ ማነቆ ሆነው የቆዩ ችግሮችን ከሥር መሠረታቸው ለይቶ የሰነድ አካል በማድረግ፣ ሰነዱ ላይ በጥልቀት በመወያየትና ማህበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ በተለይም የእናቶችንና ህፃናትን ጤና በማሻሻል ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየታዩ ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎትን ጨምሮ በርካታ ሠራዎች መሠራታቸውን ዶ/ር ደሳለኝ አንስተዋል።

የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ሚካኤል በበኩላቸው ተወዳዳሪና ጠንካራ የጤና ሥርዓት በዞኑ ላይ በመፍጠር በዋና ዋና ተግባራት ክትትልና የአመራር ቁርጠኝነት ያሻልም ነው ያሉት።

አቶ ሀብቴ አክለውም የወባ በሽታ እንደ ክልል ቀዳሚ አጀንዳ እየሆነ መምጠቱን ጠቅሰው፤ ጉዳዩ ለባለሙያና ብቻ የሚተው ሳይሆን የአመራርና የማህበረሰብ የጋራ ርብርብ ያስፈልጋል በማለት በበጀት ዓመቱ በዞኑ በማጤማ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑን ጠቁመዋል።

በመድረኩም የውይይትና የወባ ንቅናቄ ሰነድ በዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ በዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ የቀረበ ሲሆን የእናቶች ጤና አገልግሎት፣ የህፃናት ጤና አገልግሎት፣ የሳንባ ነቀርሳን በሽታ መከላከልና ማከም፣ የጤና መድህን አገልግሎትና የወባ በሽታ መከላከልና ማከም ተጠቃሾች ናቸዉ።

በቀረበው ሰነድ መነሻ ሀሳብ ያነሱ የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት፤ በዞኑ በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው አመርቂ ውጤት የወረዳዎች ድምር ውጤት ነው ብለው፤ ማጤማ ላይ የታየው ጠንካራ የቅንጅት ሥራ በሌሎች ተግባራትም መጠናከር አለበት በማለት የወባ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ልሰጠው ይገባል ብለዋል።

የማህበረሰቡ ህመም ሊያመን ይገባል ያሉት ተሳታፊዎች በተለይ የእናቶችና ህፃናት ጉዳይ አንገብጋቢ በመሆኑ ከወረዳ አምቡላንስ ጋር ተያይዞ ያለው ጉዳይ እልባት ቢያገኝ በማለት በባለሙያ ጥቅማጥቅም ጋር ተያይዞ ያለው ጉዳይ በትኩረት ቢታይ ብለው በተለይም የጤና ተቋማት አገልግሎት እየተሻሻለ ቢሆንም የበለጠ መሻሻል እንዳለበት ሀሳባቸውን አንስተዋል።

ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳብና አስተያየት ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በመጨረሻም የ2018 ዕቅድ ግብ ስምምነት በመፈራረም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች ዕውቅናና የማበረታቻ ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

ምንጭ:- ሀዲያ ቴሌቬዥን
ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ

የዞኑን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥና ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ መዋቅራዊ አሰራሮችን በመከተል በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ ተጠቆመሆሳዕና፦11/02/2018 ዓ.ምየሀድያ ዞን ...
21/10/2025

የዞኑን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥና ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ መዋቅራዊ አሰራሮችን በመከተል በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ ተጠቆመ

ሆሳዕና፦11/02/2018 ዓ.ም

የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ "በባለቤትነት ላይ የተመሠረተ ዕውቅናና ተጠያቂነት ለጤና ሥርዓት ግንባታ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው።

የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ በመክፈቻ ንግግራቸው የዞኑን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ መዋቅራዊ አሰራሮችን በመከተል በቅንጅትና በቁርጠኝነት ሊሠራ ይገባል ብለዋል።

መላው የዞኑ ህብረተሰብ ጤናና ብልፅግና ዕውን ለማድረግ ህብረተሰቡ የራሱንና የአከባቢውን ንፅህና መጠበቅ አለበት ያሉት ኃላፊው በቀጣይ አከባቢው ላይ የወባ ሥርጭት እንዳይስፋፋ ለመከላከል በትኩረት ሊሠራ ይገባልም ነው ያሉት።

በመድረኩም የ2017 አፈፃፀምና የ2018 ዕቅድ ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩም የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤን ጨምሮ፣ የዞኑ ጤና መምሪያ የማኔጅመንት አባላት፣የዞን ጤና መምሪያ ባለሙያዎች እንዲሁም ከሁሉም መዋቅሮች የጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎችን ጨምሮ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት እየተሳተፉ ሲሆን በነገውም ዕለት ጉባኤው የምቀጥል ሆኖ በነገው ዕለት የዞን አስተባባሪ አካላትን ጨምሮ ከየመዋቅሩ የወረዳ አስተዳዳሪዎችና ዋና የመንግሥት ተጠሪዎች እና የዞኑ አመራር ፑል እንደምገኙ ተጠቁሟል።

ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ

 #አስቸኳይ  #ማስታወቂያለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙያ ፈቃድ አገልግሎት አመልካቾች በሙሉ ፡- በሀገር ዐቀፍ ደረጃ በተከሰተ የሲስተም መቆራረጥ ምክንያት ከቀን 5/2/2018 ጀምሮ ላልተወ...
16/10/2025

#አስቸኳይ #ማስታወቂያ
ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙያ ፈቃድ አገልግሎት አመልካቾች በሙሉ ፡-

በሀገር ዐቀፍ ደረጃ በተከሰተ የሲስተም መቆራረጥ ምክንያት ከቀን 5/2/2018 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሙያ ፈቃድ አገልግሎት የማይሰጥ መሆኑን ከታላቅ ይቅርታ ጋር እንገልጻለን።

ችግሩን በአስቸኳይ ለመቅረፍ ከጤና ሚኒስቴር ጋር እየተሰራ መሆኑን እየገለጽን አገልግሎቱ እንደጀመረ በማስታወቅያ የምንገልጽ መሆኑን እናሳዉቃለን።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤናነክ አገልግሎቶች እና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Address

Hosa'ina

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ/Hadiya Zone Health Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram