WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ

WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ Former, the college was called “Otona Hospital” established in 1928 as Small Clinic ; now WSU,CHSM

Wolaita Sodo University College of health science and medicine was established in 1928 as small clinic by Dr Thomas Lambe , missionary. Served for 50 years as primary hospital and for 30 years as general hospital. The hospital amalgamated with Wolaita Sodo University in 2004 E.C with academic responsibility ,demand driven research ,community service and quality clinical services . VISION

The college aspires to be one of the top five colleges of Health Science and Medicine in teaching, demand driven research and community services and quality clinical services nationally and well- well organized college in East Africa by 2020 E.C

MISSION

The college committed to work being engaged in provision of effective teaching and learning , research and community services as well as quality clinical services to the society and to provide its innovative educational philosophy of community based education (CBE) in areas of excellent in academic and professional competence , research adoption ,innovation and knowledge /technology transfer

STRATEGIC THEMES

• Excellent in academic and professional competence
• Excellent in research adoption , innovation and knowledge /technology transfer
• Excellent in quality clinical service
• Excellent in service in different aspects of administration and development issues

በወቅታዊ ሄሞራጅክ ፈቨር ( Hemorrhagic Fever ) በሽታ ቅድመ ጥንቃቄን አስመልክቶ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል =============በሽታውን አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጤና ሚንስ...
13/11/2025

በወቅታዊ ሄሞራጅክ ፈቨር ( Hemorrhagic Fever ) በሽታ ቅድመ ጥንቃቄን አስመልክቶ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል =============
በሽታውን አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጤና ሚንስቴርን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በትኩረት እየተከታተሉ ቢሆንም ተቋማዊ የጥንቃቄና የዝግጅት ሥራዎችን ለመሥራት አስቻይ ውይይት ተካሂዷል ።
-------
ዶክተር ወኪል ወልዴ ፦ በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ፥ የሕብረተሰብ ጤና ስጋት ሲከሰት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት በትኩረትና በቅንጅት የሚሰራ ቢሆንም እንደተቋም ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን መሥራት ወሳኝ ነው ብለዋል ።

ዶክተር አክለው ፤ አስፈላጊውን ግብዓት ለማሟላት (PPE) ፣ የግንዛቤና የጥንቃቄ ሥራዎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።

በውይይቱ የሁሉም ሕክምና ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ሕክምና አገልግሎት ዳይሬክተሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈው በጋራ መግባባት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ።

ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኘነት
ሕዳር 04/2018 ዓ.ም

12/11/2025

ወቅታዊ የጤና ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

ከአምስት መቶ ሺህ ብር በላይ  ዋጋ ያለው ለሕክምና አገልግሎት የሚውል  ድጋፍ ተደረገ ።=========የኢትዮጵያ ስኳር ሕሙማን ማሕበር ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንሰና ሕክምና ኮሌጅ ...
08/11/2025

ከአምስት መቶ ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያለው ለሕክምና አገልግሎት የሚውል ድጋፍ ተደረገ ።
=========
የኢትዮጵያ ስኳር ሕሙማን ማሕበር ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንሰና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንስቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፤ አምስት መቶ ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያለው ለሕክምና አገልግሎት የሚውል ማቀዝቀዣ ድጋፍ አደረገ
==========
ሲስተር ሰላማዊት ገብረ ሀና በሆስፒታሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ሕክምና ክፍል አስተባባሪ ድጋፉ፥ ከኢትዮጵያ ስኳር ሕሙማን ማሕበር ጋር ባደረጉት መልካም ግንኘነት ተጻጽፈው ያመጡት ድጋፍ እንደሆነ ተናግረዋል ።
ሲስተር ሰላማዊት፥ ማሕበሩ የስኳር በሽታን መከላከልና መረጃ ላይ የተመሠረተ የሕክምና እንዲሁም የምክር አገልግሎት አባላቱ እንዲያገኙ በትኩረት እየሠራ ይገኛልም ብለዋል ።

ድጋፉን ዶ/ር ተገኝ ባሼ ፥ በሆስፒታሉ የጤና አገልግሎት ምክትል ኮርፖሬት ዳይሬክተር ፥ ማሕበሩ ያደረገውን አብርቶ አመስግነው ተረክበዋል ።

ዕውቀትን በተግባር!
የተሻለ የጤና አገልግሎት ለሕዝባችን!

ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ቡድን
ጥቅምት 29, 2018 ዓ.ም

ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነጻ የጡት ካንሰር ምርመራና የምክር አገልግሎት    መሰጠት ተጀመረ ።=====================👉 የጡት ካንሰር በሽታን ቀድሞ ማወቅ ከሞት ይታደጋል ።=====...
03/11/2025

ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነጻ የጡት ካንሰር ምርመራና የምክር አገልግሎት መሰጠት ተጀመረ ።
=====================
👉 የጡት ካንሰር በሽታን ቀድሞ ማወቅ ከሞት ይታደጋል ።
==============
ጥቅምት ፥ አለም አቀፍ የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በመሆኑ ፤የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፥ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራና የምክር አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ዶክተር ተገኝ ባሼ በሆስፒታሉ የጤና አገልግሎት ምክትል ኮርፖሬት ዳይሬክተር በፕሮግራሙ መክፈቻ ተናገሩ ።

ዶክተር ተገኝ በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ የሚሰጠውን ነፃ አገልግሎት ወገኖቻችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ መረጃውን በማጋራት እንዲተባበሩም አሳስበዋ።

👉የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ .... ግንኙነት
።።። ጥቅምት 24/2018። ዓ.ም።።።

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የ2018 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች እየገቡ ነው!! በ2017 ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ (ሪሜዲያል) መርሀ-ግብር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመከታተ...
31/10/2025

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የ2018 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች እየገቡ ነው!!

በ2017 ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ (ሪሜዲያል) መርሀ-ግብር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን በመከታተል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በአንደኛ አመት ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች የሠላም አምባሳደር ወደሆነው ዩኒቨርሲቲያችን በመግባት ላይ ይገኛሉ፡፡

የዩኒቨርሲቲው እና የአካባቢው ማሕበረሰብም ደማቅ አቀባባል እያደረገላቸው ሲሆን፤ መደበኛ የምዝገባ ሂደት የሚከናወነው ጥቅምት 21 እና 22/ 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል!!

ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን አረንጓዴ፣ ጽዱ፣ ሠላማዊ፣ ሕብረብሔራዊ እና ተወዳዳሪ ወደ ሆነው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሰላም መጣችሁ!!

Wolaita S**o University

።።።።።። ማስታወቂያ !።።።።።።። ለወላይታ ሶዶ ከተማና አካባቢው ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት በላይ ለሆኑ እናቶቻችንና እህቶቻችን በሙሉ ፤=====================👉 የጡት ካንሰር በሽ...
30/10/2025

።።።።።። ማስታወቂያ !።።።።።።።

ለወላይታ ሶዶ ከተማና አካባቢው ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት በላይ ለሆኑ እናቶቻችንና እህቶቻችን በሙሉ ፤
=====================
👉 የጡት ካንሰር በሽታን ቀድሞ ማወቅ ከሞት ይታደጋል ።
==============
ጥቅምት ፥ አለም አቀፍ የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በመሆኑ ፤ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ፥ ከጥቅምት (21- 30/2018 ዓ.ም) ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራና የምክር አገልግሎት ይሰጣል ።

👉 ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ከጥዋቱ 2 : 00 ሰዓት ጀምሮ በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ የሚሰጠውን ነፃ የጡት ካንሰር ቅድመ ምርመራና የምክር አገልግሎት ተጠቃሚ ይሁኑ ።

ውድ የማሕበራዊ ትስስር ገጻችን ቤተሰቦች ፤ ወገኖቻችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መረጃውን በማጋራት ስለሚተባበሩን ከወዲሁ እናመሰግናለን

👉የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
።።። ጥቅምት 20/2018። ዓ.ም።።።

የሐዘን መግለጫ =====የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ፥ የስፔሻሊቲ ተማሪ ዶክተር አንዷለም ተመስገን በድንገት ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።ዶክተር አንዷለም ተመስገን የመ...
29/10/2025

የሐዘን መግለጫ
=====
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ፥ የስፔሻሊቲ ተማሪ ዶክተር አንዷለም ተመስገን በድንገት ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

ዶክተር አንዷለም ተመስገን የመጀመሪያ ዓመት የውስጥ ዴዌ ሕክምና ስፔሻሊቲ ተማሪ የነበሩ ሲሆን ፤ ዛሬ ጥቅምት 19, 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በድንገት በሞት ተለዩ ።

የኮሌጁ አስተዳደር በዶክተር አንዷለም ተመስገን ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ ፥ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለመላው ባልደረቦች መጽናናትን ይመኛል ።

''ቁንጭር''  የቆዳ  በሽታ  ሕክምና ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ  ተካሂዷል።=======ወ/ ሶዶ /02/ 11–13፣ 2018 ዓ/ም  ====== የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆ...
24/10/2025

''ቁንጭር'' የቆዳ በሽታ ሕክምና ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተካሂዷል።
=======
ወ/ ሶዶ /02/ 11–13፣ 2018 ዓ/ም
======
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር በቁንጭር ('ቦልቦ') ህክምና ዙሪያ የማህበርሰብ አቀፍ ግንዛቤ ማስጨበጥና በህመሙ የተያዙትን የልየታ ስራ ሰርቷል፡፡

የግንዛቤ ማስጨበጫው በኦፋ ወረዳ በሚገኘ ቲዳ ጋርቤ ጤና ጣቢያ እና በካዎ ኮይሻ ወረዳ በሚገኘው ላሾ ጤና ጣቢያ ነው።

የቆዳ ህክምና ባለሙያዎች፣ የትሮፒካል ዴርማቶሎጅ ስፔሻሊስቶች፣ ማይክሮባዮሎጂስት፣ ፓራስቶሎጅስት እና የህብረተሰብ ጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ፤ በሽታውን ለመከላከል እና ለማከም ጠቃሚ መረጃ ተሰጥተዋል ።

ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኘነት
ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ሴክተር  ኮንፍራንስ በበይነ መረብ  እየተካሄደ ይገኛል ።=====ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤ. ሳ.ሕ. ኮሌጅ ።። ።።።የከሰዓት ፕሮግራም ትኩረቱን ያደረገው በInte...
23/10/2025

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ሴክተር ኮንፍራንስ በበይነ መረብ እየተካሄደ ይገኛል ።
=====
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤ. ሳ.ሕ. ኮሌጅ ።። ።።።

የከሰዓት ፕሮግራም ትኩረቱን ያደረገው በIntegrated patient Safety & AMR Strategies for a Resilient Health System ሲሆን ፤ የባለድርሻ አካላት ሀሳብ አስተያየት እየተሰጠ ይገኛል ።

በጉባኤው ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተርን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ።

የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 13/2018። ዓ.ም

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ሴክተር  ኮንፍራንስ በበይነ መረብ ከጥቅት ደቂቃዎች በኃላ ይጀመራል ።====ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ።።ጉባኤውን አስመልክተው ዶክተር ወኪል ወልዴ...
23/10/2025

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ሴክተር ኮንፍራንስ በበይነ መረብ ከጥቅት ደቂቃዎች በኃላ ይጀመራል ።

====ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ።።

ጉባኤውን አስመልክተው ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ገለፃ አደረጉ ።

ኮንፍራንሱ ተረኛ ያልሆኑ ሁሉም ጤና ባለሙያዎች በቀጥታ በበይነ መረብ እንዲሳተፉና በሃገራዊ የጤና ፖሊስ፣ አገልግሎት አሠጣጥ፣ አቅጣጫዎች እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተሳታፊ እንዲሆኑ ዕድል የፈጠራ ነው ብለዋል ።

ጉባኤው የተሻለና የተሳካ እንዲሆን አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ በመሆኑ ፤ትኩረት ሰጥተን እንከታተላለን ሲሉ አሳስበዋል ።

የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኘነት
።።።።። ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም

ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል እንኳን  አደረሳችሁ  በማለት  ከተማሪዎች  ጋራ  በደስታ ተከብሯል ።=========የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬ...
27/09/2025

ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ በማለት ከተማሪዎች ጋራ በደስታ ተከብሯል ።
=========
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር፥ ዶክተር ወኪል ወልዴ እንዲሁም የተማሪዎች አገልግሎት ዲን መምህር መለሰ ማላቆን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተማሪዎችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም መስቀል በዓል በሠላም አደረሳችሁ እያሉ በዓሉን ከተማሪዎች ጋራ በደስታ አክብሯል።

ተማሪዎች ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ሠራተኞች ፤ የተቋሙ የበላይ ኃላፊዎቻችን እንዲህ በበዓላት በአባትነት መንፈስ ሲጠይቁን ያስደስተናል ሲሉ ተናግረዋል ።

መልካም የመስቀል በዓል ።
በዓሉ የሠላም ፣የጤናና የፍቅር ይሁንልን

ዘገባው የኮሌጁ ኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኘነት ነው ።..... መስከረም 17/2018

በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።...
26/09/2025

በምክትል ፕረዚዳንት ማዕረግ
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር ወኪል ወልዴ ፥ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
===
ዶክተር ወኪል ''የተከበራችሁ የኮሌጃችን የክርስትና ዕምነት ተከታይ ክሊኒካል፣ አካዳሚክና አስተዳደር ስታፍ እንዲሁም ደንበኞቻችን በሙሉ ፡

''እንኳን ለመስቀል በዓል በሠላም፤ በጤና አደረሳችሁ! አደረሰን !''

''በዓሉ ፥ ፍቅር የሚገለፅበት ፣ ወዳጅነት የሚጠነክርበት፣ አንድነት የሚጎለብትበት እንዲሆን እመኛለሁ'' ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገለፁ ።

ዶክተር በድጋሚ ፥በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የአብሮነት እንዲሆን ተመኝተዋል ።

መስከረም 16/2018 ዓ.ም፧

Address

Wolaita
Sodo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to WSU College of Health Science and Medicine - ወሶዩ ጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram